የምግብ ዋስትናን በዓለም ዙሪያ ማረጋገጥ የዩናይትድ ስቴትስ ጥቅም ጉዳይ መሆኑ ላለፉት ሁለት ቀናት መጋቢት 20 እና መጋቢት 21 / 2009 ዓ.ም. ዋሺንግተን ዲሲ ላይ በተካሄደው ዓመታዊው የዓለም የምግብ ዋስትና ጉባዔ ላይ ተገልጿል፡፡
ጆአኪም ደመር ይባላል። ስዊድናዊ የዶክሜንትሪ ወይም የዘጋቢ ፊልም ሠሪ ነው።
የዩናይትድ ስቴትስ ቀዳማዊት እመቤት ሜለኒያ ትራምፕ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በትላንትናው ዕለት እዚህ ዋሺንግተን ዲሲ ባዘጋጀው የ2017 ዓ.ም. ዓለምቀፍ የጀግና ሴቶች ሽልማት ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል።
የዓለም ሚቲኦሮሎጂ ቀን መጋቢት 14 “ደመናን መረዳት” በሚል መሪ ቃል በመላው ዓለም ታስቦ ውሏል፡፡
ሰሜን ኮሪያ ምንም እንኳ ዓለምቀፍ ማዕቀብ ቢጣልባትና እንድትገለል ቢደረግም፣ የጦር መሣሪያ ለመግዛትና የጋራ መከላከያ ስምምነት ለመፈራረም፣ ፍላጎት ያላቸው በርካታ የአፍሪካ ሀገሮችን ሽርክና ማግኘት ችላለች ይላል፤ ምርመራውን ያካሄደው የተባበሩት መንግሥታት ባለሞያዎች ቡድን።
ካሁን በሁዋላ ከስማርት ፎን የተለቁ የኤሌክትሮኒክ መሣሪያዎች ሁሉ ወደ አውሮፕላን የሚገቡት ተመርምረው ይሆናል ተብሏል።
ስለዚህ ጉዳይ ኋይት ሃውስ መልስ እንዲሰጥ ቪኦኤ ጠይቆ ምላሽ አላገኘም።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ትናንት ይፋ ያደረጉት የ“አሜሪካ ትቅደም” በጀት በሃገር ውስጥም፣ በሃገር ውስጥም ከሃገር ውጭም እያነጋገረ ነው፡፡
“የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ባይታወጅ ኖሮ የት ነው የሚቆመው አመጹ? የት ነው ጋብ የሚለው ነገር በጣም አጠያያቂ ነው የነበረው።” አቶ አታክልት አምባዬ። “የአስቸኳይ ጊዜውን አዋጁን ያወጁትም ሰዎች መፍትሔው እንፈልጋለን መፍትሔ አልተፈለገም። መፍትሔው ምንድ ነው? ችግሩ ምንድነው? የሚለው ነገር ላይ ውይይት አላየንም።” አቶ ፈቃደ ሸዋ ቀና።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ “አሜሪካ ትቅደም” በጀታቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡
“በተለያዩ ሁኔታ በፍርድ ቤት ሂደቶች አልፈው ጉዳያቸው ሳይሳካላቸው ቀርቶ ነገር ግን ወንጀል ስለሌላቸው ሊሆን ይችላል ከአገር ያልተባረሩ፤ በዓመት ወይ በስድስት ወር አንዴ ወደ ኢሚግራሽን መሥሪያ ቤት እየፈረሙ በሰላም የመሚኖሩ .. ለእነኚህና ለሌሎች አሁን አሳሳቢ ሁኔታ እየተፈጠረ ነው።” የሚ ጌታቸው በካሊፎኒያ የአሜሪካ የሕግ-ጠበቆች ማኅበር የሳንታክላራ ቫሊ ሊቀመንበር።
በቱርክና በአውሮፓ ኅብረት መካከል ያለው ውጥረት እየተባባሰ መምጣቱን በአህጉሪቱ ውስጥ ባለው የስደት ጉዳይ ላይ አሳሳቢ ጥላ እንዲያርፍ ማድረጉ ተገለፀ፡፡
“የልብ ትርታ መረበሽ ብዙውን ጊዜ ያንን ያህል ለጤና የሚያሰጋ ነገር የለውም። ምን ሊሆን ይችላል በሚል ግለሰቡን ማሳሰቡ ነው። ነገር ግን ረዘም ላለ ጊዜ ተደጋግሞ ሲመጣ፥ ከእርሱ ጋር ተያይዞም የትንፋሽ ማጠር እና ደረት ላይ ጫና በሚሰማበት ጊዜ ግን ሌላ ክትትል ሊያስፈልገው ይችላል።” ዶ/ር ውብሸት አየነው የልብ ሕክምና ከፍተኛ አማካሪ ሃኪም ናቸው።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ከእርሣቸው የቀደሙት ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ “በምርጫው ወቅት ኒው ዮርክ በሚገኘው ሕንፃዬ ላይ የስልክ መሥመሮቼን ጠልፈው ይሰልሉኝ ነበር” ሲሉ ላሰሙት ክሥ ዋይት ሃውስ ቤተመንግሥት ማስረጃ እንዲያቀርብ ግፊቱ አሁንም እንደበረታ ነው፡፡
