የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር መስራች ኮ/ል ታደሰ ሙሉነህ ስርዓተ ቀብር፣ ዛሬ በትውልድ ቦታቸው መርሃዊ ከተማ ተፈፀመ፡፡
በድሬዳዋ ከሳምንት በፊት ተቀስቅሶ በነበረው ተቃውሞ ሁከትና ረብሻ አስነስተዋል፣ ከተባሉት መካከል 155ቱ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፤
የአስተዳደር ወሰንና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን እንደዚሁም የዕርቀ ሰላም ኮሚሽንን በማቋቋም እና የአባለቱን ሹመት በማፅደቅ ሂደት በፓርላማው የታየው ድጋፍና ተቀውሞ የዛሬውን የኢህአዴግ ውስጣዊ ሁኔታ በግልፅ ያሳየ ነው ይላል ቀጣዩ ዘገባ፡፡
የቡርጂ ወረዳ መንግሥት ሰራተኞች ሥራ የማቆም አዱማ ከመቱ ሁለተኛ ሳምንት ይዟል፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን ጠቅላላ ጉባዔ፣ የግንባሩን ሊቀ መንበርና 7 የሥራ አስፈፃሚ አባላትን በመምረጥ አጠናቀቀ።
የቤኒሻንጉል ክልል ሰላም ግንባታና ፀጥታ ቢሮ 203 ፀረ ሰላም ኃይሎች ያላቸውን ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ገለፀ፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ በአካሄደው ስብሰባ በጠ/ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ የቀረቡትን የአስተዳደር ወሰንና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን፣ እንደዚሁም የዕርቅ ሰላም ኮሚሽን አባላት ሹመት አፅድቋል፡፡
በድሬዳዋ የሐይማኖት በዓል አከባበር ላይ የተፈፀመ ጥቃትን ተከትሎ የተነሳው ተቃውሞ ላይ ተሳትፋችኋል በመባል የተያዙ 27 ተጠርጣሪዎች ላይ የአስተዳደሩ የመጀመሪያ ፍርድቤት ፈቅዶት የነበረውን ዋስትና የይግባኝ ሰሚ ፍርድቤቱ ውድቅ አድርጎታል፡፡
የፌደራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት በዐቃቤ ሕግና በአቶ ኢሣያስ ዳኛው መካከል ባለው ክርክር፣ የዕግድ ትዕዛዙን አነሳ፡፡
ሰሜናዊ አፍጋኒስታን ውስጥ በተካሄደ የተለያየ ውጊያ ታሊባን እስከ አርባ ያህል የመንግሥት ወታደሮችን መግደሉ ተገለፀ።
ሕገ መንግሥቱን ጨምሮ የተለያዩ ህጎች እንዴት መሻሻል እንዳለባቸው የሚቀርቡ የመፍትሄ ሃሳቦች እንዲበረታቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ ታገሰ ጫፎ አሳስበዋል።
ከቤኒሻንጉል ጉምዝ በሎ ጃገንፎይና ሶጌ ወረዳዎች ተፈናቅለው በነቀምቴ ከተማ ሠፍረው የሚገኙ ቪኦኤ ያነጋገራቸው አንዳንድ ተፈናቃዮች - መንግሥት ዘላቂ መፍትሄ ይስጠን እያሉ ነው።
"ለኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት ያላትን የተፈጥሮ ሃብት አስተባብሮ መምራት የሚችል መንግሥት ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ
የተባበሩት መንግሥታት የወንጀልና የሱስ አምጭ ዕፆች መከላከያ ጽ/ቤት በኤርትራ ጉባዔ እካሄደ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ዛሬ ፓርላማ ቀርበው የሰጡት ማብራሪያ ላይ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋ ግምገማቸውን ለቪኦኤ አካፍለዋል።
ወንጀለኛ በይፋ ሲንቀሳቀስ እያየ ለሕግ ያላቀረበ ግለሰብም ሆነ ቡድን በህግ እንደሚጠየቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ አስታውቀዋል።
ከጂግጂጋ ወደሃረርና አዲስ አበባ የሚወስደው መንገድ ባቢሌ ላይ ተዘጋ፡፡
በቴፒ ከተማ በዛሬው ዕለት ዳግም በተቀሰቀሰ ግጭት 10 ሰዎች መገደላቸውን የከተማው ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ በሌላ በኩል አምስት ሰዎች መገደላቸውንና ቁጥራቸው ያልታወቁ በርካታ ሲቪሎች መቁሰላቸውን የከተማው ፍትህና ፀጥታ አስተዳደር አመልክቷል፡፡
ስለ ለውጥ መናገር ለውጥን መጀመር መለወጥ አይደለም ሲሉ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር አስገነዘቡ፡፡
በደቡብ ወሎ ዞን ወረኢሉ ወረዳ ስር የሚገኙት የካቤና ለጎጎራ አካባቢ ኗሪዎች የካቤ የቀድሞ ወረዳነት ተመልሶልን ራሳችንን ማስተዳደር አለብን የሚል ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ጥያቄውን ተከትሎ የወረኢሉ ወረዳነት ሊታጠፍ ይችላል የሚል ጭምጭምታ በመሰራጨቱ በወረዳው ውጥረት ነግሶ ቆይቷል፡፡
የኢትዮጵያ አቃብያነ ህግ በቀድሞው በሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንትና በ46 ሌሎች ሰዎች ላይ ባለፈው ዓመት በክልሉ ዘር ተኮር ግጭት ቀስቅሰዋል የሚል ክስ ትናንት መስርትዋል ሲል ሮይተርስ የዜና አገልግሎት ዘግቧል።
ባሳለፍነዉ ሳምንት መጨረሻ በምዕራብ እንዲሁም ምሥራቅ ጉጂ በኢትዮጵያ መከላከያ ኃይልና በኦሮሞ ነጻነት ግንባር ታጣቂዎች መካከል በታካሄደ ግጭት የሰው ህይወት ማለፉን በርካቶች ከቤታቸው መፈናቀላቸው ተናግረዋል።
የአገር ሸማግሌዎች ፣ የሀይማኖት አባቶችና ወጣቶች የተገኙበት የሰላም ኮንፈረንስ በይርጋለም ከተማ ተካሂዷል፡፡
በኦሮሞ ነፃነት ግንባር እና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል የተዋቀረው የአባ ገዳዎች እና ሽማግሌዎች የዕርቅ ሂደት የቴክኒክ ኮሚቴ፣ የዕርቅ ሂደቱ ተስፋ ሰጪ መሆኑን እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋርም ውይይት መደረጉን ገለፀ።
በትላንትናው ዕለት ከጭናክሰን ከተማ አካባቢ ቤተክርስትያን አንግሰው ወደ ጂግጂጋ ከተማ ሲመለሱ በነበሩ ምዕመናን ላይ ጥቃት መፈፀሙንና ይሄንን ተከትሎ በተነሳው ረብሻ ሁለት ሰዎች መገደላቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ለቪኦኤ ተናገሩ፡፡
ተጨማሪ ይጫኑ