በሀገሪቱ የተቃውሞ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚታወቁት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስና ሰማያዊው ፓርቲ “መግለጫው ምንም አዲስ ነገር የለውም የተለመደው አዘናግቶ መግዢያና አምባገነንነትን ማስቀጠያ ነው” ብለውታል።
የእሥላማዊ ሪፐሊካችን ጠላቶች ሁከት አዘል ፀረ-መንግሥት ተቃውሞዎችን እያራገቡ ነው ሲሉ የኢራን የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ሃሜኒ ዛሬ ክሥ አሰምተዋል።
በአመራር ድክመት የተፈጠሩትን አደጋዎችና ሥጋቶች ለመቅረፍ በሚያስችል መግባባትና ስምምነት ግመገማውን ማጠናቀቁ የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡
በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሻምቡ ከተማ ውስጥ ዛሬ ጠዋት በተነሳ ግጭት በተኩስ የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ አራት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ።
“ለመቀራረብ የሚረዱት ነገሮች በአገዛዙ እጅ ነው ያሉት። አንደኛ የመወያያ መስመሮችን በሙሉ ነጻነት እንዲኖሩ ማድረግ። ሁለተኛ ምንም ተጨባጭ ወንጀል ሳይኖርባቸው፤ በፖለቲካ ምክንያት ሃሳባቸውን በነጻ በመግለጻቸው ብቻ የታሰሩ ሰዎችን መልቀቅ። እነኚህ ለዜጎች በሙሉ እንደ አዲስ እንድንጀምር፤ ቂምንና ጥላቻን እንድንሰርዝ ይረዱናል። በእነኚህ በትንንሽ ነገሮች ብንጀምር ጥሩ ነው እላለሁ።” ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም
ኢህአዴግ ሀገሪቱ ውስጥ ያለውን ችግር ሊፈታ እንደማይችል አሳይቶናል ሲሉ አቶ ልደቱ አያሌው አስታወቁ፡፡
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በእነ ጉርሜሳ አያኖ ጉዳይ በሚመሰክሩበት አግባብ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ ቆርጧል፣ ሌሎች ተለዋጭ ቀጠሮዎችንም ሰጥቷል፡፡
ዘመቻው ማረሚያ ቤቱ ውስጥ እየተፈፀመ ያለውን የመብት ጥሰት ምስል ያሳየ ነበር ያሉት አስተባባሪዎቹ ለአንድ ቀንም ቢሆን ብዙ ሰው የተሳተፈበትና የእስረኞቹ ታሪኮች የተነገሩበት ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ በኦሮምያና በሶማሌ ክልል ተወላጆች መካከል የሚካሄደው ግጭት አላቆመም። ከሁለቱም በኩል ብዙ ስዎች እንደተገደሉና ብዙ ቤቶች እንደጋዩ ተዘግቧል። በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መካከል፣ ብሄር ተኮር ግጭት ተከስቷል።
እስረኞቹ በምርመራ ወቅት አሰቃቂ ተግባር እንደተፈፀመባቸና ይህንንም ችሎት በሚቀርቡበት ወቅት እንደሚናገሩ አንዳንዶቹም ልብሳቸውን ገልጠው የተጎዳውን የሰውነታቸውን ክፍል ለችሎት እንደሚያሳዩ ጠበቀቻቸው ተናግረዋል።
"መታከምም ሆን ማንበብ ተከልክሏል" የምትለው በእስር ላይ የሚገኙት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ም/ሊቀመንበር ልጅ ወ/ት ቦንቱ በቀለ አባቷን ልትጠይቅ ስትሄድ መታመማቸውን እንደነገሯት ተናግራለች።
ለኢትዮጵያ የመንግሥት ሰራተኛ ሴቶች የሚሰጠው የወሊድ ፈቃድ ሦስት ወር የነበረው አራት ወር እንዲሆን ተራዝሟል።
እየተካሄዱ ያሉ እሥራቶች ሰላማዊ የትግል እንቅስቃሴያቸውን እያወኩ መሆናቸውን የስልጤ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባል አስታወቁ፡፡
