“የልብ ትርታ መረበሽ ብዙውን ጊዜ ያንን ያህል ለጤና የሚያሰጋ ነገር የለውም። ምን ሊሆን ይችላል በሚል ግለሰቡን ማሳሰቡ ነው። ነገር ግን ረዘም ላለ ጊዜ ተደጋግሞ ሲመጣ፥ ከእርሱ ጋር ተያይዞም የትንፋሽ ማጠር እና ደረት ላይ ጫና በሚሰማበት ጊዜ ግን ሌላ ክትትል ሊያስፈልገው ይችላል።” ዶ/ር ውብሸት አየነው የልብ ሕክምና ከፍተኛ አማካሪ ሃኪም ናቸው።
ጉዳዩን በውጭ ሆነው የሚከታተሉ የሟቾቹን ቁጥር 13 ያድርሱታል። ታፍነው የተወሰዱት 27 እንደሆኑ ሲናገሩ። በርካታ ቤቶች ተቃጥለዋል ይላሉ።
በደቡብ አፍሪካ ከሁለት ዓመት በኋላ በድጋሚ ባገረሸው በመጤዎች ጥላቻ ላይ ያነጣጠረ ዝርፊያ ፕሪቶሪያ "አትረጅቪል" በተባለች መንደር ውስጥ ሙሉ የሱቅ ንብረታቸውን እንደተሰረቁ ሁለት ኢትዮጵያውያን ለአሜሪካ ድምጽ ተናገሩ። በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ሱቃችን ሲዘረፍ ይሄ ሁለተኛ ጊዜያቸው እንደሆነ የተናገሩት ነጋዴዎች “ሱቆቹን ያሟላነው ተበድረን ነበር። ዕዳውን ሳንከፍል ከነቤተሰቦቻችን ቧዶ እጃችንን ቀረን ብለዋል።”
የመሠረታዊ ሰብዓዊ መብቶች ከበሬታ የተመረኮዘው የዓለም ሠላምና መረጋጋት “ደንታ ቢስ የፖለቲካ ጥቅም አግበስባሶች” በሚባሉት አደጋ ተደቅኖባቸዋል ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ዜይድ ራዓድ አል ሁሴን አስጠነቀቁ።
በ1ሺኽ 5 መቶ የዓለም ሻምፒዮኗ ገንዘቤ ዲባባ በዓለም አቀፉ የ ቪልላ ድ ማድሪድ አንድ ሺኽ ሜትር ሩጫ ውድድር የግልዋን ፈጣን ጊዜ አስመዝግባ አሸነፈች።
የኦሮምያና የሶማሌ ክልል አዋሳኝ በሆኑ ወረዳዎች በታጣቂዎች ለሚፈፀምው ጥቃት መፍትሄ ለማስገኘት በአስቸኳይ ጊዜ ኮማንድ ፖስትና በሁለቱ ክልሎች ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መንግሥት አስታወቀ፡፡
ከሊብያ ወደ ጣልያን በሚወስደው የሜዲቴራኔያን ባሕር መሥመር ላይ የሚሞቱ ፍልሰተኞች ቁጥር ማሻቀቡን የሚያሳዩ ሪፖርቶች እየደረሱት መሆኑን ዓለምአቀፉ የፍልሰት ድርጅት - አይኦኤም አስታወቀ፡፡
የተባበሩት መንግሥታት የምግብና እርሻ ድርጅት /FAO/ በሁኔታው ቤተሰቦችና አርብቶ አደሮች እየተሰቃዩ ነው እንደሆነ አስታውቋል።
“ፈርማጆ” በሚለው ቅጽል ስማቸው የሚታወቁት አዲሱ የሀገሪቱ ፕሬዝደንት ሞሐመድ አብዱላሂ ቃለ መሃላ ፈጽመው በትረ ስልጣኑን ተረክበዋል። በሚቀጥሉት አራት ዓመታት ሀገሪቱን ለማረጋጋት፣ ሰላም ለማስፈንና በአሁኑ ወቅት በርካታ ዜጎችን ለተረጂነት ያጋለጠው ድርቅ ያስከተለውን ረሃብ ለመቋቋም ሕዝቡ፣ መንግስቱና አጋሮቻቸው አብረው እንዲሠሩ ጠይቀዋል
“በሰላምም ይሁን በአመፅ - ነፃነት በአስፈላጊው መንገድ ሁሉ!” ይል ነበር ማልኮም ኤክስ በየንግግሩ አዝማች፤ እንደልማድም ሆኖበት፤ ደግሞም የነፃነትን አስፈላጊነት ለማፅናት፡፡
በሊቢያ ሰሜናዊ የባሕር ወደብ፣ ቢያንስ ሰባ አራት የአፍሪካውያን ፍልሰተኞች አስከሬን ማግኘቱን፣ የሊቢያ ቀይ ጨረቃ ዛሬ ማክሰኞ አስታወቀ።
ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ታዋቂው የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት በተለይ በኢኮኖሚ ታሪክ ዘርፍ ፈር ቀዳጅ ሥራ መስራታቸውን አንጋፋ ኢትዮጵያዊ ሙሑር ተናግረዋል፡፡
18ኛው የኢትዮ ሱዳን የድንበር ልማት ስብሰባ መቀሌ ከተማ ውስጥ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
