በዩናይትድ ስቴትስ የሚደገፉት የሶርያ ዲሞክራስያዊ ኃይሎች እስላማዊ መንግሥት ነኝ በሚለው ፅንፈኛ የአማፅያን ቡድን ተይዘው የነበሩ 41 ቦታዎችን አስመልሰናል አሉ።
ዩናይትድ ስቴትስ የዣማል ኻሾግዢን ግድያ መመርመሩን ትቀጥላለች። “አሜሪካ ስለግድያው ለመሸፋፈን የሞከረቸው ነገር የለም” በማለት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፓምፔዮ ተናገረዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ የኢሚግረሽን ፖሊስን አስመልክቶ የሚካሄደው ንግግር ባለበት መቆም ተጠያቂዎች ዲሞክራቶች ናቸው ሲሉ ዛሬ ነቅፈዋል።
የዓረብ ሊግ የባሻር አል አሳድን ሦሪያ እንደገና በአባልነት እንዲቀበል ሩሲያ ማግባባት ይዛለች ሲሉ በአካባቢው የተመደቡ ዲፕሎማቶች ተናገሩ።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ እራሡን "እስላማዊ መንግሥት ነኝ" ብሎ በአወጀው በፅንፈኛው ቡድን ላይ ድል መጎናጸፋቸውን በመጪው ሣምንት በይፋ እንደሚያሳውቁ ተናገሩ።
የቬነዝዌላ ወታደሮች ከዩናይትድ ስቴትስና ሌሎች ሃገሮች የሚላከውን ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማገድ - ቁልፍ የድንበር መተላለፊያ በር ዘግተዋል።
መቀዶኒያ ኔቶን ለመቀላቀል የሚያስችላትን ቁልፍ የሥምምነት ሰነድ ዛሬ ፈርማለች።
በፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕና በሰሜው ኮርያው ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን መካከል የሚካሄደውን የሁለተኛ ዙር ውይይት ዝግጅት ለማጠናቀቅ፣ የዩናይትድ ስቴትሱ የሰሜን ኮሪያ ልዩ መልዕክተኛ በዚህ ሳምንት ወደ ፕዮንግያንግ እንደሚጓዙ ተገለፀ።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዛሬ፤ ማክሰኞ - ጥር 28/2019 ዓ.ም. ምሽት ላይ ለተወካዮች ምክር ቤቱ ጥምር ጉባዔ በሃገራቸው አጠቃላይ ሁኔታ ላይ ንግግር ያደርጋሉ። በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕና በተወካዮች ምክር ቤቱ አፈጉባዔ ናንሲ ፔለሲ መካከል የተፈጠረው መፋጠጥ ለውጥ አላሳየም። ሌላ የመንግሥት መዘጋት ዙር፣ ወይም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሥጋት አሜሪካ ላይ አንዣብቧል።
ከሊብያ ወደ ሰሜን ቻድ በሰልፍ ያመሩ የነበሩ 40 ፒክ-አፖ መኪናዋችን እንደመለሰ፣ የፈረንሳይ ወታደራዊ ጦር አስታወቀ።
ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ሃሰተኛ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ውስጥ የሚማሩ በማስመሰል የተመዘገቡ 138 ሰዎችን መንግሥቱ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አንድ ፌደራል ባለሥልጣን አስታወቁ። ባለሥልጣኑ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ተጨማሪ ሰዎችም ሰሞኑን እንደሚያዙ አረጋግጠዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ ከአሥርት ዓመታት በላይ ከቆየው ሁሉንም ዓይነት የኑክሌር ጦር መሣሪያ ግንባታ ከሚያግደው ዓለምቀፍ ሥምምነት መውጣቷን ዛሬ አስታውቃለች።
አዲሱ የማሌዥያ ንጉሥ ዛሬ በተደረገው የንግሥና ስነ ሥርዓት በትረ ሥልጣኑን በኦፊሴል ተረክበዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ከሜክሲኮ ጋር በሚዋሰነው ድንብር ላይ ግንብ ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት ዛሬ በአዲስ መልክ አጠናክረውታል። የሀገሪቱ ምክር ቤት ለግንቡ የሚሆን ባጀት ባይመድብላቸውም እንኳን “በሆነው መንገድም ቢሆን” ይገነባል ብለዋል።
የብሪታንያ ከአውሮፓ ህብረት መውጣትን አስማልክቶ የሀገሪቱና የአውሮፓ ህብረት ተደራዳሪዎች ዛሬ የተለያየ አመለካከት አንፀባርቀዋል።
ኢራን የሳይበር ሥለላ ሥራዋን በማስፋት ዋና ዋና የፖለቲካና የቢዝነስ ባለሥልጣኖችን እንቅስቅሳሴ ለመከታተል የሚያስችላት መረጃ እየሰረቀች ይመስላል ይላሉ የዜና ዘገባዎች።
በዓለም ደረጃ ሙስናን የሚታገለው ቡድን እንደሚለው በፀረ ሙስና ጥረት ውስጥ ከፈረጃቸው ሀገሮች መካከል ዩናይትድ ስቴትስ በአራት ነጥብ ወደ ኋላ ቀርታለች ይላል። ዩናይትድ ስቴትስ ለመጀመርያ ጊዜ ከፍተኛ ቦታ ከተሰጣቸው ሀገሮች ዝርዝር ወጥታለች።
የፓኪስታን ከፍተኛ ፍርድ ቤት “የእስልምናን እምነት ስም አጉድፋለች” በሚል በሀሰት የተከሰሰችውን ክርስትያን ሴት በነፃ መለቀቅን አፅድቋል፤ ለአስርት ዓመት በዘለቀ የፍርድ ሂደት፡፡
የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሳዑዲ ተወልጅ ጋዜጠኛ ዣማል ኻሾግዢ አገዳደልን አስመልክቶ ከሚመረምረው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፍርድ ጠቢብ ጋር ዛሬ ተገናኝተው ተነጋገረዋል። ቱርክ ዓለምቀፍ ምርመራ እንዲካሄድበት እየጠየቀች ነው።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ የምክር ቤት ተደራዳሪዎች በደቡባዊው የሀገሪቱ ድንበር ግንብ ለመገንባት የሚያስችል ሥምምነት ያቀርባሉ የሚለው ግምታቸው ከአምሳ ከመቶ ያነሰ መሆኑ ገልፀዋል።
“... አብይ አሕመድ ጥረቶቻቸው እንደሚሳኩላቸው የብዙዎች ተስፋ ነው ...” ሲል ፎረን ፖሊሲ ፅፏል።
ሼኽ መሐመድ ሁሴን አል-አሙዲ ወደ ኢትዮጵያ የሚመለሱት መቼ እንደሆነ ለጊዜው አይታወቅም።
በቬነዝዌላ ሁኔታዎች ከቁጥጥር ውጭ ወጥተው ብዙ ደም ከመፋሰሱ በፊት ሰላማዊ ንግግር እንዲጀመር የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ከፍተኛ ባለሥልጣን ሚሼል ባሽሌ ጥሪ አቀረቡ።
የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ የቀድሞ ፖለቲካ አማካሪ ሮጀር ስቶን - ዛሬ በቁጥጥር ሥር ዋሉ፣ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሏል።
በአፍጋኒስታን ለ17 ዓመታት የዘለቀውን ጦርነት በፖለቲካ ድርድር ለማብቃት በዩናይትድ ስቴትስና በታሊባን መካከል ኳታር ውስጥ የሚካሄደው የሰላም ንግግር መቀጠል ትልቅ ተስፋ አሳድሯል።
ተጨማሪ ይጫኑ