በሰሜን ወሎ ዞን እስካሁን ውጥረት መንገሱን ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል። በወልዲያ፣ በቆቦ በመርሳና የንግድና የሥራ እንቅስቃሴ መቋረጡን ትምሕርት ቤት መዘጋቱን ነዋሪዎቹ ጨምረው ተናግረዋል።
ትላንት የተከፈተው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ አሁን ማማሻውን ተጠናቋል። በሙስና ላይ የሚካሄደውን ትግል በማሸናፍ ላይ እንደሚያተኩር የተገልፀው ይኸው ጉባዔ ሌሎች ውሳኔዎችም ይፋ ተደርገውበታል።
በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ ከማክሰኞ ጀምሮ በተቀሰቀሰ ተቃውሞና ግጭት የሰው ሕይወት መጥፋቱን ንብረት መውደሙ የሚታወስ ሲሆን በዛሬው ዕለት ወጣቶች ከየቤታቸው እየታሰሩ መሆኑን ነዋሪዎች ገልፀዋል። የክልሉ ፕሬዝዳንት ችግሩ የፓርቲው ነው ብለዋል። በስደት ላይ የሚገኘው ሲኖዶስ የወልዲያን ግድያ አውግዟል።
ሁለት የተመድ የረድዔት ሠራተኞች ዛሬ ባወጡት መግለጫ፣ በዚህ ሳምንት መግቢያ በየመን የባሕር ወደብ በሰጠሙት ሠላሳ ፍልሰተኞች ሞት የተሰማቸውን ኃዘን ገለጹ።
ኢህአዴግ በሚከተለው አክራሪ ኮሚኒስታዊ ቆኖና ምክንያት ለሀገሪቱ ችግሮች መፍትሄ መስጠት እንደማይቻለው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ አስታወቀ፡፡
በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት ጉዳያቸው እንደገና እየታየ የሚገኘው ሁለቱ የኢንተርኔት አምደኞች፣ ዛሬ የመከላከያ ምስክሮቻቸውን ሳያቀርቡ ቀሩ።
ንብረታቸው በመቃጠሉ ሳቢይም ከቆቦ ከተማ ሸሽተው አላማጣ መግባታቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።
በቆቦ ከተማ ለሁለት ቀናት በተደረገ ተቃውሞና ግጭት እስካሁን ሰባት ሰዎች መሞታቸውን ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ገልፀዋል። ከተቃውሞው በኋላ በርካታ ንብረቶች በቃጠሎ መውደማቸንና በአሁኑ ሰዓት ከተማው በመከላከያ ሠራዊት በቁጥጥር ስር መዋሉን ነግረውናል።
ሙስና በአፍሪካ ውስጥ እያስከተለ ያለው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ፡፡
ኢትዮጵያ በሊብያ የሚገኙ ዜጎቿን ወደ ሀገር መመለስ መጀመሯን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የኔዘርላንድስ መንግሥት የኤርትራ ኤምባሲ ጉዳይ ፈፃሚ አምባሳደር ተከስተ ገብረመድህንን ከሀገሩ እንዲወጡ ማዘዙ ተቀባይነት የሌለው አድራጎት ነው ስትል ኤርትራ ተቃውሞ አሰምታለች።
ወልድያ ውስጥ በጥምቀት በዓል ቀናት የመከላከያ ሠራዊት አባላት ናቸው በተባሉ ታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ የተገደሉ አባቶች የአድራጎቱ ተጠያቂዎች በአፋጣኝ ሕግ ፊት እንዲቀርቡላቸው ጠይቀዋል።
ተከስተ የማነ ከሰባት ዓመት በፊት ሀገሩን ኤርትራን ለቆ የሊቢያ በረሃን አቋርጦ እስራኤል የገባው በፖለቲካ ስደት ምክንያት እንደሆነ ይናገራል።
