እውቁ አሜሪካዊ ስቲቭ ሃርቬይ “ኪሪኩ ብራዘርስ” በሚል የቡድን መጠሪያ የሚታወቁ ሁለት ታዳጊዎችና ሁለት ወጣቶች የሰርከስ ትርዒት አቅርቦ ተመልካቹን አስደንቋል።
ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ ተሰደው የሚገኙ ተፈናቃዮች ምግብና መጠለያ በማጣት ችግር ላይ መሆናቸውን ተናገሩ። ለተፈናቃዮቹ ዕርዳታ እያደረገ ያለው የኬንያ ቀይ መስቀል በበኩሉ ማምሻውን ባወጣዉ መግለጫ ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ በመሰደድ ላይ ያሉ ሰዎች ቁጥር እያሻቀበ መሆኑን ገልፀዋል።
ቀጣዩን የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር የሚመርጠው የኢህአዴግ ምክር ቤት ስብሰባ በዛሬው ዕለት ተጀምሯል፡፡
በጉጂ ዞን ሻኪሶ ከተማ የሚገኘው ብቸኛ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ዛሬ ትምህርት መዘጋቱንና አንዳንድ ተማሪዎችም በፀጥታ ኃይሎች መደብደባቸውን የዓይን እማኞች ገለፁ፡፡ ሁኔታው የተፈጠረው ተማሪዎቹ በሞያሌ የተገደሉ ሰዎችን ለማሰብ ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት በማጣቱ ነው ብለዋል - እነዚሁ የዓይን እማኞች፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉድይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰንና የሩስያው አቻቸው ሰርጌ ላቨሮቭ በቅርቡ በኢትዮጵያ ጀምረው በየቅል ያተኩሩባቸውን የአፍሪካ ሀገሮች ጎብኝተዋል።
በባሌ ዞን በሰዌና ወረዳ ቡርቃ ጠሬ በተባለ መንደር የሚኖሩ ነዋሪዎች ላይ የሶማሌ ክልል ልዩ ፖሊስ ተኩስ ከፍቶ ከአንድ ቤት ቤተሰብ አምስት ሰዎች ተገደሉ ሲሉ ለቤተሰቡ የቅርብ ምንጮችና አንድ የወረዳ አስተዳዳሪ ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ። በተጨማሪም የልጆቹ እናትና አንድ ልጅ የመቁሰል አደጋ እንደደረሰባቸው ገልፀዋል።
ከዋልድባ ገዳም ተይዘው በእስር የሚገኙት ሁለቱ መነኮሳት ሀይማኖታዊ ልብሳቸውን ከመልበስ እንዳይከለከሉ ፍ/ቤት ትዕዛዝ ሰጠ፡፡
ከ1997 እስከ 2001 ዓ.ም በባህርዳር ዩኒቨርስቲ በፕሬዚዳንትነት ያገለገሉት ዶ/ር ፀሐይ ጀምበሩ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡
ከእስር በቅርቡ የተፈቱት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አቶ አንዷለም አራጌና ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ወልዲያ ናቸው።
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሀገር ውስጥ ለሚገኙ ለተፈናቀሉና ቤተሰቦቻቸው ለተገደሉባቸው ቤተሰቦች በዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት በኩል የሚያደርጉትን እርዳታ በተመለከተ ከሰብሳቢ አቶ ታማኝ በየነና ከትብብሩን አቅም ግንባታ ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ተሾመ ጋራ ውይይት አድርገናል።
የፓርቲውን ሊቀመንበር ብሎም የሀገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር የሚመርጠው የኢህአዴግ ምክር ቤት በመጨው ሳምንት መጀመሪያ እንደሚሰበሰብ ተገለፀ፡፡
በሀዋሳ የአዋዳ ዩኒቨርስቲ የሁለተኛ አመት ተማሪ ናት።
