ሞያሌ ከትናንት በስቲያ አንድ የ20 ዓመት ወጣት በመከላከያ ፖሊስ መገደሉንና ሦስት ወጣቶች መቁሰላቸውን የወረዳው አስተዳዳሪ ገለጹ። ከቆሰሉት መካከል የስድስት ዓመት ልጅ እንደሚገኝበት ተናግረዋል።
የዚህ ዓመቱ የመሪዎች ጉባዔ በሙስና ላይ ማተኮሩ ትግሉ አሁን ተጀመረ ማለት እንዳልሆነ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ አስታወቁ፡፡
ወልዲያ ውስጥ የተፈጠረው የከተማዪቱን ማኅበራዊ ስብጥርና ግንኙነቶች የማያንፀባርቅ አሣዛኝ ሁኔታ መሆኑን በሰሞኑ ግርግር የንግድ ተቋማቸውና መኖሪያ ቤታቸው ሙሉ በሙሉ እንደወደሙባቸው የገለፁት የኃይላይ ሕንፃ ባለቤት አቶ ኃይላይ ንጉሤ ለቪኦኤ ገለፁ።
አዲስ አበባ የተሰባሰቡ የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገሮች አምባሳደሮች ኮሚቴ የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርብ አፍሪካ ላይ የሰነዘሩትን የሚያወግዝ ረቂቅ የአቋም መግለጫ አዘጋጅተዋል።
ወልድያ ከተማ የመንግሥት ታጣቂዎች ፈፅመውታል ያሉትን የግፍ ግድያ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ እና ሰማያዊ ፓርቲ አውግዘውታል።
ዶ/ር መረራ ጉዲና ለአውሮፓ ፓርላማ እማኝነት የሰጡበትን መድረክ ካዘጋጁትና ከጋባዦችም አንዷ የነበሩት የፓርላማው አባል አና ጎምሽ የኢትዮጵያ መንግሥት 528 እሥረኞችን በመፍታቱ የተፈጠረውን ደስታ ከተጋሩት ሰዎች አንዷ ቢሆኑም የኢትዮጵያን መንግሥት በብርቱ ኮንነዋል።
ከኢትዮጵያ ሶማሌና ከሶማሌላንድ የተለያዩ ከተሞች የተባረሩ ተፈናቃይ የኦሮሞ ተወላጆች፤ በባሌ ዞን ውስጥ የምግብ እጥረትን ጨምሮ ለተለያዩ ችግሮች መጋለጣቸውን ገለጹ። የዞኑ አስተዳዳሪ ፤ “እርዳታ እየሰጠንና የተቻለንን እያደረግን ነው ለሁሉም ግን በቂ ነው ማለት አንችልም።” ብለዋል።
የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ ጉባዔ አዲስ አበባ ላይ ተከፍቷል፡፡
በአማራ ክልል ወልድያ ከተማ ሲካሄድ በነበረው ሀይማኖታዊ ክብረ በዓል በተፈጠረ ግጭት ሰባት ሰዎች እንደተገደሉ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች እንደቆሰሉ ተገለፀ፡፡
በግጭቶቹ ቢያንስ የስድስት ሰው ሕይወት መጥፋቱን፣ የቆሰሉም እንዳሉ፣ በቁጥጥር ሥር የዋሉም እንደነበሩ የመላ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አቶ አዳነ ጥላሁን ለቪኦኤ ገልፀዋል።
የኢሕአዴግን የሁለት ሣምንታት ግምገማ ተከትሎ እየተወሰዱ ባሉ እርምጃዎችና በሌሎችም አጠቃላይ ጉዳዮች ላይ የኢትዮጵያ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽንስ ጉዳዮች ኃላፊ ሚኒስትር ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ለአሜሪካ ድምፅ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስና የመላ አማራ ሕዝብ ድርጅት ዓለምአቀፍ ድጋፍ ሰጭዎች በጋራ ለመሥራት ተስማምተው የመግባቢያ ሰነድ ቅዳሜ፣ ጥር 12/2010 ዓ.ም ከዋሺንግተን ዲሲ ወጣ ብሎ በሚገኘው ማርክ ሴንተር ሂልተን ሆቴል ውስጥ ይፈራረማሉ።
"በክልሉ አምባገነንነት ሰፍኗል፣ ሥጋት ነግሷል። ወጣቶች ከዚያ ለመቆየት የሚያስችል ተሥፋ በማጣታቸው በአደጋ ለተመላ ስደት ተዳርገዋል። መልስ ያልተገኘላቸው ብዙ ጥያቄዎች አሉን።" ዑመር ዶል የድርጅቱ ሊቀመንበር ናቸው።
