ወደ ኢጣልያ የሚገቡ ስደተኞችና ፍልሰተኞች ቁጥር እየቀነሰ የመጣ ይምሰል እንጂ ከፈረንሣይ ጋር በምትዋሰነው ውቢቱ ቬንቲሚግሊያ ከተማ ያለው ሁኔታ ግን የሚያሳየው እንደዚያ ዓይነቱን እውነት አይደለም።
መንግሥት ለሰብዓዊ መብቶች መከበርና ለዲሞክራሲ መስፈን ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዲያሳይ ሰመጉ ጠየቀ፡፡
ሱዳን ከኤርትራ ጋር ያላትን ድንበር ዘግታለች።
ለ18 ቀናት ስብሰባ የተቀመጠው ገዢው ፓርቲ በመጨረሻ ቅዳሜ ዕለት ያወጣውን የጹሑፍ መግለጫ በተመለከተ የተለየያዩ አስተያየቶች እየተሰጡ ይገኛሉ። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ትምሕርት መምሕር ረዳት ፕሮፌሰር አቶ አበባው አያሌው ከአዲስ አበባ፣ አቶ አሉላ ሰለሞን ከዋሽንግተን ዲሲና አቶ ገረሱ ቱፋ ከአምስተርዳም በመግለጫው ላይ ተወያተዋል።
የሰብዓዊ መብት ተከራካሪው አቶ ያሬድ ኃይለማርያምና የዞን ዘጠኝ የኢንተርኔት ጸሐፊው በፍቃዱ ኃይሉ በየትኛውም ቋንቋ ቢገለፅ ኢትዮጵያ ውስጥ ቁጥራቸው እንኳን በግልፅ የማይታወቅ የፖለቲካ እስረኞች መኖራቸውን ይናገራሉ።
እስረኛ መፍታትና ማዕከላዊን መዝጋትን የተመለከተው የኢሕአዴግ መግለጫ በአነስተኛ ዋጋ ብዙ ትርፍ ሊያስገኙ የሚችሉ በፖለቲካው ዓለም ሁለት ስስ ጉዳዮች የተመረቱበት እንደሆነ የቀድሞው የአዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጅ መስፍን ነጋሽ ይናገራል። "ከማሰር ይልቅ መፍታቱ ሕግና ደንብን መከተል እንዳለበት እየተነገረን ነው" የምትለው ደግሞ የአዲስ ስታንዳርድ ዋና አዘጋጅ ፀዳለ ለማ ናት። የውይይቱን ሙሉ ክፍል አድምጡት።
በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የተወለደው ጋዜጠኛ ኢብራሂም ሻፊ ረቡዕ ታኅሣሥ 25 ቀን 2010 ዓ.ም በናይሮቢ ከተማ ላንጋታ በተሰኘው ቦታ ልክ በ40ኛ ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ዛሬ አርብ ታኅሣሥ 27 ቀን 2010 ዓ.ም በአዲስ አበባ በኮልፌ እስላም መቃብር የቀብር ሥነ ስርዓቱ ተፈጽሟል።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት በእሥር የሚገኙት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግሬስ አመራር አባላት እነ አቶ ጉርሜሳ አያኖ በምክርነት በቆጠሩዋቸው ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት አቀራረብ ላይ ውሳኔ እንዳልደረሰለት አስታወቀ፡፡
አፍሪካ በጋዜጦች የተሰኘው ፕሮግራማችን ስለ አፍሪካ ከተፃፉት የተወሰኑትን ጨምቆ ያቀርባል።
ሰሞኑን የተጠናቀቀው የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ስብሰባ ከአመራሩ አንድነት አንፃር የነበሩ ችግሮች በጥልቀት የተዳሰሱበት እንደነበረ የግንባሩ አራት አባል ድርጅቶች ሊቃነ-መናብርት አስታወቁ፡፡
"ፕሮፌሰር እደማሪያም በግል ጥረታቸው የድሕረ ምረቃ የሕክምና ትምሕርት ፕሮግራሞች እንዲከፈት ያደረጉ ናቸው።" ከቀድሞ ተማሪዎቻቸው አንዱ ፕሮፌሰር ጌታቸው አደራዬ። “ለሕመምተኛና ለተማሪ ከፍ ያለ ክብር የሚሰጥ፤ ጥሩ ተማሪ የሚያፈራና ከእርሱ የተሻሉ እንዲሆኑ የሚያደርግ፤ ተማሪ ሆነን 'ተሳስተሃል' ብለን ደፍረን እንድናገረው የሚያበረታታን ፕሮፌሰር፤ ለሞያው የረቀቀ ክብር ያለው ‘ሃኪም’ የሚለው መጠሪያ ለእርሱ የተጻፈ የሚመስል ባለሞያ ነበር።” ዶ/ር አሰፋ ጄጃው።
ኤድ ሮይስ በምክር ቤቱ የካሊፎርኒያን 39ኛውን ወረዳ ማለትም የኦሬንጅ የሎስ አንጀለስ እና የሳን በርናርዲኖ ነዋሪዎችን ይወክላሉ።
