በዚህ ዓመት የሚደረገው ምርጫ ባለፉት ምርጫዎች የታዩት ጉድለቶችን የሚያርም ለማድረግ መንግሥት ቁርጠኛነት እንዳለው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት አስታወቁ።
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ምኒስትር ዐብይ አህመድ እስራኤል የሚገኙ ኤርትራውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች ወደሃገራቸው መመለስን ጉዳይ አስመልክቶ ከቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋር ያደረጉት ውይይት የለም ሲሉ የፅህፈት ቤታቸውን ምንጮች ለአሜሪካ ድምፅ ገለጡ።
ማኅበራዊ ኃላፊነታቸውን በማይወጡ ሚዲያዎች ላይ መንግሥት ዕርምጃ መውሰድ አለበት ሲሉ አንዳንድ የባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ጠየቁ።
ትናንትና ከትናንት በስቲያ በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ አጣዬ አካባቢና በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን አጎራባች ቀበሌዎች ተፈጥሮ የነበረው ውጥረት እየተረጋጋ መምጣቱን የፀጥታ ኃይሎችና ኅብረተሰቡ ገልፀዋል፡፡
ዋይት ሃውስ ቤተመንግሥት በአባይና በኅዳሴ ግድብ ላይ ማምሻውን መግለጫ አውጥቷል።
"በመንገድ ግንባታ ምክንያት የምንኖርበትን የመንግስት ቤት ቶሎ እንድናፈርስ መወሰኑ ቅሬታ አሳድሮብናል" ሲሉ አንዳንድ የአምቦ ከተማ 03 ቀበሌ ነዋሪዎች ተናገሩ:: "ግንባታው ከ100 በላይ አባ ወራዎችን ስለሚያስነሳ ቤት አልባ ያደርገናል" ብለዋል::
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ አውጥቷል። የአሜሪካ ኤምባሲ የደህንነት ማሳሰቢያ አውጥቷል። በጎንደር ከተማና በአካባቢዋ ተከስቶ በነበረው የሰላም መደፍረስ የፀጥታው ሁኔታ ወደነበረበት መመለሱን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል። የህወሓት ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል አቶ ጌታቸው ረዳ ክሱ ምላሽ ሰጥተዋል።
በኦሮምያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ዋና ዋና የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት መፈራረማቸውን ዘግበናል፡፡
የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴ ሐሣባቸውን ለአሜሪካ ድምፅ አካፍለዋል፡፡
የአማራ ክልል ፖሊስ ኮምሽን የኢንፎርሜሽን እና ሚዲያ ልማት ዋና መምሪያ ሃላፊ ረዳት ኮምሺነር ሰይድ አህመድ ባለፈው ዓርብ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተውቋል።
በባህር ዳር ከተማ አልፎ አልፎ ምሽት ላይ የሚሰማው የተኩስ ድምፅ ምንነት ግራ እንዳጋባቸው ለቪኦኤ አስተያየታቸውን የሰጡ አንዳንድ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ።
ዴሞክራሲ በተግባር
በሐረሪ ክልል የሚገኝ የማኅበረሰብ የትምህርት ተቋም በይዞታው ውስጥ በሚፈፀም ህገወጥ የመሬት ወረራ የተነሳ የመማር ማስተማር ሥራ መጀመር አልቻልኩም አለ።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ዛሬ በተጀመረው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጉባዔ ንግግር አድርገዋል።
ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በባህርዳርና በአዲስ አበባ የተፈፀሙትን ጥቃቶች የተመለከተው ምርመራ እንደቀጠለ መሆኑን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል እንደሻው ጣሰው ለአሜሪካ ድምፅ አስታውቀዋል፡፡ ምርመራው ዘግይቷል የሚባለው ነገርም ትክክል አይደለም ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፡፡ የተወሰ ጊዜም እንደሚወስድ ይታወቅ እንደነበርም አብራርተዋል፡
የአዲስ አበባ መስተዳደር በዘንድሮ የትምህርት ዓመት ከመዋዕለ-ሕፃናት እስከ 8ኛ ክፍል ለሚገኙ በ415 ት/ቤቶች ለሚገኙ 300,000 ተማሪዎች የምገባ መርሃ-ግብር አዘጋጀቷል፡፡
የሚነሱ ቅሬታዎች ሚዛናዊነትን፥ የጋራ እሴቶቻችንንና መርኆችን በጠበቀ መንገድ መቅረብ አለባቸው ሲሉ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ መክረዋል።
ላለፍት 7 ቀናት ሲያካሂዱት የነበረውን ፀሎተ ምህላ ያጠናቀቁት በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ምዕመናን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ላይ ይፈፀማሉ ያሏቸው ጥቃቶች እንዲቆሙ ጠይቀዋል።
የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ እየደረሰ ባለው ጥቃት ዙሪያ ከቤተክርስቲያንቷ ጋር በሃዋሳ ከተማ መከሩ።
ላለፉት ሦስት ወራት በነቀምቴ ኩምሳ ሞረዳ ቤተ መንግሥት ታስረው የሚገኙ ግለሰቦች እስካሁን ፍርድ ቤት አለመቅረባቸው እንዳሳሰባቸው ከቤተሰቦቻቸው መካከል አንዳንዶቹ ለቪኦኤ ገልፀዋል::
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊና ለፍትኅ ፓርቲ/ኢዜማ/ በመላው ዓለም በሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የድጋፍ ማኅበር መቋቋም መጀርመሩን አስታወቀ፡፡
በድሬዳዋ በሦስት ቀበሌዎች የሚኖሩና በጣም ዝቅተኛ በሆነ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ከ15ሺ በላይ ነዋሪዎች ከያዝነው ወር ጀምሮ የምግብ ዋስትና ተጠቃሚ መሆን ይጀምራሉ።
ተጨማሪ ይጫኑ