ነባሮቹን የዩናይትድ ስቴትስ የኢሚግሬሽን፣ የጤና ጥበቃና ሌሎችም ፖሊሲዎችን ለመለወጥ የጎሉ እርምጃዎችን እንደሚወስዱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በመጀመሪያው የዋይት ሃውስ ወራቸው ውስጥ ተናግረዋል፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ዛሬ ምሽት ላይ ለተወካዮች ምክር ቤቱ በሚያደርጉት ንግግር ላይ ሃገሪቱ ለረዥም ጊዜ ይዛው በቆየችው ዓለምአቀፍ ግዴታዎቿና ቃሎቿ ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ እንደሚፈልጉ የሁለቱም ገዥ ፓርቲዎች አባላት የሆኑ እንደራሴዎች ተናግረዋል፡፡
በደቡብ አፍሪካ ከሁለት ዓመት በኋላ በድጋሚ ባገረሸው በመጤዎች ጥላቻ ላይ ያነጣጠረ ዝርፊያ ፕሪቶሪያ "አትረጅቪል" በተባለች መንደር ውስጥ ሙሉ የሱቅ ንብረታቸውን እንደተሰረቁ ሁለት ኢትዮጵያውያን ለአሜሪካ ድምጽ ተናገሩ። በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ሱቃችን ሲዘረፍ ይሄ ሁለተኛ ጊዜያቸው እንደሆነ የተናገሩት ነጋዴዎች “ሱቆቹን ያሟላነው ተበድረን ነበር። ዕዳውን ሳንከፍል ከነቤተሰቦቻችን ቧዶ እጃችንን ቀረን ብለዋል።”
በመጭዎቹ ስድስት ወራት ውስጥ “ከሃያ ሚሊዮን በላይ ቁጥር ያለው ሰው አፍሪካ ውስጥ ለበረታ ረሃብ ወይም ቸነፈር ይጋለጣል፤” - የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዥ ናቸው ይህንን ክፉ ዜና ሰሞኑን ይፋ ያደረጉት፡፡
የመሠረታዊ ሰብዓዊ መብቶች ከበሬታ የተመረኮዘው የዓለም ሠላምና መረጋጋት “ደንታ ቢስ የፖለቲካ ጥቅም አግበስባሶች” በሚባሉት አደጋ ተደቅኖባቸዋል ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ዜይድ ራዓድ አል ሁሴን አስጠነቀቁ።
በ1ሺኽ 5 መቶ የዓለም ሻምፒዮኗ ገንዘቤ ዲባባ በዓለም አቀፉ የ ቪልላ ድ ማድሪድ አንድ ሺኽ ሜትር ሩጫ ውድድር የግልዋን ፈጣን ጊዜ አስመዝግባ አሸነፈች።
ከሊብያ ወደ ጣልያን በሚወስደው የሜዲቴራኔያን ባሕር መሥመር ላይ የሚሞቱ ፍልሰተኞች ቁጥር ማሻቀቡን የሚያሳዩ ሪፖርቶች እየደረሱት መሆኑን ዓለምአቀፉ የፍልሰት ድርጅት - አይኦኤም አስታወቀ፡፡
ከሩሲያ ጋር አብረው ሊሠሩ የሚችሉባቸውን አካባቢዎች መፈለግ፤ በኢራንና በቻይና ላይ ኾምጠጥ ያለ አቋም በመያዝ ለእሥራኤል መሪ ለቤንጃንሚን ኔታንያሁ ጠንካራ ድጋፍ በመሥጠት በሃገራቸው የውጭ ፖሊሲ ላይ ለውጦችን እንደሚያመጡ ዶናልድ ትራምፕ በምርጫ ዘመቻቸው ወቅት ቃል ሲገቡ ነበር፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በዚህ ሣምንት ውስጥ የተከለሰ የጉዞ ዕገዳ ትዕዛዝ ያወጣሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡
“በሰላምም ይሁን በአመፅ - ነፃነት በአስፈላጊው መንገድ ሁሉ!” ይል ነበር ማልኮም ኤክስ በየንግግሩ አዝማች፤ እንደልማድም ሆኖበት፤ ደግሞም የነፃነትን አስፈላጊነት ለማፅናት፡፡
ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ታዋቂው የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት በተለይ በኢኮኖሚ ታሪክ ዘርፍ ፈር ቀዳጅ ሥራ መስራታቸውን አንጋፋ ኢትዮጵያዊ ሙሑር ተናግረዋል፡፡
