የእሥያን የንግድ አቅጣጫ አስመልክቶ የዩናይትድ ስቴትስና የቻይና ፕሬዚዳንቶች ለአካባቢው የንግድ መሪዎች ባደረጓቸው ንግግሮች ውስጥ ጨርሶ የሚጣረሱ አመለካከቶችን አንፀባርቀዋል።
የፈረንሣይዋ ከተማ ቱሉዝ አቅራቢያ አንድ ሰው ያሽከረክራት የነበረችን መኪና ሆን ብሎ ተማሪዎች ላይ ነድቶ በሦስት ቻይናዊያን ተማሪዎች ላይ ጉዳት ማድረሱን የሃገሪቱ ፖሊስ አስታወቀ።
የዩናይትድ ስቴትስ ኃይሎች ትንናት ሐሙስ ሶማልያ ውስጥ በሚገኘው አልሻባብ ላይ የአየር ጥቃት አካሂደው፣ በርካታ አማፅያን መገደላቸውን፣ የዩናይትድ ስቴትስ ጦር አስታወቀ።
የሊባኖሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳድ አል ሃሪሪ ሥልጣን የለቀቁት ያለ ፍላጎታቸው መሆኑን የሚያሳይ ምንም ምልክት የለም ሲሉ የየዩናይትድ ስቴትስ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን ዛሬ አርብ አስታወቁ።
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሩስያው መሪ ቭላዲሚር ፑቲን፣ ቪየትናም ውስጥ በሚካሄደው የእስያ ፓሲፊክ ሀገሮች የኢኮኖሚ ጉባዔ ወቅት የጎንዮሽ ንግግር ያደርጉ ይሆናል የተባለውን ግምት ዋይት ሃውስ “የለም” አለ።
የተመድ ጠቅላላ ጉባዔና የፀጥታው ጥበቃ ምክር ቤት ትናንት ሐሙስ፣ ለዓለማቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት አራት ዳኞችን መረጠ።
የሩቅ ምሥራቅ እስያን አካባቢ ነፍሰ ገዳይ ካሉት የሰሜን ኮሪያ አገዛዝ ዩናይትድ ስቴትስና ቻይና ተባብረው ነፃ እንዲያወጡ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ቤጂንግ ላይ ጥሪ አስተላልፈዋል።
በመካከለኛው ምዕራብ ዩናይትድ ስቴትሷ የሜነሶታ ክፍለ ግዛት የሚኒያፖሊስ ከተማ እአአ 2013 በምክር ቤት አባልነት በመመረጥ የመጀመሪያው ሶማሊያዊ-አሜሪካዊ አብዲ ዋርሳሜ ተፎካካሪያቸውን ሞሃመድ ኑርን ሃምሳ ለአርባ ሰባት በመቶ በሆነ ጠባብ ልዩነት በማሸነፍ ነው በድጋሚ የተመረጡት።
ፓኪስታን ውስጥ የሚገኘው የታሊባን ጦር ሠፈር፣ አፍጋኒስታን ውስጥ ሠላምና መረጋጋት ለማስፈን ለተያዘው ጥረት ደንቃራ ነው ሲሉ፣ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን ድርጅት ኔቶ ዋና ፀኃፊ ጄንስ ስቶልንበርግ አስታወቁ።
ዩናይትድ ስቴትስ ቴክሳስ ክፍለ ሃገር አንድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተኩስ ከፍቶ ሃይ ሥድስት ሰው ገድሎ ሌሎች ከሃያ በላይ ያቆሰለው የሃይ ስድስት ዓመት ዕድሜው ዴቪን ኪሊ ጥቃቱን ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳው የቴክሳስ ባልሥልጣናት ክትትል ይዘዋል።
“በደርግ አባልነቴ ሰለባ ለሆኑት ሰዎች፥ በእነርሱም አማካኝነት ለመላው ኢትዮጵያውያን ተንበርክኬ ይቅርታ እጠይቃለሁ።” አቶ እሸቱ ዓለሙ። “አቶ እሸቱ፥ ዛሬም ‘ይህን በደል ፈጽሜያለሁ’ ሲሉ ወንጀሉን አላመኑም። በጸጸትም የተዋጡ ሰው አይደሉም።” አቶ ዓለሙ ጥሩነህ በጊዜው በእስር ቤት እንግልት ከደረሰባቸውና ከሞት የተረፉ ከዛሬው ሰባት ምሥክሮች አንዱ።
