የዩናይትድ ስቴትስ አርባ አምስተኛው ፕሬዚዳንት ለመሆን የፊታችን ዓርብ ቃለ-መሃላ በሚፈፅሙት ተመራጭ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ላይ የተቃውሞ ሣምንት ተጀምሯል።
በተጠናቀቀው የአውሮፓ 2016 ዓ.ም ለዓለም የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ከፍተኛውን አደጋ የደቀነው “እያንሠራራ የመጣው ርካሽ የሚባል የሕዝብ ተቀባይነትን የማግኘት አዝማሚያ ነው” ሲል ሂዩማን ራይትስ ዋች የሚባለው የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ቡድን አስታወቀ፡፡
የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ የስንብት ንግግርና የፕሮፌሰር ብሩክ ኃይሉ ትንታኔ
ከኬንያ የስደተኞች ካምፕ ተነስቶ የዩናይትድ ስቴትስ የሚኔሶታ ክፍለ ሃገር ምክር ቤት አባልነት መብቃት ዕውነት መንገዱን ሲያስቡት ዕውን የሚሆን አይመስልም።
ሳምንታዊ የስፖርት ዝግጅት
በዩናይትድ ስቴትስ 43ኛ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ዋከር ቡሽ የተጀመረው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት የኤድስ አጣዳፊ ድጋፍ መርኃ ግብር(ፔፕፍር) ዓለመቅፉን ወረርሽኝ ለመቆጣጠር ግዙፍ የተባለለት አስተዋፅዖ አበርክቷል፡፡
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ላለፉት አጭር ዓመታት በዋና ፀሐፊነት ያገለገሉት ባን ኪ ሙን ዛሬ ታኅሣሥ 21/2009 ዓ.ም ተሰናብተዋል፡፡
የኦባማ አስተዳደር ወደ ፍፃሜው እየተቃረበ በመጣ መጠን የዋሺንግተንና የመስኮብ ግንኙነት ከድጡ ወደ ማጡ እየተንሸራተተ ይበልጥ እየሻከረ ሲሄድ እያየን ነው፡፡
ዓለምችን በ2016 ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ለረዥም ጊዜ ተፋጠው ከቆዩት አምባገነን መሪ አንስቶ በሽምግልና ዕድሜያቸው ሕዋ ላይ በመቆየት እስከሚታወቁት ጠፈርተኛ እንዲሁም በስፖርቱ ዓለም ገናና ስም ያፈሩ ሰዎችን አጥታለች።
የተሰናባቹ የኦባማ አስተዳደር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ አብዝተው የሚያሳስቧቸው የእሥራኤል ፍልስጥኤም ግጭት በዘላቂነት የሚቆምበት ጉዳይና የእሥራኤል ጥቅምና ደኅንነትም የሚጠበቅባቸው መላዎች መሆናቸውን እየተናገሩ ነው፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ከፍተኛ አደጋ ላይ ወድቋል ያሉትን የእስራኤልና ፍልስጥኤም የሁለት መንግሥታት ምስረታ መፍትሄ አስመልክተው ዛሬ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ቁርሾ እየተዘጋ ይመስላል፡፡ ያኔ በተቃራኒ ጎራ ተሰልፈው የተናነቁት የዩናይትድ ስቴትስና ጃፓን ዛሬ ወዳጆች ናቸው፡፡ የእርቅን ጉዳይ ግን ሁለቱም ዝም ዝም ከማለት በስተቀር ጨርሶ አልዘነጉትም ነበር፡፡
የሩሲያ ባለሥልጣናት በሳምንቱ ማብቂያ ወደ ሦሪያ ሲበር ተከስክሶ ዘጠና ሁለት ተሣፋሪዎቹ ባለቁበት ወታደራዊ አውሮፕላን አደጋ ምክንያት ዛሬ ሰኞን ብሔራዊ የሃዘን ቀን እንዲሆን አውጀዋል።
የተመራጩ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፕሬዚዳንታዊ ድል ፖለቲካውን ቀየረው፡፡
እሥላማዊ መንግሥት ነኝ የሚለው የሽብርና የሁከት ቡድን ሁለት ቱርካዊያን ወታደሮችን ከነሕይወታቸው አቃጥሎ ሲገድል የሚያሣይ የቪድዮ ምሥል ትናንት አውጥቷል፡፡
እሥራኤል በኃይል በያዘችው የፍልስጥዔም ክልል ውስጥ የምታካሂዳቸውን የግንባታ ሥራዎች እንድታቆም በሚጠይቀው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት የውሣኔ ሃሣብ ላይ ዩናይትድ ስቴትስ ድምፅ ሳትሰጥ ቀርታለች፡፡
ዌስት ባንክ ውስጥ በምትገኘው ቤተልሄም ወንድና ሴት ስካውቶች ማንጀር አደባባይ ላይ ባደረጉት የበዐል ሠልፍ ገናን አብሥረዋል፡፡
በአትሌቲክሱ የረዥም ርቀት ሩጫ ውድድሮች ኢትዮጵያን በበርካታ ዓለምቀፍ መድረኮች በበላይነት ያስጠራው ዝነኛው አትሌት ምሩፅ ይፍጠር በ72 ዓመት ዕድሜው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡
“በደማችን ውስጥ የሚገኝ የስኳር መጠን .. አመጋገባችን፥ የሰውነታችን ክብደት መጨመር እና የአካል እንቅስቃሴ መኖር ወይም ያለመኖር፤ ያኔ ‘የስኳር ሕመም ያዘኝ’ የሚባለው አባባል ይመጣል።” ዶ/ር ኤልያስ ሰይድ ሲራጅ የሥኳር ሕሙማን ክትትል ባለ ሞያ።
ቲቢ በድፍን ዓለም በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ በሽታዎች መካከል የመሆኑ ነገር እንደቀጠለ ነው፡፡ ባለፈው የአውሮፓ ዓመትም በቲቢ ምክንያት ሁለት ሚሊየን ሰው አልቋል፡፡
ለለውጥ የተገባውን ቃል ተግባራዊ ማድረግ የኢትዮጵያ መንግሥት ብቻ ሃላፊነት እንደሆነ በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት የዴሞክራሲ የሠብዓዊ መብቶችና የሥራ ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሊኖውስኪ አሳሰቡ፡፡
በቱርክ የሩሲያ አምባሣደር የነበሩትን አንድሬ ካርሎቭን የገደለው ሲቪል የለበሰና ተረኛ ያልነበረ የፖሊስ አባል “አሌፖን አትርሱ! ሶርያን አትርሱ! የእኛ ሃገሮች ደኅና እስካልሆኑ እናንተም ደኅና አትሆኑም!” እያለ ይጮኽ እንደነበረ እማኞች ለቪኦኤ ተናግረዋል፡፡
ዘጠና ዘጠኝ ዓመቷ ነው “ተብሎ ይታመናል፤ ነገር ግን ከዚያም ሊበልጥ ይችላል” - የዣ ዣ ጋቦርን ዜና ዕረፍት ከሚናገሩት ዘገባዎች በአንዱ ነው እንዲህ የተባለው፡፡
1870 ሜጋ ዋት ኃይል የሚያመነጨው ጊቤ ሦስት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ዛሬ ተመረቀ።
በያዝነው ታህሣስ ወር የሚያበቃው 2016 ዓ.ም. “ለአፍሪካ ጋዜጠኞች፤ የጨለመ ዓመት ነው” ለጋዜጠኞች መብት የሚሟገተው ቡድን ሲፒጄ እንደሚለው፡፡
ተጨማሪ ይጫኑ