“የሕጉን መሠረት ሲጥሉ ይሄው እስካሁን ድረስ ከሞላ ጎደል በዚያ ማዕቀፍ ሥር ነው ይሄ ማኅበረሰብ የሚንቀሳቀሰው። ምን ድነው መርሳት የሌለብን ያችኛዋ አሜሪካ በ1789 ሕገ መንግስት የተወለደችውን። ይሄ ኅገ-መንግስት ሲቀረጽ በጊዜው ለማን ነው የተቀረጸው? የሚለውን ነው።” ዶ/ር ብሩክ ኃይሉ የፖለቲካ ሳይንስ መምሕር
"ጆን ብራውን በጣም የተበሳጨ አሜሪካዊ ነው፡፡ ባርነት የማስወገጃው ብቸኛ መንገድ ተቋሙን በአምፅ ማሰወገድ ነው ብሎ ያምን ነበር፡፡ በጦርነት መደምሰስ" የሀርፐርስ መሪ ብሔራዊ ፓርክ ዋና የታሪክ ተመራማሪው ዴኒስ ፍራይ የባርነት መሪና ተቃዋሚው ጆን ብራውንና ጓዶቹ ያንን የአሜሪካ የፅልመት ዕድሜ ለማብቃት የጀመሩትን ትግል ያስታውሳሉ፡፡
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቅርብ ተባባሪዎቻቸውና የምርጫው ጊዜ አማካሪዎቻቸው ከሩስያ ቅርብ ግንኙነት ነበራቸው የሚለውን ወሬ አልተቀበሉም።
"ይህ ሁኔታ ሲከሰት ወቅት የውሃውን መጠን ማጉደል የሚያስችል እርምጃ ወሰድን። በዚያም ጎርፉ በሚያደርሰው መሸርሸር ሳቢያ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ ችለናል።” ቤል ክሮይል የካሊፎርኒያ ክፍለ ግዛት የውሃ ሃብት መምሪያ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ናቸው።
ለክብረ በዓሉ በመላ ሃገሪቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች አደባባይ መውጣታቸው ተዘግቧል።
በአመዛኙ ሙስሊም ከሆኑ ሰባት ሀገሮች ፍልሰተኞችና ስደተኞች ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዳይገቡ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጥለውት የነበረውን የማስፈፀሚያ ትዕዛዝ ያስቆመው የሴአትል ዳኛ ውሣኔ በይግባኝ ሰሚ ችሎት ፀና፡፡
እንግሊዝ ከአውሮፓ ኅብረት የምትወጣበትን ሂደት የፊታችን መጋቢት አጋማሽ አካባቢ ልትጀምር ታቅዷል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስደተኞችን አስመልክቶ የሰጡት አከራካሪ ትዕዛዝ መጻዒ ዕድል በአሁኑ ወቅት በዩናይትድ ስቴትስ የፌዴራሉ ፍርድ ቤት እጅ ውስጥ ይገኛል። በመጨረሻ ግን ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሊያመራ እንደሚችል ይገመታል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በጦርነት በተበጠበጠችው የመን ውስጥ ለሚኖሩ 12 ሚሊዮን ሕዝብ ነፍስ አድን የሚሆን የ2.1 ቢሊዮን ዶላር እርዳታ ጠየቀ።
የዩናይትድ ስቴትስ የጉዞ ዕገዳ ሕግ፣ ኬንያ ውስጥ ውዥንብር ፈጥሯል።
ከሊቢያ ተነስተው በሜዲተራኒያን ባህር አቋረጠው ወደ ጣሊያን ለመግባት በጉዞ ላይ የነበሩና ባጋጠማቸው አደጋ የድረሱልኝ ጥሪ ያሰሙ 1500 ስደተኞች በጣሊያን የባህር ላይ ጠባቂዎች አማካኝነት ሕይወታቸው ተርፏል።
እስራኤል በኃይል በያዘቻቸው ግዛት ውስጥ መቶ ቤቶችን ለመገንባት አዲስ ሕግ ማውጣትም ፊሊስጤማውያን ባለሥልጣኖችን አስቆጥቷል፡፡
ዛሬ ጥር 29 በሴት የመራቢያ እና የፆታ አካላት ላይ የሚፈፀም ማንኛውም ጉዳት ይህም ማለት ግርዛት፣ መተልተል፣ መስፋት የመሳሰሉ ኢ - ሰብዓዊ አድራጎቶችን የመቃረኛ፣ የማውገዣ፣ ዓለም አቀፍ ቀን ነው፡፡
በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በምክር ቤት አባሎች መካከል አንድ አዲስ ትንቅንቅ ተጀምሯል፡፡
ተጨማሪ ይጫኑ