<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>ኢትዮጵያ/ኤርትራ - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/3661</link>
        <description>Ethiopia and Eritrea related news and features</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>ኢትዮጵያ/ኤርትራ - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/3661</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Sat, 25 Apr 2026 04:17:20 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zy--yeqv$y" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት በዶ.ር ደብረ ጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን ወቀሰ</title>
            <description>የኢትዮጵያ መግሥት በዶ.ር ደብረ ጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን የፕሪቶሪያውን ስምምነት ጥሷል ማለቱን የሀገር ውስጥ ብዙኅን መገናኛ ዘገቡ።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት፣ በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ አዲስ አበባ ለሚገኙ ዲፕሎማቶች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በማብራሪያቸው፣ ለፕሪቶሪያው ስምምነት መተግበር የዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ድጋፍ መጠየቃቸውን የመንግሥት ብዙኅን መገናኛዎቹ ዘግበዋል፡፡
በዶ/ር ደብረ ጽዮን የሚመራው ቡድን ስምምነቱን ጥሷል መባሉን ማስተባበሉን በማስተባበል፣ በአንጻሩ ስምምነቱ የተጣሰው በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ ቡድን ነው ሲል በተደጋጋሚ ምላሽ መስጠቱ ይታወቃል፡፡ በሌላ በኩል የአፍሪካ ኅብረት፣ በክልሉ ባለው ውጥረት ተሳታፊ የሆኑ አካላት ራሳቸውን እንዲያቅቡና ችግሩ በውይይት እንዲፈታ ጠይቋል፡፡
በህወሓት የፖለቲካ አንጃዎች መካከል በተፈጠረው ሽኩቻ እጇ እንዳለበት በአቶ ጌታቸው የተከሰሰው የኤርትራ መንግሥት ክሱን አስተባብሏል።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት፣ በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ በአዲስ አበባ ለሚገኙ ዲፕሎማቶች ማብራሪያ መስጠታቸውን ጠቅሶ የዘገበው ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት፣ በውይይቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ራሱን ነጥሎ የወጣው የህወሓት አንጃ የፕሪቶሪያው ስምምነት ሙሉ ለሙሉ እንዳይተገበር እንቅፋት ኾኗል ማለታቸውን ዘግቧል።
በህወሓት አመራሮች መካከል አለመግባባቱ ከተካረረ ወዲህ በፌደራል መንግሥቱ በኩል እንዲህ ዐይነት አቋም ሲያዝ የመጀመሪያው ነው።
የትግራይ ክልል ሰሞናዊው ውጥረት ከተከሰተ በኋላ፣ በአዲስ አበባ ላሉ ዲፕሎማቶች ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ መንግሥት በተሰጠ በዚኽ ማብራሪያ ላይ፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም በክልሉ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት አስፈላጊውን እገዛ እንዲያደርግም ዶ/ር ጌዲዮን ጥሪ ማድረጋቸውን ከፎቶግራፎች እና ከቪዲዮ ጋራ የወጣው ዘገባ አመልክቷል፡፡
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳም፣ በክልሉ ላለው ውጥረት፣ “መፈንቅለ መንግሥት እያደረገ ነው” ያሉትን እና “አንድ የህወሓት አንጃ” ሲሉ የጠቀሱትን አካል ተጠያቂ በማድረግ በትላንትናው ዕለት ለጋዜጠኖች ከሰጡት ማብራሪያ ጋራ ተመሳሳይ ይዘት ያለው ማብራሪያ ለዲፕሎማቶች መስጠታቸው በዘገባው ተመልክቷል፡፡
በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው ህወሓት ምክትል ሊቀ መንበር የኾኑት አቶ ዐማኑኤል አሰፋ በበኩላቸው፣ ትላንት ማምሻውን ለብዙኀን መገናኛ በሰጡት መግለጫ፣ በአኹኑ ጊዜ በትግራይ ክልል እየተካሔደ ያለው፣ &quot;በወረዳዎች እና በከተሞች የሕገ መንግሥት ማስከበር እንጂ፣ መፈንቅለ መንግሥት ተብሎ እየተገለጸ ያለው ስሕተት ነው፤&quot; ሲሉ ክሱን ተከላክለዋል፡፡
“በትግራይ ክልል በአሁኑ ጊዜ አዲስ የተለየ ክስተት ሳይኖር በወሬ ግርግር እንደተፈጠረ እየተገለፀ ነው ያለው” ሲሉም ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል የአፍሪካ ኅብረት፣ በህወሓት ውስጥ የተፈጠረውን ሁኔታ በጥልቅ ስጋት በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
ኅብረቱ በመግለጫው፣ “በአሁኑ ወቅት እየታዩ ካሉት ሁኔታዎች በመነሳት ወገኖቹ በህወሀት እና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል ፕሪቶሪያ ላይ በተፈረመው ግጭቶችን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት የተካተቱትን ግዴታዎች እንዲያከብሩ እናበረታታለን ብሏል።
ስምምነቱን ማክበር በብዙ ፈተና የተገኘው ሰላም እንዲዘልቅ ብሎም ለዘላቂ ሰላም ግንባታ፥ ለዕርቅ እና ለልማት አመቺ ሁኔታ ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን አጽንዖት ሰጥተን እናሳስባለን ያለው የአፍሪካ ኅብረት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የገቧቸውን ቃሎች እንዲያከብሩ እና ሰላማዊ መፍትሄ እንዲገኝ በትብብር እንዲሰሩ እንማጸናለን ብሏል።
የአፍሪካ ኅብረት ለፕሪቶሪያ ስምምነት ተግባራዊነት የማያወላውል ድጋፉን በድጋሚ ያረጋግጣል፥ በዚህ ሂደትም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር አብሮነቱን ይቀጥላል ያለው መግለጫው ኅብረቱ በከፍተኛ ልዑክ አማካይነት በወገኖቹ መካከል ውይይት እና ትብብር የሚኖርበትን መንገድ ማመቻቸቱን ለመቀጠል ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ከፍተኛ አባል ሴናተር ጂን ሻሂን በኤክስ ገጽ ባሰፈሩት ጽሑፍ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል እየተባባሰ ያለው ውጥረት እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።
“ከግጭት እና አለመረጋጋት ይልቅ ለሰላም እና ለዲፕሎማሲ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል” ያሉት ሴናተር ሻሂን፣ “መሪዎቹ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነትን እንዲያከብሩ ጥሪ አቀርባለሁ” ብለዋል፥ አስከትለውም በአፍሪካ ቀንድ የሚፈጠር ግጭት “በቀጣናው የባሰ ስቃይ ከማስከተል ያለፈ ውጤት አይኖረውም” ብለዋል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ፣ “ከኤርትራ ጋር ግንኙነት እየፈጠሩ ያሉ አካላት አሉ” ሲሉ ወንጅለው ነበር፡፡
በሌላ በኩል የኤርትራ የማስታወቂያ አቶ የማነ ገብረ መስቀል ትላንት በኤክስ ላይ ባወጡት መግለጫ፣ “ኤርትራ በህወሓት የፖለቲካ አንጃዎች ውስጥ የተፈጠረውን የውስጥ ሽኩቻ የማባባስ ፍላጎት የላትም ፤ ይህ በትግራይ ህዝብ ላይ አላስፈላጊ ስቃይ ያስከትላል ብላ ታምናለች” ብለዋል።
በዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል በሚመራ ህወሓት ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ዐማኑኤል አሰፋም ትላንት በሰጡት መግለጫ፣ ከኤርትራ መንግስት ጋራ ሌላ አካልን ለመጉዳት ተብሎ የሚፈፀም ግንኙነት የለንም በማለት የአቶ ጌታቸውን ክስ ተከላክለዋል።
የኤርትራው ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ በትላንቱ የኤክስ መግለጫቸው “የኤርትራ ጦር በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል አለ” በሚል በተወሰኑ አካላት የሚሰነዘረው ተደጋጋሚ ክስ “ፍፁም ሀሰት እና ግጭት ለመቀስቀስ ምክንያት ለመፍጠር የሚደረግ ነው” ሲሉ ገልፀዋል፡፡
