ቆይታ ከእጅ እንንሳ ሙዚቀኞች ጋር
በዚህ ባለንበት ወቅት ላይ እራስን ከኮሮና ቫይረስ ለመጠብቅ የሚረዱ መረጃዎች በብዛት እየወጡ ይገኛሉ፡፡ በኪነ፟ጥበብ ውስጥ ያሉ ባለሞያዎችም ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ እጅ እንንሳ የሚል ነጠላ ዜማ ለቀዋል፡፡ ሙዚቃው በአጭር ጊዜ ብዙ አድማጭንን እና አድናቆትን አግኝቷል፡፡ ኤደን ገረመው የዜማ እና የግጥም ጸሃፊውን አለማየሁ ደመቀን እና ሙዚቀኞቹን ሚሚ ሙሉቀን እና ትንሳኤ ጎበናን አነጋግራ ተከታዩን አሰናድታለች፡፡