በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ጉዞ ላይ ማስጠንቀቂያ አወጣች


አሜሪካ በኢትዮጵያ ጉዞ ላይ ማስጠንቀቂያ አወጣች
አሜሪካ በኢትዮጵያ ጉዞ ላይ ማስጠንቀቂያ አወጣች

ዩናይትድ ስቴትስ ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ ላሰቡ ዜጎቿ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አውጥታለች፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ከትናንት በስተያ ምሽት ላይ ባወጣው ማስጠንቀቂያ ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ አማራና ኦሮምያ ክልሎች ውስጥ በቀጠለው ለብዙ ሕይወት መጥፋት፣ በሺሆች ለሚቆጠሩ ሰዎች መታሠርና መጎዳት እንዲሁም ለተከታታይ የንብረት ውድመትን ምክንያት በሆነው አለመረጋጋት ምክንያት አሜሪካዊያን ወደ ኢትዮጵያ ለማድረግ የያዙትን እጅግ አስፈላጊ ያልሆነ የጉዞ ውጥን ሁሉ እንዲሠርዙ አሳስቧል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በሃገሪቱ ውስጥ ባለው የፀጥታ ሁኔታ ምክንያት የአሜሪካ ኤምባሲ በብዙ የሃገሪቱ ክፍሎች ውስጥ የቆንስላ አገልግሎት ለመስጠት ያለው ችሎታ የተወሰነ መሆኑንም ይኸው የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አመልክቷል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ከመስከረም 28/2009 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መደንገጉን መግለጫው አስታውሶ ጥቅምት 5/2009 ዓ.ም በወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እርምጃዎች አፈፃፀም መመሪያ መሠረት ግለሰቦች ወትሮ የተፈቀዱ የነበሩ ግንኙነት ማድረግን፣ መገናኛ ብዙኃንን መከታተልን፣ በስብሰባዎች ላይ መሣተፍን፣ ከሌሎች መንግሥታት ወይም ከውጭ ድርጅቶች ጋር ግንኙነቶችን ማድረግን፣ የሰዓት እላፊ ገደብን መጣስን የመሳሰሉ ተግባራት ውስጥ ቢገኙ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሊታሠሩ እንደሚችሉ አሳስቧል፡፡

መመሪያው የዩናይትድ ስቴትስና የሌሎችም ሃገሮች ዲፕሎማቶች ለመንግሥት ቀድመው ሳያሳውቁና ፍቃድ ሳያገኙ ከአዲስ አበባ ከአርባ ኪሎ ሜትር ርቀት ዘልቀው እንዳይጓዙ የሚከለክል መሆኑ የአሜሪካ ኤምባሲ ለዜጎቹ ድጋፍ ለመስጠት ያለውን አቅም በብርቱ እንደሚጎዳው መግለጫው አስረድቷል፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ መመሪያው ሙሉ ቃል በአሜሪካ ኤምባሲ ዌብ ሳይት ላይ ሠፍሮ እንደሚገኝም አስታውቋል፡፡

የኢንተርኔት፣ የሞባይል ዳታና የስልክ አገልግሎቶች በመላ ሃገሪቱ ውስጥ በየወቅቱ ወይም ሙሉ በሙሉ የሚቋረጡ መሆናቸውም ኤምባሲው ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ ዜጎች ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት የሚያስተጓጉል መሆኑንም የጉዞ ማስጠንቀቂያው አመልክቷል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ በሚቆዩበት ጊዜ ዜጎቹ አማራጭ የግንኙነት ዝግጅቶች እንዲኖሯቸውና ያለውን ሁኔታም ለቤተሰብና ለወዳጆቻቸው እንዲያሳውቁም የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ መክሯል፡፡

የፀጥታ ማሳሰሲያ መልዕክቶችን ከአሜሪካ ኤምባሲ ለማግኘት መመዝገብ የሚቻልበትን ሁኔታ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ባወጣው በዚህ የጉዞ ማስጠንቀቂያ ሠነድ መጨረሻ ላይ አስፍሯል፡፡ (ከሥር ከተቀመጠው የእንግሊዝኛው የማስጠንቀቂያ ሠነድ በታች ማግኘት ይቻላል፡፡)

ዜጎቹ ሠላማዊ ሰልፎችና ትላልቅ ስብሰባዎች ላይ እንዳይገኙ፣ አካባቢዎቻቸውን ያለመታከት እንዲያጠኑና የሚገኙበትን የግል ደኅንነት ሁኔታ እንደዲገመግሙም የማስጠንቀቂያ ሠነዱ መክሯል፡፡