በኢትዮጵያ የታሪክ መዝገብ በሥነ-ጥበብ ምዕራፍ በሙዚቃው ገፅ ላይ ጎልተው ካሉ ስሞች አንዱ በረከት መንግሥትአብ ተብሎ ይነበባል።
ምዕራብ ሃረርጌ ዳሮ ለቡ ወረዳ ውሰጥ ዛሬ ተጣለ ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች በገለፁት ጥቃት አንድ ሰው መገደሉ፣ አንድ ሰው መቁሰሉና ሰባ ግመሎች መዘረፋቸው ተገለፀ። የዞኑ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽንስ ጉዳዮች ኃላፊ ግን ዛሬ ተፈጠረ የተባለውን ሁኔታ አስተባብለዋል።
በኅዳሴ ግድብ ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን ወደፊት ለማራመድ የሚያስችል አዲስ ሃሣብ ማቅረባቸውን ኢትዮጵያ ውስጥ ጉብኝት ላይ ያሉት የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰምሃ ሹክሪ አስታውቀዋል።
"እነ ጉርሜሳ አያኖ" በሚል የክስ መዝገብ በእሥር ሆነው እየተከራከሩ የሚገኙት አራቱ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ አመራር አባላት፣ በምስክርነት የቆጠሯቸው ከፍተኛ የመንግሥቱ ባለሥልጣናት፣ ዛሬ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ።
ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ የተወሰኑ አመራሮችን ከኃላፊነት ዝቅ እንዲሉ መወሰናቸውን የኢዴፓ ብሔራዊ ምክር ቤት አባላት አስታውቀዋል።
ዛሬ የፈረንጅ ገና ነው /በኢትዮጵያዊያን አጠራር/ ወይም ባለቤቶቹ እንደሚሉት ክሪስማስ።
የፌደራሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ በኦሮሞ ፌዳራሊስት ኮንግረስ /ኦፌኮ/ ሊቀ መንበር በዶ/ር መረር ጉዲና ላይ አሥር ሲዲ ተጨማሪ ማስረጃ ማቀረቡ ተሰማ። የተከሳሹ ጠበቃ ተቃውሞአቸውን ለፍርድ ቤት ማቅረባቸውን ይናገራሉ።
የቀድሞ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትርና አምባሣደርም ሆነው ያገለገሉት ኸርማን ኮኸን ባለፈው ሣምንት ውስጥ በትዊተር ባወጡት ሃሣብ ለሕዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ - ሕወሐት መሪዎች ምክር አዘል መልዕክት አስተላልፈዋል።
በኦሮምያና በሶማሌ ክልል አዋሳኝ ወረዳዎች የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ የተፈናቀሉ ዜጎችን ለመደገፍ የበኩላቸውን እያደረጉ መሆኑን የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበርና ዓለምቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታውቀዋል፡፡
በመቀሌ ከተማ የጤፍ ዱቄት ከኖራ ደባልቆ ለማረሚያ ቤት በማቅረብ የተጠረጠረ ነጋዴ፣ በቁጥጥር ሥር መዋሉ ታውቋል፡፡
99 በመቶ በኢሕዴግ አባላት የሚመራው የኢትዮጵያው ፓርላማ አባላት ሰዎች ከቀያቸው እየተፈናቀሉና እየሞቱ ውይይት ሊደረግ አይገባም ሲሉ ለዛሬ ተጠርቶ የነበረውን የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ያለውን ልዩ ጥቅም በተመለከተ የተዘጋጀን የዐዋጅ ረቂቅ ውይይት ላልተወሰነ ጊዜ አራዘሙት።
በምሥራቅ ሀረርጌ ዞን ጉሚ ቦርደዴ ወረዳ ኦቦንሳ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ከሶማሌ ክልል የመጣው ልዩ ኃይል ዛሬ ጠዋት በደረሰው ጥቃት የ6 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን ነዋሪዎችና የወረዳ ባለሥልጣናት ገልፀዋል፡፡
ተጨማሪ ይጫኑ