“ዩናይትድ ስቴትስ በክልሉ ላላት በብሔራዊ ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ላተኮረ ግንኙነቷ ቅድሚያ በመስጠት ለረዥም ጊዜ በኢትዮጵያ መንግስት የሚፈጽሙትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች አይታ እንዳላየች ስታደርግ ቆይታለች። ያ ፍጹም የተሳሳተ ነገር ነው። በመሆኑም ይሄ ያን ስህተት የማመን የመጀመሪያ እርምጃ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት በገዛ ዜጎቹ ላይ የሚፈጽመው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጽሞ ተቀባይነት የለውም።” ኮንግሬስማን ማይክል ሃዋርድ ኮፍማን የUS የተወካዮች ምክር ቤት አባል።
በምኅፃር ናሳ (NASA) ተብሎ የሚጠራው የኬንያው ግዙፍ የተቃውሞ ጥምረት ብሄራዊ እምቢ ባይነት ንቅናቄ “የወንጀል ቡድን ነው” ሲል የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስቴሩ አስታወቀ።
የአፍሪካ ሕብረት ጉባዔ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በዛሬው ዕለት አፍሪካ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ያላትን የንግድና ምጣኔ ኃብት ትስስር የተመለከተ ውይይት ተካሂዷል።
ንግድና ኢንቨስትመንት ለአፍሪካ መፃዒ ዕጣ ያላቸውን አስፈላጊነት እንደሚረዱ የገለፁ የአፍሪካ መሪዎች ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ሁኔታ ለመፍጠር የሚያደርጉትን ጥረት እያፋጠኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ዩናይትድ ስትቴትስ ኖርዌይና ብሪታንያ ደቡብ ሱዳን የሚዋጉት ሁሉም ወገኖች አሁንም በብዙ አስር ሺሕዎች የሚቆጠሩ ልጆችን ለተዋጊነት መመልመላቸውን መቀጠላቸው ያሳሰባቸው መሆኑን ገለፁ።
በሰሜን ምሥራቃዊቱ የሊቢያ ከተማ ቤንጋዚ በሁለት ተሽከርካሪዎች ላይ የተጠመዱ የቦምቦች ፈንድተው ለሠላሳ ሦስት ሠዎች ሕይወት መጥፋት እና ሌሎች በርካቶች መቁሰል ምክኒያት መሆናቸው ተገለጠ።
የኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በእስራኤል የሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞችን ወደ ሌላ ሀገር ለማሽጋገር የቀረበው ሃሳብ ተቀባይነት የሌለው ነው ብለዋል፡፡
ሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ አቅራቢያ ዛሬ ማክሰኞ በርቀት መቆጣጠሪያ በፈነዳ ቦምብ አራት ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች ሥድስት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ባለሥልጣናትና እማኞች ገለፁ።
በደቡብ ሱዳን ግጭት ውስጥ የሚሳተፉት ወገኖች በሙሉ ከአንድ ወር በፊት የተፈረመውን የተኩስ አቁም ውል እንዲያከብሩ የሀገሪቱን የሰላም ሥምምነት ተፈፃሚነት የሚቆጣጠረው አካል አሳሰበ።
የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ ጉባዔ አዲስ አበባ ላይ ተከፍቷል፡፡
አፍሪካ በጋዜጦች የተሰኘው ፕሮግራማችን ስለ አፍሪካ ከተፃፉት የተወሰኑትን ጨምቆ ያቀርባል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚታየው አለመረጋጋት ምክንያቱ ‘የሕገ መንግሥቷ አንቀፅ 39 ነው’ ሲሉ የኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ አስታውቀዋል።
በሰሜን አፍሪካይቱ ሀገር ቱኒዚያ መንግሥት የወሰደውን የቁጠባ እርምጃን በመቃውም ለሦስት ቀናት ያህል በተካሄደው ግጭት የታከለበት ሰልፍ ከ5መቶ በላይ የሚሆኑ ሰዎች መታሰራቸውን ባለሥልጣኖች ገልፀዋል።
የቱርክ መንግሥት ለሶማልያ ወታደሮች ጦር መሣሪያ መስጠቱን፣ የሶማልያው መከላከያ ሚኒስትር መሐመድ ዓሊ ሀጋ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአሜሪካ ድምፅ ራድዮ ሶማልኛ አገልግሎት አረጋገጡ።
"ፕሮፌሰር እደማሪያም በግል ጥረታቸው የድሕረ ምረቃ የሕክምና ትምሕርት ፕሮግራሞች እንዲከፈት ያደረጉ ናቸው።" ከቀድሞ ተማሪዎቻቸው አንዱ ፕሮፌሰር ጌታቸው አደራዬ። “ለሕመምተኛና ለተማሪ ከፍ ያለ ክብር የሚሰጥ፤ ጥሩ ተማሪ የሚያፈራና ከእርሱ የተሻሉ እንዲሆኑ የሚያደርግ፤ ተማሪ ሆነን 'ተሳስተሃል' ብለን ደፍረን እንድናገረው የሚያበረታታን ፕሮፌሰር፤ ለሞያው የረቀቀ ክብር ያለው ‘ሃኪም’ የሚለው መጠሪያ ለእርሱ የተጻፈ የሚመስል ባለሞያ ነበር።” ዶ/ር አሰፋ ጄጃው።
የቀድሞውን የዚምባብዌ ፕሬዚዳንት ሮቤርት ሙጋቤን ባለፈው ዓመት ዘልፈሻል በሚል ታስራ የነበረችን የዩናይትድ ስቴትስ ዜጋ ክሥ አንድ የሃገሪቱ ፍርድ ቤት ውድቅ አድርጎ በነፃ አሰናብቷታል።
የናይጀሪያ ጦር ኃይል፣ በአማፂው ቡድን ቦኮ ሃራም ከአራት ዓመታት በፊት ከቺቦክ ትምህርት ቤት ተጠልፈው ከነበሩት ልጃገረዶች መካከል አንዷን ማስለቀቁ ተገለፀ።
ኬንያ ውስጥ የእስላማዊው አልሻባብ አማፅያን በፖሊሶች ተሽከርካሪ ላይ ዛሬ ባደረሱት ጥቃት፣ አምስት መኮንኖች መሞታቸው ተገለፀ።
በሰሜናዊ ናይጄሪያ ቦርኖ ክፍለ ሃገር ውስጥ በሚገኝ መስጊድ ዛሬ በደረሰ የአጥፍቶ ጠፊ ፍንዳታ፣ አሥር ሰዎች መሞታቸው ተገፀ።
ግብጽ ዋና ከተማ ካይሮ አቅራቢያ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን ደጃፍ ዛሬ ዓርብ ተኩስ የከፈተው ታጣቂ ቢያንስ አራት ሰዎች ገደለ። ሌሎች አምስት ሰዎች አቁስሏል። ከሞቱት መካከል አንዱ ፖሊስ መሆኑ ታውቋል።
“ለመቀራረብ የሚረዱት ነገሮች በአገዛዙ እጅ ነው ያሉት። አንደኛ የመወያያ መስመሮችን በሙሉ ነጻነት እንዲኖሩ ማድረግ። ሁለተኛ ምንም ተጨባጭ ወንጀል ሳይኖርባቸው፤ በፖለቲካ ምክንያት ሃሳባቸውን በነጻ በመግለጻቸው ብቻ የታሰሩ ሰዎችን መልቀቅ። እነኚህ ለዜጎች በሙሉ እንደ አዲስ እንድንጀምር፤ ቂምንና ጥላቻን እንድንሰርዝ ይረዱናል። በእነኚህ በትንንሽ ነገሮች ብንጀምር ጥሩ ነው እላለሁ።” ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም
ዩናይትድ ስቴትስ ማዕቀብ ብትጥልብኝም በአደባባይ የፕሬዚደንት ሳልቫ ኪር መንግሥትን ወክዬ መናገሬን አልተውም ሲሉ የደቡብ ሱዳን የማስታወቂያ ሚኒስትር ማይክል ማኩዌ ተናገሩ።
ዩናይትድ ስቴትስ ትናንት ሶማሊያ ውስጥ ባደረሰችው የአየር ጥቃት አራት የፅንፈኛው አልሸባብ አባላት መግደሏን እና ዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ አቅራቢያ ፈንጂ ጭኖ ይጓዝ የነበረ መኪና ማውደሟን የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ዕዝ ዛሬ አስታወቀ፡፡
"ከስምንታችን መሃከል አንድ እርሡ ወንድሜ ብቻ ነው የታሰረው። እንደሚመስለኝ ወንድሜ ተዋጊ ወታደር መስሏቸው ይሆናል። ነገር ግን እርሱ ተዋጊ ወታደር አይደለም።" ግሬስ ገበ ቁጥሩ 30 ሺህ የሚደርስ ስደተኛ በማስተናገድ ላይ በምትገኘው የድንበር ከተማ አባ ከተጠለሉ ደቡብ ሱዳናውያን አንዷ።
ላይቤሪያዊያን መጭውን ፕሬዚዳንታቸውን ለመምረጥ ትናንት ሲሰጡ የዋሉትን ድምፅ ውጤት በጉጉት እየጠበቁ መሆናቸውን እየገለፁ ነው።
ተጨማሪ ይጫኑ