ገዥው ፓርቲ አህአዴግና መንግሥት የፖለቲካ መሪዎችና ግለሠቦች ያሏቸውን ለመፍታት የደረሱበት ውሳኔ መነሻ፣ ከሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር እያነጋገረ ነው፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት ለዘመናት ሲክደው የነበረውን የፖለቲካ እስረኞች አምኖ ለመፍታት መወሰኑ የሚያስደስት ነው ያሉ ከዚህ ቀደም ታስረው የተፈቱ ሦስት የኢንተርኔት አምደኞች፤ “ነገር ግን ጉዳዩ እንደተለመደው የፖለቲካ ማታለያ ሆኖ እንዳይቀር ውሳኔው ግልጽ ሊደረግና በሀገሪቱ ውስጥ ባሉ እስር ቤቶች በየትኛውም የፖለቲካ አመለካከታቸው የታሰሩ ሰዎች በአስቸኳይ ሊፈቱ” ይገባል ብለዋል።
የጣና ሐይቅን የወረረው እምቦጭ እንዴት እንደሚወገድ፣ ኦታዋ ካናዳና አካባቢዋ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እየተረባረቡ ይገኛሉ።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አሥራ ዘጠነኛ ወንጀል ችሎት በኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግሬስ /ኦፌኮ/ ሊቀመንበር በዶ/ር መረራ ጉዲና እና በዓቃቤ ሕግ መካከል ባለው ክርክር ላይ ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ይዟል፡፡
ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በአሁኑ ወቅት በእሥር ላይ የሚገኙ የፖለቲካ እሥረኞች እንደሚፈቱና በዓቃቢ ሕግ የተመሰረተባቸው ክስም እንደሚቋረጥ ገለፁ፡፡
የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ “የዴሞክራሲያዊ ምኅዳሩን ለሁሉም ሰፊ ለማድረግ” ባሉት ጥረቶች ምክንያት፣ የፖለቲካ እስረኞች እንደሚፈቱ አስታውቀዋል።
ዓለምቀፉ የኢትዮጵያውያን የጋራ ግብረ ኃይል በአለፈው ሳምንት አርብ ጀምሮ በውጭ ሃገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የውጭ ምንዛሬ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይልኩ የተዓቅቦ ጥሪ።
በሀገሪቱ የተቃውሞ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚታወቁት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስና ሰማያዊው ፓርቲ “መግለጫው ምንም አዲስ ነገር የለውም የተለመደው አዘናግቶ መግዢያና አምባገነንነትን ማስቀጠያ ነው” ብለውታል።
የእሥላማዊ ሪፐሊካችን ጠላቶች ሁከት አዘል ፀረ-መንግሥት ተቃውሞዎችን እያራገቡ ነው ሲሉ የኢራን የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ሃሜኒ ዛሬ ክሥ አሰምተዋል።
በአመራር ድክመት የተፈጠሩትን አደጋዎችና ሥጋቶች ለመቅረፍ በሚያስችል መግባባትና ስምምነት ግመገማውን ማጠናቀቁ የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡
በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሻምቡ ከተማ ውስጥ ዛሬ ጠዋት በተነሳ ግጭት በተኩስ የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ አራት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ።
“ለመቀራረብ የሚረዱት ነገሮች በአገዛዙ እጅ ነው ያሉት። አንደኛ የመወያያ መስመሮችን በሙሉ ነጻነት እንዲኖሩ ማድረግ። ሁለተኛ ምንም ተጨባጭ ወንጀል ሳይኖርባቸው፤ በፖለቲካ ምክንያት ሃሳባቸውን በነጻ በመግለጻቸው ብቻ የታሰሩ ሰዎችን መልቀቅ። እነኚህ ለዜጎች በሙሉ እንደ አዲስ እንድንጀምር፤ ቂምንና ጥላቻን እንድንሰርዝ ይረዱናል። በእነኚህ በትንንሽ ነገሮች ብንጀምር ጥሩ ነው እላለሁ።” ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም
ኢህአዴግ ሀገሪቱ ውስጥ ያለውን ችግር ሊፈታ እንደማይችል አሳይቶናል ሲሉ አቶ ልደቱ አያሌው አስታወቁ፡፡
ተጨማሪ ይጫኑ