“ኤርትራ የፕሪቶሪያን የሰላም ስምምነት ለማፍረስ ምንም ፍላጎት የላትም። ይህ በመሰረቱ የኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ነው” ያሉት አቶ የማነ “በቀይ ባህር ዙሪያ በተለያዩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሃይሎች ሌት ተቀን የሚያወጧቸው ግጭት ቀስቃሽ መግለጫዎች ለአላስፈላጊ ውጥረት ምንጭ ሆነው ቀጥለዋል” በማለት ከሰዋል፡፡
በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እና የኤርትራን ክስ በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለአሁን አልተሳካም፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/tigray-tension-update/8011028.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/tigray-tension-update/8011028.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 21:59:39 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0cc21c8a-e1d4-4e12-b76c-5691b2b9e8b7_cx0_cy5_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያውያት ሴቶች ጥያቄ ምንድን ነው? - የአድማጭ ተመልካቾች አስተያየት</title>
            <description>መጋቢት፥ የዓለም አቀፍ ሴቶች ወር ነው። ሴቶች ትምህርትንና ሥራን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች እኩል ዕድል እንዲያገኙ ለማብቃት በመላ ዓለም የሚደረጉ ጥረቶች፦ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በጦርነት እና በሌሎችም ሰው ሠራሽ ምክንያቶች መጓተታቸውን፣ በሴቶች ላይ አተኩረው የሚሠሩ ተቋማት ያወጧቸው ሪፖርቶች ያሳያሉ። 
ዘንድሮም፣ ወርኃ መጋቢት(ማርች 8)፥ “ትግበራን ማፋጠን” በሚል መሪ ቃል በመላው ዓለም እየታሰበ ይገኛል። 
በዐዲስ አበባ የአሜሪካ ድምፅ ዘጋቢ ኬኔዲ አባተ፣ በርእሰ መዲናዪቱ ጎዳናዎች ላይ ተዘዋውሮ፤ ለመኾኑ የኢትዮጵያውያት ሴቶች ጥያቄ ምንድን ነው? የሴቶች እኩልነት እንዲሰፍን ምን ቢደረግ ይበጃል? በማለት ጠይቆ ያገኘውን ምላሽ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/women-day-voxpop/8010711.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/women-day-voxpop/8010711.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 17:29:27 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/196b6129-1211-4881-3514-08dd5c897904_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>&quot;በትግራይ መፈንቅለ መንግሥት እየተፈጸመ ነው&quot; ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ተናገሩ</title>
            <description>በትግራይ ክልል፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ቢሮዎች በየደረጃው በመስበር እና ማኅተሞችን በመንጠቅ መንግሥትን የማውረድ ሥራ እየተሠራ ነው፤ ሲሉ ፕሬዘደንቱ አቶ ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል።
በዐዲስ አበባ የሚገኙት አቶ ጌታቸው፣ ዛሬ ኀሙስ፣ መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም. ረፋድ፣ በሸራተን ዐዲስ ሆቴል ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ አኹን በክልሉ ያለው ኹኔታ፣ &quot;የፕሪቶርያውን ስምምነት የሚጥስና ከፍተኛ ግጭት የሚፈጥር ስለኾነ፣ የፌደራል መንግሥቱ ይህን የሚያስቆም ርምጃ መውሰድ አለበት፤” ብለዋል።
“በምክር ቤት ወይም በካቢኔ ደረጃ ተሰብስበን የፌዴራሉ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ ያቀረብነው ጥያቄ የለም፤” ያሉት አቶ ጌታቸው፣ በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት መሠረት፣ የፌደራል መንግሥቱ ከህወሓት ጋራ ያቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር የመታደግ ሓላፊነት እንዳለበት አመልክተዋል።
