በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ማየት የተሳነው ቦይ ስካውት
የአዲስ አበባ ስካውት ማህበር በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን አይነስውር ስካውት ከዳግማዊ ሚኒሊክ አንደኛ ድረጃ ትምህርት ቤት ለስካውት ለቃለ መሃላ አብቅቷል።። ከተመሰረተ ከመቶ አመታት በላይ ያስቆጠረው የኢትዮጵያ ስካውት ማህበር አባላት የሆኑ የተለያዩ የአካል ጉዳተኞች ያላቸው ስካውቶች ቢኖሩም ማየት የተሳነው አባል ግን ኖሮት እንደማያውቅ የማህበሩ ምክትል ኮሚሽነር ወልጊኛ ሁንዴሳ ነግረውናል።