“የሕጉን መሠረት ሲጥሉ ይሄው እስካሁን ድረስ ከሞላ ጎደል በዚያ ማዕቀፍ ሥር ነው ይሄ ማኅበረሰብ የሚንቀሳቀሰው። ምን ድነው መርሳት የሌለብን ያችኛዋ አሜሪካ በ1789 ሕገ መንግስት የተወለደችውን። ይሄ ኅገ-መንግስት ሲቀረጽ በጊዜው ለማን ነው የተቀረጸው? የሚለውን ነው።” ዶ/ር ብሩክ ኃይሉ የፖለቲካ ሳይንስ መምሕር
"ጆን ብራውን በጣም የተበሳጨ አሜሪካዊ ነው፡፡ ባርነት የማስወገጃው ብቸኛ መንገድ ተቋሙን በአምፅ ማሰወገድ ነው ብሎ ያምን ነበር፡፡ በጦርነት መደምሰስ" የሀርፐርስ መሪ ብሔራዊ ፓርክ ዋና የታሪክ ተመራማሪው ዴኒስ ፍራይ የባርነት መሪና ተቃዋሚው ጆን ብራውንና ጓዶቹ ያንን የአሜሪካ የፅልመት ዕድሜ ለማብቃት የጀመሩትን ትግል ያስታውሳሉ፡፡
ኬንያ ውስጥ ሰባት የሐኪሞች ማኅበር ባለሥልጣናት ለአንድ ወር በእስር እንደሚቆዩ ተገለፀ።
የኬንያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዓለም እጅግ ግዙፍ የሚባለው የስደተኞች መጠለያ ሠፈር እንዳይዘጋ ማገዱን የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች አሞግሰዋል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሠባት አብዛኞቹ የእስልምና ዕምነት ተከታይ በሆኑ ሀገሮች ዜጎች ላይ የጣሉት የጉዞ ገደብ እንዲፀና ያቀረቡትን ጥያቄ የዩናይትድ ስቴትስ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ትላንት ማታ ውድቅ አደረገ።
አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዚደንት ሞሃመድ ኣብዱላሂ የሀገራቸውን ስም ከዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ትረምፕ የጉዞ እገዳ ዝርዝር ላይ ለማስፋቅ ጥረት እንደሚያደርጉ አስታወቁ።
በአመዛኙ ሙስሊም ከሆኑ ሰባት ሀገሮች ፍልሰተኞችና ስደተኞች ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዳይገቡ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጥለውት የነበረውን የማስፈፀሚያ ትዕዛዝ ያስቆመው የሴአትል ዳኛ ውሣኔ በይግባኝ ሰሚ ችሎት ፀና፡፡
ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ መንግሥቱ የዳዳብን መጠለያ ጣቢያ እንዳይዘጋ ከለከለው።
ሶማልያ አዲስ ፕሬዚዳንት መርጣለች፤ ትናንት ነው የሶማሊያ ፓርላማ በሁለተኛ ዙር ምርጫ ሞሐመድ ዐብዱላሂ ሞሐመድን የመረጣቸው። አዲሱ ፕሬዚደንት የተመረጡት የቀድሞውን ፕሬዚዳንት ሃሰን ሼክ መሃሙድን 184 ለ97 በሆነ ድምፅ ብልጫ አሸንፈዋቸው፡፡
የሶማልያ ምክር ቤት አባላት ቀጣዩን የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ለመምረጥ በሰጡት ድምጽ “ፋርማጆ” በሚል ቅጽል ስም የሚታወቁት ሞሐመድ ዐብዱላሂ ሞሐመድ የበዛ ድምፅ በማግኘት ለሀገሪቱ ፕሬዚዳንትነት ሆነው ተመርጠዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ የጉዞ ዕገዳ ሕግ፣ ኬንያ ውስጥ ውዥንብር ፈጥሯል።
ከሊቢያ ተነስተው በሜዲተራኒያን ባህር አቋረጠው ወደ ጣሊያን ለመግባት በጉዞ ላይ የነበሩና ባጋጠማቸው አደጋ የድረሱልኝ ጥሪ ያሰሙ 1500 ስደተኞች በጣሊያን የባህር ላይ ጠባቂዎች አማካኝነት ሕይወታቸው ተርፏል።
ተጨማሪ ይጫኑ