ቅዳሜ በ1/27/2018 ሜሪላንድ ሲልቨርስ ስፕሪንግ የሚከናወነው በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያት የመብት ተሟጋችነት አስተዋፅዖ ታሪክ የሚዘክረው የዶክተር ማይገነት ሽፈራው መጽሐፍ “Struggle From Afar” ይምረቃል፡፡
በዛሬው ዕለት ቁጥራቸው የበዛ የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች ለተቃውሞ ሰልፍ አደባባይ መውጣታቸው ታውቋል። የተቃውሞው ምክኒያት የመሰረተ ልማት እጦት መሆኑን የሰልፉ ተሳታፊዎችና የከተማው ነዋሪዎች ነግረውናል።
ሞያሌ ከትናንት በስቲያ አንድ የ20 ዓመት ወጣት በመከላከያ ፖሊስ መገደሉንና ሦስት ወጣቶች መቁሰላቸውን የወረዳው አስተዳዳሪ ገለጹ። ከቆሰሉት መካከል የስድስት ዓመት ልጅ እንደሚገኝበት ተናግረዋል።
የዚህ ዓመቱ የመሪዎች ጉባዔ በሙስና ላይ ማተኮሩ ትግሉ አሁን ተጀመረ ማለት እንዳልሆነ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ አስታወቁ፡፡
ወልዲያ ውስጥ የተፈጠረው የከተማዪቱን ማኅበራዊ ስብጥርና ግንኙነቶች የማያንፀባርቅ አሣዛኝ ሁኔታ መሆኑን በሰሞኑ ግርግር የንግድ ተቋማቸውና መኖሪያ ቤታቸው ሙሉ በሙሉ እንደወደሙባቸው የገለፁት የኃይላይ ሕንፃ ባለቤት አቶ ኃይላይ ንጉሤ ለቪኦኤ ገለፁ።
አዲስ አበባ የተሰባሰቡ የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገሮች አምባሳደሮች ኮሚቴ የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርብ አፍሪካ ላይ የሰነዘሩትን የሚያወግዝ ረቂቅ የአቋም መግለጫ አዘጋጅተዋል።
ወልድያ ከተማ የመንግሥት ታጣቂዎች ፈፅመውታል ያሉትን የግፍ ግድያ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ እና ሰማያዊ ፓርቲ አውግዘውታል።
ዶ/ር መረራ ጉዲና ለአውሮፓ ፓርላማ እማኝነት የሰጡበትን መድረክ ካዘጋጁትና ከጋባዦችም አንዷ የነበሩት የፓርላማው አባል አና ጎምሽ የኢትዮጵያ መንግሥት 528 እሥረኞችን በመፍታቱ የተፈጠረውን ደስታ ከተጋሩት ሰዎች አንዷ ቢሆኑም የኢትዮጵያን መንግሥት በብርቱ ኮንነዋል።
ከኢትዮጵያ ሶማሌና ከሶማሌላንድ የተለያዩ ከተሞች የተባረሩ ተፈናቃይ የኦሮሞ ተወላጆች፤ በባሌ ዞን ውስጥ የምግብ እጥረትን ጨምሮ ለተለያዩ ችግሮች መጋለጣቸውን ገለጹ። የዞኑ አስተዳዳሪ ፤ “እርዳታ እየሰጠንና የተቻለንን እያደረግን ነው ለሁሉም ግን በቂ ነው ማለት አንችልም።” ብለዋል።
የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ ጉባዔ አዲስ አበባ ላይ ተከፍቷል፡፡
በአማራ ክልል ወልድያ ከተማ ሲካሄድ በነበረው ሀይማኖታዊ ክብረ በዓል በተፈጠረ ግጭት ሰባት ሰዎች እንደተገደሉ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች እንደቆሰሉ ተገለፀ፡፡
በግጭቶቹ ቢያንስ የስድስት ሰው ሕይወት መጥፋቱን፣ የቆሰሉም እንዳሉ፣ በቁጥጥር ሥር የዋሉም እንደነበሩ የመላ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አቶ አዳነ ጥላሁን ለቪኦኤ ገልፀዋል።
ተጨማሪ ይጫኑ