በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሶማሌ ክልል በድርቅና ኮሌራ ሕይወት ጠፋ ሲል ኦብነግ አስታወቀ


ሶማሌ ክልል
ሶማሌ ክልል

በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ድርቅና ኮሌራ የዜጎችን ኑሮ እየጎዱ መሆኑን ጠቅሶ ባለፉት አራት ቀናት ከሰላሣ ሰዎች በላይ መሞታቸውን የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) አስታውቋል።

በክልሉ ከአንድ ሚሊዮን ሦስት መቶ ሺህ በላይ ሰዎች በድርቅ ምክንያት ለምግብ እጥረት በመጋለጣቸው ለበርካታ ወራት የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ሲደረግላቸው መቆየታቸውን የብሔራዊ የአደጋ ስጋትና አመራር ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሣ አመልክተዋል፡፡

በአካባቢው የዳይር ዝናብ መስተጓጎሉን ኮሚሺነሩ ገልፀዋል።

በክልሉ ተከስቶ የቆየውን የኮሌራ በሽታ ለመቆጣጠርም የጤና ጥበቃ ሠራተኞች የተሣካ ሥራ ማከናወናቸውን አቶ ምትኩ አስረድተዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ከተለያዩ አካላት የተውጣጣ ግብረ ኃይል ከነገ ጀምሮ በመላ ሃገሪቱ የድርቁን ሁኔታ እንዲገመግም እንደሚያሠማራ አስታውቋል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

በሶማሌ ክልል በድርቅና ኮሌራ ሕይወት ጠፋ ሲል ኦብነግ አስታወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:33 0:00

XS
SM
MD
LG