በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያ በጋዜጦች


በሳዑዲ አረቢያ የመመለሻ ሠፈር ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያዊያን
በሳዑዲ አረቢያ የመመለሻ ሠፈር ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያዊያን

ኢትዮጵያ በጋዜጦች የተሰኘው ዝግጅታችን በሳምንቱ ውስጥ ስለ ኢትዮጵያ ከተጻፉት የተወሰኑትን ጨምቆ ያቀርባል። ኢትዮጵያ ከአፍሪቃ ሚልዮነሮችን በማፍራት ፍጥነት ብልጫ ማግኘትዋን የሚገልጽ ዘገባ ይገኝባቸዋል።

theguardian የተባለው ድረ ገጽ ያወጣው ጽሁፍ ሳውዲ አረብያ ከውጭ ሀገራት የገቡ ሰራተኞችን ለማስወጣት በወሰደችው ውስኔ መሰረት ሁለት ሚልዮን የሚሆኑ ከሀገር ይወጣሉ ይላል።

በሳውዲ አርበያ በመካሄድ ላይ ያለው የውጭ ተወላጅ ሰራተኞችን የማባረር
ዘመቻ በሀገሪቱ ላይ ችግር ማስክተሉ አልቀረም። የህንጻ ስራ ቦታዎች ባዶ
ቀርተዋል። አስከሪኖችን የሚያጥብ የለም። አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ጠባቂአጥተው ተዘግተዋል። ጅዳ ላይ አይነ-ምድር በሚጠራቅምበት አከባቢ በጽዳት ስራ ላይ ተሰማርተው የነበሩት የውጭ ተወላጆች ፖሊሶች መጡ ሲባል ጥለው በመሄዳቸው አንድ የአይን-ምድር ታንክ ሞልቶ በአስከፊ ሁኔታ ፈሰሰ። ቁሻሻም በየቦታው ተከምሯልሲል ዘገባው አስገንዝቧል።

theguardian ላይ የወጣ ሌላ ጽሁፍ ደግሞ ኢትዮጵያ ሚሊዮንሮችን በማፍራት ፍጥነትዋ “የአፍሪቃ አንበሳ” በሚል እየተመጎሰች ነው ይላል። ኢዮጵያ ከአስርተ-አመት የኢኮኖሚ እድገት በኋላ “በአፍሪቃ አንበሳነት” እየተሞገሰች ነው። መሰረቱ ብሪታንያና ደቡብ አፍሪቃ የሆነው New world Wealth የተባለ ስለ ሀብት ጥናት የሚያካሄድ ተቋም ከስድስት አመታት በፊት በሚልዮኖች ዶላር የሚቆጠር ሀብት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ቁጥር 1,300 ነው የነበረው። እስካለፈው መስከረም ወር ባለው ጊዜ ግን 2,700 ደርሷል ይላል ዘገባው። ሙሉውን ዝግጅት ያድምጡ።
Ethiopia-Press-Review-12-13-13
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:35 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ
XS
SM
MD
LG