ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ሚጌል ዳያዜል ካኔል ቤርሞዴዝን ለቀጣዩ ኩባ ፕሬዚዳንትነት ብቸኛው ዕጩ አድርጎ ማቀረቡን የኩባ መንግሥት አስታወቀ።
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ የአሜሪካ የመረጃ ድርጅት ሲአይኤ ዳይሬክተር ማይክ ፖምፒዮ ከሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ጋር በሚስጥር ተገናኝተው ተነጋግረዋል የሚለውን ዜና “ትክክል ነው” ሲሉ ዛሬ አረጋገጡ።
“በእኔ ዓይን .. የወደፊቷ ኢትዮጵያችን የፖለቲካ እስረኞች የሌሉባት እንድትሆን ማሰብ ብዙዎች ይስማሙበታል ባይ ነኝ።” ጌብ ሃምዳ (ዶ/ር) “ይሄ መንግስት አዋላጅ መንግስት ከመሆኑ በፊት .. አዋላጅ ባለ ሥልጣናት አንዲመጡ ያስፈልጉታል። ዶ/ር አብይ የመጡበትም ይሄው የአዋላጅ ባለ ሥልጣን አካሄድ ነው።” ዘላለም እሸቴ (ዶ/ር)
ሶሪያ ላይ ትናንት የተካሄደው ጥቃት እጅግ የተዋጣ እንደነበርና ከዚህ በተሻለ ሁኔታ ሊከናወን እንደማይችል ዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ዛሬ አስታውቀዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ፣ እንግሊዝና ፈረንሣይ በሶሪያ ላይ የከፈቱት የተቀናጀ ጥቃት እየተካሄደ መሆኑን ፕሬዚዳንት ትረምፕ አስታወቁ።
የታሊባን ሽምቅ ተዋጊዎች ምዕራብ አፍጋኒስታን ውስጥ አንድ የመንግሥቱን የፀጥታ መቆጣጠሪያ ጣቢያ አጥቅተው በትንሹ 11 ወታደሮችን ገድለዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አምስት አባላት ሰሞኑን አራት የአፍሪካ ሃገሮችን በጎበኙበት ወቅት የተደረገላቸው አቀባበል የሞቀ እንደነበርና በትረምፕ አስተዳደር ላይ የተሰሟቸውን ቅሬታዎች የገለፁላቸው እንደነበሩ አመልክተዋል።
ታሊባን ዛሬ ማለዳ ደቡብ ምሥራቃዊቱ ጋዝኒ ክፍለ ሃገር ውስጥ ባደረሰው ጥቃት አንድ የአውራጃ ዋና አስተዳዳሪና ሰባት ፖሊሶችን ገድሏል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በሦሪያ ተፈጸመ የተባለውን ኬሚካዊ የጦር መሣሪያ ጥቃት አስመልክቶ በዛሬው የትዊተር መልዕክታቸው “ዩናይትድ ስቴትስ በሦሪያ ላይ ጥቃት የምትከፍትበትን ቀን ፈፅሞ አልተናገርኩም” ብለዋል። “ጥቃቱ ፈጥኖም፣ ዘግይቶም ሊካሄድ ይችላል” ይላል የትዊተር መልዕክታቸው።
“በመጀመሪያ ደረጃ የምክር ቤቱን ተቆርቋሪነት ያሳያል። እና ይሄ ሕገ-ውሳኔ የአሜሪካ መንግስት ኢትዮጵያ ውስጥ በሚካሄደው የሰብዓዊ መብት ረገጣ፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን፣ የሕዝብን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላው በግዴታ መባረርን፣ እናም የሕግ አልባነትን በመቃወም የወጣ ውሳኔ ነው።” ፍጹም አቻምየለህ ሂደቱን የተከታተሉ እና በዋሽንግተን ዲሲና በአካባቢው በጥብቅና ሥራ የተሰማሩ የሕግ ባለ ሞያ
"የሩሲያ ኃይሎች ወደ ሦሪያ የሚተኮሱ ማናችውንም ሚሳይሎች አየር ላይ ቀልበው ይጥላሉ" ሲሉ በሊባኖስ የሩሲያ አምባሳደር ከተናገሩ በኋላ የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ትረምፕ መልስ ሰጥተዋል።
የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ የግል ጠበቃ ቢሮ እንዲበረበር የፍርድ ቤት ማዘዣ አውጥተው ዋራንቱን ተፈፃሚ ባደረጉት ልዩ መርማሪ ራበርት መለር እርምጃ ፕሬዚዳንቱ በብርቱ ቢቆጡም የማባረር ሃሣብ እስካሁን አለማንፀባረቃቸው እየተነገረ ነው።