ጂቡቲ የኢትዮጵያ ዋንኛ የወጭና የገቢ ንግድ በር ሆና እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስታወቀ፡፡
"ለፍተሻ ሲያመጡት እጆቹን በካቴና ታስሮ ነበር” - ባለቤታቸው "አስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁ ሰዎችን ዝም ማሰኛና ትችንት ወንጀል ማድረጊያ መሳሪያ ነው”- አምነስቲ
በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት ከግንቦት ሰባት ጋራ በመተባበር የሽብር ወንጀል ክስ ቀርቦበት ጉዳዩን በመከታተል ላይ የሚገኘው አቶ አስቻለው ደሴ በድብደባ የተጎዳውን የዘር ፍሬ እንዳይታከም እክል እንደገጠመው በዛሬው ዕለት ለፍርድ ቤት ማመልከቱ ተሰማ።
ስደተኞቹን የመመዝገብ ሥራው እንዳልተጠናቀቀም አስታውቋል። "አባቴን ቀብሬ ብቻዬን ቁጭ ብያለሁ" የሚለውን አባቱ የተገደለበት ወጣትና "እቤቴ ውስጥ ቁጭ ብዬ በጥይት ተመታሁ"የሚሉ በሆስፒታል ተኝተው በመታከም ላይ የሚገኙ የአምስት ልጆች እናት አነጋግረናል።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ አሥራ ዘጠነኛ ወንጀል ችሎት በቂሊንጦ እሥረኛ ማቆያ ቃጠሎ በተጠረጠሩት በእነ ማስረሻ ሰጤ መዝገብ ብይኑን ሳያሰማ ቀረ፡፡
የኤርትራ መንግሥት በዘፈቀደ ያሠራቸውን ሁሉ በአፋጣኝ እንዲለቅቅና ፍትሐዊ ፍርድ የሚያገኙበትን ሁኔታ እንዲያረጋግጥ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ቢሮ አሳሰበ።
የባለፈው ቅዳሜ ግድያ ሸሽተው በኬንያ ሰፍረው የሚገኙ የኢትዮጵያ ስደተኞች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ የዓለምቀፉ የስደተኞች ድርጅት /ዩኤንኤችሲአር/ ተጨማሪ የሰው ኃይል ወደ ቦታው ሊልክ መሆኑን የድርጅቱ ኬንያ ቅርንጫፍ ቃል አቀባይ ዩቮን ንዴጌ ተናገሩ።
ወደ ዐሥራ ስምንት የሚሆኑ ከአማራ የፖለቲካ ድርጅቶች፣የሲቪክና የማኅበረሰብ ድርጅቶችና የመገናኛ ብዙኃን ሲልቨር ስፕሪንግ ሜሪላንድ የሦስት ቀን ጉባኤ አካሂደዋል።
ሰማያዊ ፓርቲ “ሰሞኑን ሞያሌ ውስጥ የንፁሃን ዜጎችን ሕይወት አጠፉ” ያላቸው የመከላከያ ሠራዊት አባላት በግልፅ ችሎት ፊት ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠይቋል።
የኦሮሚያ ክልል ፍትሕ ቢሮ በሞያሌ ከተማ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የተፈፀመው ግድያ በስሕተት የተፈፀመ ነው ብሎ እንደማያምን አስታወቀ።
ካለፈው ጥር እስከ መጭው ታኅሣስ ባለው የአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ቁጥራቸው ወደ ስምንት ሚሊየን የሚጠጋ ኢትዮጵያዊያን ሰብዓዊ ዕርዳታ እንደሚፈልጉ መንግሥትና አጋሮቹ አስታውቀዋል።
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ውስጥ በደረሰ የአውቶብስ አደጋ፣ 38 ሰዎች መሞታቸውን አንዳንድ ዘገባዎች አመለከቱ።
በደቡብ ኦሮሚያ በሞያሌ ከተማ ትናንት ማታ አንድ ሰው ባልታወቁ ሰዎች ተመቶ መሞቱና ሌላው ደግሞ በጥይት ተመቶ መቁሰሉ ተሰማ። ከሞያሌ ከተማ አራት ቀበሌዎች እጅግ በርካታ ነዋሪዎች መሰደዳቸው ታወቀ። እስካሁን ለማረጋጋት በተወሰደው እርምጃም በርካታ ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አንድ የኮማድ ፖስቱ ጽ/ቤት ተወካይ አስታወቁ።
ተጨማሪ ይጫኑ