ጠቅላላው የሰብዓዊ መብቶች አጠባበቅ ሥርዓት በሽብርተኛነት፣ በመጤ ጠሎችና ዝናን ናፋቂ በሆኑ ፖለቲከኞች፣ ከፍተኛ ጥቃት ሥር ወድቋል ሲሉ፣ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ጉዳዮች ከፍተኛ ኮሚሽነር ዘይድ ራአድ አል ሁሴን አስገንዝበዋል።
ክፍፍል የሚታይባት ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካዊ የተሃድሶ መንፈስ እንድትይዝ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕ አሳስበዋል።
ነባሮቹን የዩናይትድ ስቴትስ የኢሚግሬሽን፣ የጤና ጥበቃና ሌሎችም ፖሊሲዎችን ለመለወጥ የጎሉ እርምጃዎችን እንደሚወስዱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በመጀመሪያው የዋይት ሃውስ ወራቸው ውስጥ ተናግረዋል፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ዛሬ ምሽት ላይ ለተወካዮች ምክር ቤቱ በሚያደርጉት ንግግር ላይ ሃገሪቱ ለረዥም ጊዜ ይዛው በቆየችው ዓለምአቀፍ ግዴታዎቿና ቃሎቿ ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ እንደሚፈልጉ የሁለቱም ገዥ ፓርቲዎች አባላት የሆኑ እንደራሴዎች ተናግረዋል፡፡
በደቡብ አፍሪካ ከሁለት ዓመት በኋላ በድጋሚ ባገረሸው በመጤዎች ጥላቻ ላይ ያነጣጠረ ዝርፊያ ፕሪቶሪያ "አትረጅቪል" በተባለች መንደር ውስጥ ሙሉ የሱቅ ንብረታቸውን እንደተሰረቁ ሁለት ኢትዮጵያውያን ለአሜሪካ ድምጽ ተናገሩ። በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ሱቃችን ሲዘረፍ ይሄ ሁለተኛ ጊዜያቸው እንደሆነ የተናገሩት ነጋዴዎች “ሱቆቹን ያሟላነው ተበድረን ነበር። ዕዳውን ሳንከፍል ከነቤተሰቦቻችን ቧዶ እጃችንን ቀረን ብለዋል።”
በመጭዎቹ ስድስት ወራት ውስጥ “ከሃያ ሚሊዮን በላይ ቁጥር ያለው ሰው አፍሪካ ውስጥ ለበረታ ረሃብ ወይም ቸነፈር ይጋለጣል፤” - የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዥ ናቸው ይህንን ክፉ ዜና ሰሞኑን ይፋ ያደረጉት፡፡
የመሠረታዊ ሰብዓዊ መብቶች ከበሬታ የተመረኮዘው የዓለም ሠላምና መረጋጋት “ደንታ ቢስ የፖለቲካ ጥቅም አግበስባሶች” በሚባሉት አደጋ ተደቅኖባቸዋል ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ዜይድ ራዓድ አል ሁሴን አስጠነቀቁ።
በ1ሺኽ 5 መቶ የዓለም ሻምፒዮኗ ገንዘቤ ዲባባ በዓለም አቀፉ የ ቪልላ ድ ማድሪድ አንድ ሺኽ ሜትር ሩጫ ውድድር የግልዋን ፈጣን ጊዜ አስመዝግባ አሸነፈች።
ከሊብያ ወደ ጣልያን በሚወስደው የሜዲቴራኔያን ባሕር መሥመር ላይ የሚሞቱ ፍልሰተኞች ቁጥር ማሻቀቡን የሚያሳዩ ሪፖርቶች እየደረሱት መሆኑን ዓለምአቀፉ የፍልሰት ድርጅት - አይኦኤም አስታወቀ፡፡
ከሩሲያ ጋር አብረው ሊሠሩ የሚችሉባቸውን አካባቢዎች መፈለግ፤ በኢራንና በቻይና ላይ ኾምጠጥ ያለ አቋም በመያዝ ለእሥራኤል መሪ ለቤንጃንሚን ኔታንያሁ ጠንካራ ድጋፍ በመሥጠት በሃገራቸው የውጭ ፖሊሲ ላይ ለውጦችን እንደሚያመጡ ዶናልድ ትራምፕ በምርጫ ዘመቻቸው ወቅት ቃል ሲገቡ ነበር፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በዚህ ሣምንት ውስጥ የተከለሰ የጉዞ ዕገዳ ትዕዛዝ ያወጣሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡
ተጨማሪ ይጫኑ