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚደንት የዶናልድ ትረምፕ የሀገር ውስጥ ደኅንነት ከፍተኛ አማካሪ ቶም ቦሰርት ባልተጠበቀ ሁኔታ ዛሬ ማክሰኞ ሥራቸውን ለቀቁ፤ ሌሎች ሥራችውን ለመተው ከሚጠባበቁ ከፍተኛ የፕሬዚዳንቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት አንዱ እንደሆነም ታውቋል።
ሦርያ ፈጽማለች ተብሎ ለተጠረጠረው የኬሚካል ጦር መሣሪያ ጥቃት ምን እርምጃ እንደሚወስዱ አሰተዳደራቸው እያጠና መሆኑን የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ አስታወቁ።
ፓኪስታን፣ ከአፍጋኒስታን ጋር በሚያዋስናት ምሥራቅዊ ኩናረ ክፍለ ሃገር ውስጥ ባደረሰችው ጥቃት አንድ ሲቪል መሞቱን የአፍጋኒስታን ባለሥልጣናት አስታወቁ።
ዋይት ኃውስ በሰጠው መግለጫ፤ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በዚህ ሳምንት ማብቂያ ገደማ ወደ ላቲን አሜሪካ ሊያደርጉ ያቀዱትን ጉዞ መሰረዛቸውን አመልክቶ፤ ሦርያን በተመለከተ የዩናይትድ ስቴትስን ምላሽ ለመከታተል መሆኑንም አስታውቋል።
የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላዲሚር ፑቲን፣ ሃገራቸው ሩሲያና ኢራን ከትናንት በስተያ ቅዳሜ የሶሪያዋ ዱማ ከተማ ላይ ለተፈፀመው የኬሚካል ጥቃት “ተጠያቂ ናቸው” ሲሉ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ክሥ አሰምተዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ መከላከያ ሚኒስትር ጂም ማቲስ አሜሪካ ሶርያ ውስጥ ለተፈፀመው የኬሚካል መሳርያ ጥቃት ወታደራዊ እርምጃ ልትወስድ እንደምትች አመላክተዋል። ማቲስ ይህን ያሉት ባለፈው ቅዳሜ ለተፈፀመው “ትርጉም የለሽ የኬሚካል ጥቃት” ላሉት “ከባድ ዋጋ ይከፈልበታል” ሲሉ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትዊተር ከገለጹ በኋላ ነው።
በእሥራኤል የጋዛ ሠርጥ ወሰን ላይ ዛሬ በተነሣ ግጭት ቢያንስ አንድ ፍልስጥዔማዊ ተገድሎ ሌሎች ቁጥራቸው አርባ የሆነ ሰዎች ቆስለዋል። ግጭቱ የተፈጠረው ከአንድ ሣምንት በፊት በዚያው አካባቢ ተካሂዶ በነበረ ሁከት የበረታበት የተቃውሞ እንቅስቃሴ 19 ፍልስጥዔማዊያን በእሥራኤል ወታደሮች መገደላቸውን ተከትሎ ነው።
የሜክሲኮ የፍትህ ሥርዓት ወደ ሰሜን አንዳንዶቹም ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ያመሩ የነበሩትን ብዛት ያላቸው ፍልሰተኞችን በመበተኑ ፕሬዚዳንት ትረምፕ አሞግሰውታል።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ትናንት ረቡዕ አሜሪካ ከቻይና ጋር የንግድ ጦርነት እያካሄደች አይደለም ብለዋል።
የሰሜንና የደቡብ ኮርያ መሪዎች በያዝነው ወር ተገናኝተው እንዲነጋገሩ በታቀደው መሰረት የሁለቱ ሀገሮች ባለሥልጣኖች የዝግጅት ንግግር አካሄደዋል። ሁለቱ መሪዎች የሚገናኙት የሰሜን ኮርያ የኑክሌ እንቅስቃሴ ያስከተልውን ውጥረት ለማርገብ ጥረት በሚደርገው ወቅት ነው።
በርካታ የዩናይትድ ስቴትስ ዲፕሎማቶችና ቤተሰቦቻቸው ዛሬ ሞስኮ ከሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ተነስተዋል። ሩስያ ጥንድ ሥለላ ያካሄዱ የነበሩ ሩስያዊ ሠላይን መርዛለች በሚል ክስ በአሜሪካና በሩስያ መካከል በተደርገው የዲፕሎማቶች መበረር እርምጃ ምክንያት ነው አሜሪካውያኑ ዲፕሎማቶቹ ከሩስያ የተነሱት።
በአሜሪካ የሲቪል መብቶች ለማስከበር በሚሊዮኖች የተቆጠረ ህዝብ ያንቀሳቀሱት ቄስ ዶክተር ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር በነፍሰ ገዳይ ጥይት ከተገደሉ ዛሬ ሃምሳ ዓመት ተቆጠረ።
ቻይና የ50 ቢልዮን ዶላር ቀረጥ በዩናይትድ ስቴትስ ዕቃዎች ላይ የመደንገግ ዕቅድ እንዳላት ዛሬ አስታወቀች። ዩናይትድ ስቴትስ ለደነገገችው ተመሳሳይ ቀረጥ ምላሽ መሆኑ ነው።
ተጨማሪ ይጫኑ