“የያዛችሁት የተሳሳተ ሰው ነው። “የእኔ ድርሻ የፕሮፖጋንዳ ሥራ ብቻ ነበር።” አቶ እሸቱ ዓለሙ። “ወንድሜና ሌሎች በጊዜው ታስረው የነበሩት ወጣቶች እንዲገደሉ ትዕዛዝ የሰጡት አቶ እሸቱ ስለመሆናቸው በፊርማቸው ያዘዙበትን ጨምሮ ብዙ ማስረጃ ተገኝቷል።” አቶ አብረሃም ብዙነህ ከከሳሽ አቃቤ ሕግ ምሥክሮች አንዱ።
ዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ኒው ዮርክ ከተማ ውስጥ በተከራየው የዕቃ መጫኛ መኪና ሥምንት ሰዎችን ሆን ብሎ ገጭቶ በመግደል የተወነጀለው የኡዝቤክሳታኑ ተወላጅ በሞት መቀጣት አለበት በሚለው አቋማቸው ፀንተዋል።
የሚያንማር መሪ ኡን ሳን ሱ ቺ ወደ ታወከው የሃገሪቱ ሰሜናዊ ክፍለ ሃገር ራኺኔ ተጉዘዋል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዛሬ ጧት በትዊተር መልዕክታቸው፣ ትናንት ማክሰኞ በኒው ዮርኩ ማንሃተን ሥምንት ሰዎችን በመኪና ገጭቶ የገደለው የኡዝቤክ አጥቂ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ የገባው በዲቪ/በግሪን ካርድ/ ነው ሲሉ አስታወቁ።
አውስትራልያ ውስጥ በሚገኝ አንድ የስደተኞች ማቆያ እስር ቤት ውስጥ የሰፈሩ ከ600 በላይ ጥገኝነት ጠያቂዎች፣ የአካባቢው ኗሪዎች ያስነሱብናል የሚሉትን አመፅ በመፍራት ከካምፑ ውስጥ አንወጣም ማለታቸው ተገለፀ።
አፍጋኒስታን ዋና ከተማ ካቡል ውስጥ በሚገኙ የዲፕሎማቲክ መኖሪያ አካባቢዎች የደረሰ የአጥፍቶ ጠፊ ፍንዳታ ስምንት ሰዎች ገድሎ ሌሎች አያሌ ማቁሰሉን፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባለሥልጣናት አስታወቁ።
ሰሜናዊ ኩርዲስታን ውስጥ ሰላም እንዲሰፍን እና የሕግ የበላይነት እንዲከበር የኢራቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይደር አል አባዲ ተማፀኑ።
ዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ የሳህል አካባቢ ሀገሮች ለሚያካሂዱዋቸው ፀረ ሽብርተኛ ጥረቶች መርጃ 60ሚሊዮን ዶላር ልትለግስ ቃል ገባች።
በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት ላይ ያለውን የካርቦን ልቀት መጠንና የኃይል አጠቃቀም የተመለከተ አውደ ጥናት ዛሬ በአዲስ አበባ ተጀምሯል፡፡
የኢራቅ ኃይል የኢራቅ ወታደራዊ ኃይል “እስላማዊ መንግሥት ነኝ” በሚለው ፅንፈኛ እስላማዊ ቡድን ቁጥጥር ሥር ያሉትን የመጨረሻ ቦታዎችን ለማስለቀቅ ጥቃት ከፍቷል።
በሃያ አንደኛው ምዕተ ዓመት እውነት ይሄ ይሆናል? ሊያሰኝ ይችላል። በዓለም ዙሪያ በሚያስገርም ቁጥር ሰው እንደጉድ ይሸጣል፣ ይገዛል፡፡
የካታላን ክልል ፕሬዚዳንት ካርለስ ፒዩጅሞንት የምክር ቤት አባላት የካታሎኒይ የራስ አስተዳደር ቦታን ለመቀልበስ በሰነዘሩት ዛቻ የሚገፉ ከሆነ የስፔን መንግሥት የካታሎኒያ ክልል ለነፃነት ከሚያካሄደው ዘመቻ ጋር የተያያዘውን የፖለቲካ ቀውስ ያባብሳል ብለዋል።
የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲ ለቋሚ የፖሊት ቢሮ ኮሚቴ የአዲስ አመራር ዝርዝር ይፍ አድርጓል። ፖሊት ቢሮ በዓለም ሁለተኛዋ ትልቅ ኢኮኖሚ በሆነችው ሀገር የበላይ አመራር ነው።
የፊሊፒንስ መከላከያ ሚኒስትር ደለፊን ሎረንዛና ማራዊ በተባለችው ደቡባዊት ከተማ በአማፅያን ላይ ሲካሄድ የቆየው የአምስት ወራት ውጊያ አብቅቷል ሲሉ ዛሬ ተናግረዋል።
ተጨማሪ ይጫኑ