መንግሥቱ ለሰልፎች ምላሽ ለመስጠት ኃይል ሊጠቀምና ቀጥታ ተኩስ ሊከፍትም እንደሚችልና ሰላማዊ ይሆናሉ የተባሉ ሰልፎችም ያለማስጠንቀቂያ የኃይል ብተና እርምጃ ሊወሰድባቸው ወይም ሰልፎቹ ወደ ሁከት ሊለወጡ እንደሚችሉ ዜጎቹ እንዲያስታውሱ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ አስጠንቅቋል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ ዜጎች የደኅንነት ሁኔታቸውን እንዲከታተሉና በፍጥነት መውጣት ካለባቸውም ሊጠቀሙበት የሚችሉት አማራጭ ዕቅድ እንዲያዘጋጁም አሳስቧል፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ሠራተኞች ኦሮምያን፣ አማራን፣ ሶማሊን፣ ጋምቤላን፣ ደቡብ ኢትዮጵያን ክልሎችና የኢትዮጵያና የኬንያ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያና የኤርትራን የድንበር አካባቢዎች ጨምሮ ወደ ብዙ የሃገሪቱ ክፍሎች የግል ጉዞዎችን እንዳያደርጉ የተገደቡ መሆናቸውንም መግለጫው አመልክቶ ለሥራ የሚደረጉ ጉዞዎች በተናጠል እየታዩ እንደሚፈቀዱም ገልጿል፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ሠራተኞች ወደ አዲስ አበባና አዲስ አበባ ውስጥ ያለ ገደብ መጓዝና መንቀሳቀስ እንደሚችሉ የማስጠንቀቂያው ሠነድ ጠቁሟል፡፡

በአካባቢው ስላለው የአል-ሻባብ እንቅስቃሴ፣ የውንብድና ቡድኖች እና ሌሎችም የደኅንነት ሥጋቶች ኢትዮጵያን በሚመለከተው የመረጃ ምዕራፍ የደኅንነት ክፍሉን ሠነዶች እንዲያዩ መግለጫው መክሯል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የግንኙነት ሁኔታ ለመተንበይ አስቸጋሪ በመሆኑ ምክንያት የዩናይትድ ስቴትስ ዜጎች በስማርት ትራቭለር ኢንሮልመንት ፕሮግራም - ኤስ.ቲ.ኢ.ፒ. /ስቴፕ/ ከሚያደርጉት ምዝገባ በተጨማሪ በቴክስት ወይም ኤስኤምኤስ የደኅንነት መረጃ ማግኘት እንዲችሉ የሞባይል ስልክ ቁጥሮቻቸውን ለኤምባሲው እንዲያስመዘግቡ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ በጥብቅ አሳስቧል፡፡

ተጨማሪ መረጃ ከዚህ በታች ከተቀመጠው የጉዞ ማስጠንቀቂያው የእንግሊዝኛ ቅጂ /ኦሪጂናል ሠነድ/ ሥር ያገኛሉ፡፡

U.S. DEPARTMENT OF STATE

Bureau of Consular Affairs
Washington, DC 20520

For travel information, call 888-407-4747

http://travel.state.gov

October 21, 2016

TRAVEL WARNING

ETHIOPIA

The U.S. Department of State warns U.S. citizens to defer all non-essential travel to Ethiopia due to ongoing unrest that has led to hundreds of deaths, thousands of arrests, as well as injuries and extensive property damage, especially in Amhara and Oromia States. The U.S. Embassy’s ability to provide consular services in many parts of the country is limited by the current security situation.

The Government of Ethiopia declared a State of Emergency effective October 8, 2016. An October 15 decree states that individuals may be arrested without a court order for activities they may otherwise consider routine, such as communication, consumption of media, attending gatherings, engaging with certain foreign governments or organizations, and violating curfews. The decree prohibits U.S. and other foreign diplomats from traveling farther than 40 kilometers outside of Addis Ababa without prior approval from the Government of Ethiopia, which severely affects the U.S. Embassy’s ability to assist U.S. citizens. The full text of the decree implementing the State of Emergency is available on the U.S. Embassy’s website.

Internet, cellular data, and phone services have been periodically restricted or shut down throughout the country, impeding the U.S. Embassy’s ability to communicate with U.S. citizens in Ethiopia. You should have alternate communication plans in place, and let your family and friends know this may be an issue while you are in Ethiopia. See the information below on how to register with the U.S. Embassy to receive security messages.

Avoid demonstrations and large gatherings, continuously assess your surroundings, and evaluate your personal level of safety. Remember that the government may use force and live fire in response to demonstrations, and that even gatherings intended to be peaceful can be met with a violent response or turn violent without warning. U.S. citizens in Ethiopia should monitor their security situation and have contingency plans in place in case you need to depart suddenly.

U.S. government personnel are restricted from personal travel to many regions in Ethiopia, including Oromia, Amhara, Somali and Gambella states, southern Ethiopia near the Ethiopian/Kenyan border, and the area near the Ethiopia/Eritrea border. Work-related travel is being approved on a case-by-case basis. U.S. government personnel may travel to and within Addis Ababa without restrictions. For additional information related to the regional al-Shabaab threat, banditry, and other security concerns, see the Safety and Security section of the Country Specific Information for Ethiopia.

Due to the unpredictability of communication in the country, the Department of State strongly advises U.S. citizens to register your mobile number with the U.S. Embassy to receive security information via text or SMS, in addition to enrolling in the Smart Traveler Enrollment Program (STEP).

For further information:

XS
SM
MD
LG