በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢትዮጵያ መንግሥት “የኃይል እርምጃ” እና የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት ትችት


Philip Manshaus, with black eyes and wounds on his face and neck, appears with his lawyer Unni Fries in court in Oslo, Norway. Manshaus, 21, is suspected of an armed attack at Al-Noor Islamic Centre Mosque and killing his stepsister.
Philip Manshaus, with black eyes and wounds on his face and neck, appears with his lawyer Unni Fries in court in Oslo, Norway. Manshaus, 21, is suspected of an armed attack at Al-Noor Islamic Centre Mosque and killing his stepsister.

“ይህ የኢትዮጵያ መንግሥት ይበልጥ አምባገነናዊ ወደሆነ አስተዳደር እያመራ ያለበትን አዝማሚያ የሚጠቁም ሌላ አዋኪ ምልክት ነው። ውስብስቡን ውስጣዊ የፖለቲካና የክልል አወቃቀር፤ እንዲሁም ከባድ ሊሰኙ የሚችሉትን ታሪካዊ ገጠመኞቻቸውን እገነዘባለሁ። ይሁንና መንግሥቱ በቅርቡ የወሰዳቸው የኃይል እርምጃዎች ግን ዘለቄታ ላለው ዲሞክራሲ ተጨባጭ አደጋዎች ናቸው።” ሴናተር ክሪስ ኩንስ በየዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ንዑስ ኮሚቴ አባል።

የኢትዮጵያ መንግሥት እየወሰደ ያለው የኃይል እርምጃ ያሳሰባቸው መሆኑን አንድ ሌላ የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባል ተናገሩ።

በምክር ቤቱ የውጭ ጉዳዮች ንዑስ ኮሚቴ አባል ሴናተር ክሪስ ኩንስ በተለይ ከአሜሪካ ድምጽ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የኢትዮጵያ መንግሥት ይበልጥ አምባገነናዊ ወደሆነ አዝማሚያ እያመራ መሆኑን የሚጠቁም ነው፤ ሲሉም ያደረባቸውን ሥጋት ገልጠዋል።

የኢትዮጵያን ጉዳይ የሚከታተሉ መሆናቸውን የተናገሩት ሚር ኩንስ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና በንግግር ነፃነት ላይ የጣላቸው ገደቦችም ሌላው አሳሳቢ ጉዳዮች ናቸው፤ ሲሉ ተችተዋል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት “የኃይል እርምጃ” እና የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት ትችት
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:56 0:00

XS
SM
MD
LG