ኢትዮጵያን ከገባችበት ችግር ለማውጣት ኢህአዴግ ተጨማሪ ፓለቲካዊ ርምጃዎችን መውሰድ እንዳለበት ዶ/ር መረራ ጉዲና አሳሰቡ፡፡ ታሳሪዎችን ለመፍታት የተደረሰበትን ውሳኔ መነሻ አድርገው የተናገሩት ዶ/ር መረራ በዚች ሀገር ፓለቲካዊ ውሳኔ የሚያስፈልግበት ከዚህ የበለጠ አሳሳቢ ጊዜ የለም ብለዋል፡፡
ከ2ሺሕ በላይ የህወሓት ከፍተኛ አመራሮችና ከ2መቶ በላይ የአጋር ድርጅቶች ከፍተኛ አመራሮች የተሳተፉበት የህወሓት ጉባዔ ትናንት ምሽት ተጠናቀቀ፡፡
የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግሬስ/ኦፌኮ/ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ኢህአዴግ የብሔራዊ መግባባቱን ሥራ በሙሉ ልብ እንዲያከናውን እና ከተቃዋሚ ኃይሎች ጋር በመሆን ለኢትዮጵያ እንደገና አዲስ ዘመን እንዲጀመር ጥሪ አቀረቡ፡፡
ከገዥው ፓርቲና ከመንግሥት የሚጠበቀው “የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና መፈታት ሳይሆን ለሕዝብ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ነው” ሲሉ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል አቶ ጥሩነህ ገምታ ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ተናግረዋል።
በእስር ላይ የሚገኘው ታዋቂው ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ኦክስፋም ኖቪብ እና ፔን ኢንተርናሽናል በተባሉ ሁለት ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የ2018 ተሸላሚ ሆኗል።
የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለአሥራ ሰባት ቀናት ያህል ተሰብስቦ ስህተቶቹንና ድክመቶቹን ገምግሞ፣ በችግሮቹ መንስዔ ላይ መክሮ የሃሳብ አንድነትና መተማመን ፈጥሯል የሚል መግላጫ ማውጣቱ ይታወቃል። ሊወስዳቸው ስላቀዳቸው እርማቶችና እርምጃዎችም ዘርዝሯል።
የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግሬስ /ኦፌኮ/ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና የተመሰረተባቸው ክስ ተቋርጦ ዛሬ መፈታታቸው ታወቀ፡፡ አያሌ ደጋፊዎቻቸው እና የኦፌኮ አባላት በቤታቸው አካባቢ በአጀብ ተቀብለዋቸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ለይፋ የሥራ ጉብኝት ዛሬ ግብፅ ካይሮ ገብተዋል፡፡
ኢራፓን ጨምሮ አሥራ ሥድስት ሀገርቀፍ ፓርቲዎች ከገዢው ኢህአዴግ ጋር እያካሄዱ ባሉት ድርድር እስካሁን የተገኘ ውጤት አለ? ወይስ በራሱ በድርድሩ ሳቢያ ቀውስ ውስጥ የገቡ ፓርቲዎች አሉ?
ኢህአዴግ እሥረኞችን ለመፍታትና ማዕከላዊን ለመዝጋት በወሰደው አቋም ወላዋይነትን አሳይቷል ሲሉ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት/መኢአድ/እና ሰማያዊ ፓርቲ ነቅፈዋል።
ከነገ በስተያ ከሚለቀቁት መካከል ከአንድ ዓመት በላይ እሥር ቤት የሚገኙት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ መሪ ዶ/ር መረራ ጉዲና ይገኙበታል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚታየው አለመረጋጋት ምክንያቱ ‘የሕገ መንግሥቷ አንቀፅ 39 ነው’ ሲሉ የኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ አስታውቀዋል።
ተጨማሪ ይጫኑ