በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጅ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ተግባራዊ ሊደረግ ነው


ኢትዮጲያውያን ጋዜጠኞች በናይሮቢ ኬንያ እአአ 2006 ጋዜጠኞች ነፃ እንዲወጡ ጥሪ እያቀረቡ /ፋይል ፎቶ/
ኢትዮጲያውያን ጋዜጠኞች በናይሮቢ ኬንያ እአአ 2006 ጋዜጠኞች ነፃ እንዲወጡ ጥሪ እያቀረቡ /ፋይል ፎቶ/

የኢትዮጵያ መንግሥት በፀር ሽብር ሕጉን በሀገር ውስጥ ፖለቲካው ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ለማድረግ እየተጠቀመበት ነው በሚል መከሰስ ከጀመር አራት ዓመታት ተቆጥሯል። አሁን ደግሞ የኢንተርኔት አምደኞች እና ፖለቲከኞች ሐሳብን የመግለጽ ነፃነትን የበለጠ ስጋት ላይ የሚጥል አዲስ የኮምፒዩተር ረቂቅ ወንጀል ዐዋጅ ወጥቷል።

በሚያዝያ ወር 2008 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጅ እየተተቸ ከሚገኝበት ነገር አንዱ ሐሳባቸውና የግል አመለካከታቸውን በኢንተርኔት አማካኝንት የሚገልጹ ግለሰቦችን የኢትዮጵያ መንግሥት አሥሮ የሚቀጣበት አንቀጽ ማካተቱ ነው።

ይሄ የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጅ በወንጀለኛ መቅጫ ሕጉም ኾነ በመገናኛ ብዙሐን ሕጉ የተሰጡንን መብቶች የሚጥስ ነው። እስካሁን ካሉት ሕጎች ሁሉ የበለጠ ከልካይ ነው። በአንድ ዓረፍተ ነገር ብቻ ይከለክላል።
ዳንኤል ብርሃኔ በኢትዮጵያ የሚገኝ የኢንተርኔት አምደኛ

ዳንኤል ብርሃኔ በኢትዮጵያ የሚገኝ የኢንተርኔት አምደኛ ነው። የራሱ ድረ ገጽም አለው። አዲሱ የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጅ ሐሳቡን በኢንተርኔት አማካኝነት በሚገልጽ በማንኛውም ግለሰብ ላይ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል ዐዋጅ ነው ብሎ ያምናል።

“ይሄ የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጅ በወንጀለኛ መቅጫ ሕጉም ኾነ በመገናኛ ብዙሐን ሕጉ የተሰጡንን መብቶች የሚጥስ ነው። እስካሁን ካሉት ሕጎች ሁሉ የበለጠ ከልካይ ነው። በአንድ ዓረፍተ ነገር ብቻ ይከለክላል” ይላል።

የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጁ በአብዛኛው ትኩረት የሚያደርገው በኢንተርኔት አማካኝነት በሚፈጸሙ ወንጀሎች ላይ ነው። ነገር ግን አንድ ሰው በኢንተርኔቱና በኮምፒዩተሩ አማካኝነት ወንጀል ፈጽሟል ብቻ ሳይኾን ወንጀል ተፈጽሞበታል ተብሎ ከተገመት ያለ ምንም ፍርድ ቤት ፍቃድ እና ትእዛዝ ብሔራዊ ደሕንነት ኮምፒዩተሩን በአካል ሳይነካ እንዲመረምር ሥልጣን የሚሰጠው አንቀጽ በረቂቁ ውስጥ ተካቷል።

ኢትዮጲያውያን ጋዜጠኞች በናይሮቢ ኬንያ እአአ 2006 ጋዜጠኞች ነፃ እንዲወጡ ጥሪ እያቀረቡ /ፋይል ፎቶ/
ኢትዮጲያውያን ጋዜጠኞች በናይሮቢ ኬንያ እአአ 2006 ጋዜጠኞች ነፃ እንዲወጡ ጥሪ እያቀረቡ /ፋይል ፎቶ/

በኢትዮጵያ ፍትሕ ሚኒስቴር ዳይሬከተር የኾኑት አቶ በላይይሁን ይርጋ ረቂቅ ዐዋጁ ሐሳባቸውን በኢንተርኔት በነፃነት ከሚገልጹ ሰዎች ጋር ምንም ግንኙነት የለውም ይላሉ።

“አንድ ሰው የእራሱን ሐሳብና አመለካከት ከተናገረ ብቻ በወንጀል ተጠያቂ አይኾንም። የዚህ ሕግ ዋና ዓላማ ግን ሰዎች ከስም ማጥፋት ጋር በተያያዘ ለድርጊታቸው የሚኖራቸው ዓላማ ነው። ዋነኛ ዓላማቸውና ግባቸው ስም ማጥፋት ከኾነ ተጠያቂ ይኾናሉ።ም ክንያቱም ስም ማጥፋት ወንጀል ነው” ብለዋል።

ኢትዮጵያ በኢንተርኔት አማካኝነት ሐሳባቻውን የሚገልጹ ግለሰቦችን በማሰቃየት፣በማሰር እና ረጅም ዓመታት በመፍረድ በተደጋጋሚ ትወቀሳለች። በዚህ ሰለባ ከኾኑት መካከል 18 ዓመት እስር ተፈርዶበት እስር ቤት የሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር

ነጋ አንዱ ነው። እንዲሁም የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ከአንድ ዓመት በላይ እስር ቤት ማሳለፋቸው ሌላው ተጠቃሽ ጉዳይ ነው።

የተቀናቃኝ የፖለቲካ ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት የነበረው አቶ ዮናታን ተስፋዬ ፌስ ቡክ ገጹ ላይ ባሰፈረው አስተያየት አማካኝነት ከታሠረ ስድስት ወራት ተቆጥሯል።

ሃበን ፈቃዱ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት በሆነው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሠራተኛ ነች የኢትዮጵያ መንግሥት በፀር ሽብር ሕጉን በሀገር ውስጥ ፖለቲካው ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ለማድረግ እየተጠቀመበት ነው ትላለች። የአቶ ዮናታንን ጉዳይም በምሳሌነት ትጠቅሳለች።

“በዮናታን ክስ ላይ የቀረቡት ማስረጃዎች በጣም አሳሳቢና መንግሥት አንድን ግለሰብ በማኅበራዊ ድረ ገጾች ላይ በሚጽፋቸው ነገሮች ላይ ተመስርቶ እንዲያሥር የሚፈቅድ ነው። ዮናታን የታሠረው በጸር ሽብር ሕጉ አማካኝነት ነው። ምን አይነት ማስረጃ እንደሚቀርብበት እንኳን ሳያውቅ ነው ፍርድ ቤት የቀረበው” ትላለች።

ይሄ የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጅ በሚቀጥለው ሳምንት ተግባራዊ የደረጋል ተብሏል።

ማርታ ቫንዶርፍ ከአዲስ አበባ ያደረሰችን ዘገባ ጽዮን ግርማ ታቀርበዋለች። ዝርዝሩን ከተያያዘው ድምጽ ያድምጡ።

የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጅ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ተግባራዊ ሊደረግ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:09 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG