የምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮች የጋራ ልማት ትብብር /ኢጋድ/ ባለሥልጣን ባለፈው ቅዳሜ ባካሄደው ስብሰባ ወደ ሀገራቸው በፍላጎታቸው ለሚመለሱ የሶማልያ ተወላጆች ሁኔታዎችን ለማመቻቸትና ሶማልያ ውስጥ ስላለው የፖለቲካና የፀጥታ ሁኔታ መፍታኄ ለማበጀት ተስማምተዋል።
ከጁባ ወደ ፒቦር ሲጓዙ የነበሩ ስድስት የረድዔት ድርጅት ባልደረቦች ባለፈው ቅዳሜ ደቡብ ሱዳን ውስጥ ተገድለዋል።
አዲሱ የሶማልያ ፕሬዚዳንት ሞሐመድ አብዱላሂ ፋርማጆ በትላንትናው ዕለት ሃገራቸው ወደ ቸነፈር ሊለወጥ የተቃረበውን ረሃብ ለማስወገድ በያዘችው ጥረት ይረዳ ዘንድ ዓለምቀፉን ማኅበረሠብ ተማፅነዋል።
ሱዳን፣ በኬሚካላዊ ጦር መሣሪያ ዕገዳ ድርጅት ውስጥ ወሳኝ ቁልፍ ሚና ተሰጣት፣ በአንዳንድ ተንታኞች ዘንድ ግን፣ የድርጅቱን ተዓማኒነት ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ውሳኔ ነው በሚል ነቀፋ አስነስቷል።
የዓለም ሚቲኦሮሎጂ ቀን መጋቢት 14 “ደመናን መረዳት” በሚል መሪ ቃል በመላው ዓለም ታስቦ ውሏል፡፡
ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ በሦስት የአፍሪ ሀገሮችና በየመን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይውት ሊያጠፋ የሚችል ረሃብ ለመግባት የቀረው የአራት ወራት ጊዜ ነው ሲል አስጠንቅቋል።
በቅርቡ ወደ ጋምቤላ ክልል በመግባት ሃያ ስምንት ሰዎችን የገደሉትና ሕፃናትን ጠልፈው የወሰዱት ዶ/ር ሪያክ ማቻር ከሚመሩት አማፂያን ጋር ሕብረት የፈጠሩ ሙርሌዎች ናቸው ሲሉ በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ተናገሩ፡፡
“የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ባይታወጅ ኖሮ የት ነው የሚቆመው አመጹ? የት ነው ጋብ የሚለው ነገር በጣም አጠያያቂ ነው የነበረው።” አቶ አታክልት አምባዬ። “የአስቸኳይ ጊዜውን አዋጁን ያወጁትም ሰዎች መፍትሔው እንፈልጋለን መፍትሔ አልተፈለገም። መፍትሔው ምንድ ነው? ችግሩ ምንድነው? የሚለው ነገር ላይ ውይይት አላየንም።” አቶ ፈቃደ ሸዋ ቀና።
የቆይታ ጊዜው ከአንድ ወር በኋላ የሚጠናቀቀው የአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ በከፊል ሊራዘም እንደሚችል ጠ/ሚ ኃይለማሪያም ደሳለኝ አስታወቁ፡፡
“በተለያዩ ሁኔታ በፍርድ ቤት ሂደቶች አልፈው ጉዳያቸው ሳይሳካላቸው ቀርቶ ነገር ግን ወንጀል ስለሌላቸው ሊሆን ይችላል ከአገር ያልተባረሩ፤ በዓመት ወይ በስድስት ወር አንዴ ወደ ኢሚግራሽን መሥሪያ ቤት እየፈረሙ በሰላም የመሚኖሩ .. ለእነኚህና ለሌሎች አሁን አሳሳቢ ሁኔታ እየተፈጠረ ነው።” የሚ ጌታቸው በካሊፎኒያ የአሜሪካ የሕግ-ጠበቆች ማኅበር የሳንታክላራ ቫሊ ሊቀመንበር።
“የልብ ትርታ መረበሽ ብዙውን ጊዜ ያንን ያህል ለጤና የሚያሰጋ ነገር የለውም። ምን ሊሆን ይችላል በሚል ግለሰቡን ማሳሰቡ ነው። ነገር ግን ረዘም ላለ ጊዜ ተደጋግሞ ሲመጣ፥ ከእርሱ ጋር ተያይዞም የትንፋሽ ማጠር እና ደረት ላይ ጫና በሚሰማበት ጊዜ ግን ሌላ ክትትል ሊያስፈልገው ይችላል።” ዶ/ር ውብሸት አየነው የልብ ሕክምና ከፍተኛ አማካሪ ሃኪም ናቸው።
ጉዳዩን በውጭ ሆነው የሚከታተሉ የሟቾቹን ቁጥር 13 ያድርሱታል። ታፍነው የተወሰዱት 27 እንደሆኑ ሲናገሩ። በርካታ ቤቶች ተቃጥለዋል ይላሉ።
በደቡብ አፍሪካ ከሁለት ዓመት በኋላ በድጋሚ ባገረሸው በመጤዎች ጥላቻ ላይ ያነጣጠረ ዝርፊያ ፕሪቶሪያ "አትረጅቪል" በተባለች መንደር ውስጥ ሙሉ የሱቅ ንብረታቸውን እንደተሰረቁ ሁለት ኢትዮጵያውያን ለአሜሪካ ድምጽ ተናገሩ። በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ሱቃችን ሲዘረፍ ይሄ ሁለተኛ ጊዜያቸው እንደሆነ የተናገሩት ነጋዴዎች “ሱቆቹን ያሟላነው ተበድረን ነበር። ዕዳውን ሳንከፍል ከነቤተሰቦቻችን ቧዶ እጃችንን ቀረን ብለዋል።”
የመሠረታዊ ሰብዓዊ መብቶች ከበሬታ የተመረኮዘው የዓለም ሠላምና መረጋጋት “ደንታ ቢስ የፖለቲካ ጥቅም አግበስባሶች” በሚባሉት አደጋ ተደቅኖባቸዋል ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ዜይድ ራዓድ አል ሁሴን አስጠነቀቁ።
በ1ሺኽ 5 መቶ የዓለም ሻምፒዮኗ ገንዘቤ ዲባባ በዓለም አቀፉ የ ቪልላ ድ ማድሪድ አንድ ሺኽ ሜትር ሩጫ ውድድር የግልዋን ፈጣን ጊዜ አስመዝግባ አሸነፈች።
የኦሮምያና የሶማሌ ክልል አዋሳኝ በሆኑ ወረዳዎች በታጣቂዎች ለሚፈፀምው ጥቃት መፍትሄ ለማስገኘት በአስቸኳይ ጊዜ ኮማንድ ፖስትና በሁለቱ ክልሎች ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መንግሥት አስታወቀ፡፡
ከሊብያ ወደ ጣልያን በሚወስደው የሜዲቴራኔያን ባሕር መሥመር ላይ የሚሞቱ ፍልሰተኞች ቁጥር ማሻቀቡን የሚያሳዩ ሪፖርቶች እየደረሱት መሆኑን ዓለምአቀፉ የፍልሰት ድርጅት - አይኦኤም አስታወቀ፡፡
የተባበሩት መንግሥታት የምግብና እርሻ ድርጅት /FAO/ በሁኔታው ቤተሰቦችና አርብቶ አደሮች እየተሰቃዩ ነው እንደሆነ አስታውቋል።
“ፈርማጆ” በሚለው ቅጽል ስማቸው የሚታወቁት አዲሱ የሀገሪቱ ፕሬዝደንት ሞሐመድ አብዱላሂ ቃለ መሃላ ፈጽመው በትረ ስልጣኑን ተረክበዋል። በሚቀጥሉት አራት ዓመታት ሀገሪቱን ለማረጋጋት፣ ሰላም ለማስፈንና በአሁኑ ወቅት በርካታ ዜጎችን ለተረጂነት ያጋለጠው ድርቅ ያስከተለውን ረሃብ ለመቋቋም ሕዝቡ፣ መንግስቱና አጋሮቻቸው አብረው እንዲሠሩ ጠይቀዋል
“በሰላምም ይሁን በአመፅ - ነፃነት በአስፈላጊው መንገድ ሁሉ!” ይል ነበር ማልኮም ኤክስ በየንግግሩ አዝማች፤ እንደልማድም ሆኖበት፤ ደግሞም የነፃነትን አስፈላጊነት ለማፅናት፡፡
በሊቢያ ሰሜናዊ የባሕር ወደብ፣ ቢያንስ ሰባ አራት የአፍሪካውያን ፍልሰተኞች አስከሬን ማግኘቱን፣ የሊቢያ ቀይ ጨረቃ ዛሬ ማክሰኞ አስታወቀ።
ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ታዋቂው የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት በተለይ በኢኮኖሚ ታሪክ ዘርፍ ፈር ቀዳጅ ሥራ መስራታቸውን አንጋፋ ኢትዮጵያዊ ሙሑር ተናግረዋል፡፡
18ኛው የኢትዮ ሱዳን የድንበር ልማት ስብሰባ መቀሌ ከተማ ውስጥ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
“የሕጉን መሠረት ሲጥሉ ይሄው እስካሁን ድረስ ከሞላ ጎደል በዚያ ማዕቀፍ ሥር ነው ይሄ ማኅበረሰብ የሚንቀሳቀሰው። ምን ድነው መርሳት የሌለብን ያችኛዋ አሜሪካ በ1789 ሕገ መንግስት የተወለደችውን። ይሄ ኅገ-መንግስት ሲቀረጽ በጊዜው ለማን ነው የተቀረጸው? የሚለውን ነው።” ዶ/ር ብሩክ ኃይሉ የፖለቲካ ሳይንስ መምሕር
"ጆን ብራውን በጣም የተበሳጨ አሜሪካዊ ነው፡፡ ባርነት የማስወገጃው ብቸኛ መንገድ ተቋሙን በአምፅ ማሰወገድ ነው ብሎ ያምን ነበር፡፡ በጦርነት መደምሰስ" የሀርፐርስ መሪ ብሔራዊ ፓርክ ዋና የታሪክ ተመራማሪው ዴኒስ ፍራይ የባርነት መሪና ተቃዋሚው ጆን ብራውንና ጓዶቹ ያንን የአሜሪካ የፅልመት ዕድሜ ለማብቃት የጀመሩትን ትግል ያስታውሳሉ፡፡
ተጨማሪ ይጫኑ