ይህ ማለት “ጦር አዝምቶ ጦርነት ይቀስቅስ ማለት አይደለም፤” ያሉት አቶ ጌታቸው፣ ነገር ግን፣ ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጋራ በመኾን፣ አኹን በክልሉ ባለው ኹኔታ ምክንያት ጦርነት እንዳይፈጠር የሚያስችሉ ርምጃዎችን መውሰድ የፌዴራል መንግሥት ኃላፊነት ነው፤” ሲሉ አስረድተዋል።
ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ፣ በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫቸው ከኤርትራ መንግሥት ጋራ ግንኙነት ያላቸው አመራሮች ይኖሩ እንደኾነ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ &quot;ግንኙነት ያላቸው የተወሰኑ ግን አደጋ መፍጠር የሚችሉ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ አመራሮች አሉ፤&quot; ሲሉ ወንጅለዋል፡፡
በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው ህወሓት ምክትል ሊቀ መንበር የኾኑት አቶ ዐማኑኤል አሰፋ በበኩላቸው፣ ዛሬ ማምሻውን ለብዙኀን መገናኛ በሰጡት መግለጫ፣ በአኹኑ ጊዜ በትግራይ ክልል እየተካሔደ ያለው፣ &quot;በወረዳዎች እና በከተሞች የሕገ መንግሥት ማስከበር እንጂ፣ መፈንቅለ መንግሥት ተብሎ እየተገለጸ ያለው ስሕተት ነው፤&quot; ሲሉ ክሱን ተከላክለዋል፡፡
ከኤርትራ መንግሥት ጋራ &quot;ግንኙነት አለ፤&quot; በሚል በአቶ ጌታቸው የቀረበውን ውንጀላ በተመለከተም፣ የኤርትራ መንግሥትን ጨምሮ ከማንኛውም የውጭ አካል ጋራ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ይኹን የፌደራል መንግሥቱን ለመጉዳት የተደረገ ግንኙነት የለም፤ ሲሉ አቶ ዐማኑኤል ምላሽ ሰጥተዋል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/getachew-s-presser-amanuels-reaction-/8010001.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/getachew-s-presser-amanuels-reaction-/8010001.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:53:52 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a0b29bb2-c45e-4a4e-082e-08dd5c8b1668_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር እንዲቆይ ፍርድ ቤት ፈቀደ</title>
            <description>ባለፈው ሰኞ ሌሊት፣ ከምትኖርበት ሕንፃ አምስተኛ ፎቅ ላይ ቁልቁል ወድቃ ሕይወቷ ካለፈው፣ ሞዴል እና የማስታወቂያ ባለሞያ ቀነኒ አዱኛ ሞት ጋራ በተያያዘ ተጠርጥሮ በቁጥጥር ሥር የሚገኘው እጮኛዋ አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ፣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር ቆይቶ ምርመራ እንዲቀጥል ፍርድ ቤት አዘዘ።
የዐዲስ አበባ ፖሊስ፣ ከቀነኒ ሞት ጋራ በዋና ወንጀል አድራጊነት የጠረጠረው አንዱዓለምን እንደኾነ በመግለጽ፣ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቆ የነበረ ሲኾን፣ ከጠበቃው ጋራ ፍርድ ቤት የቀረበው አንዱዓለም ደግሞ፣ የቀነኒ ሕይወት ያለፈው በአደጋ እንደኾነ በመግለጽ ከእስር እንዲፈታ አመልክቶ ነበር።
ሟች ቀነኒ አዱኛ ዋቆ፣ ሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ከሌሊቱ 10 ሰዓት ገደማ፣ አምስተኛ ወለል ላይ ከሚገኘው የቤቷ የማብሰያ ክፍል ቨረንዳ በኩል፣ ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ ኹኔታ ቁልቁል ወደ ምድር ወድቃ ለሕክምና ርዳታ ወደ ያኔት ሆስፒታል እየተወሰደች ባለችበት ወቅት ሕይወቷ ማለፉን፣ የዐዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ትላንት አስታውቆ ነበር።
የምርመራ መዝገቡን ለፍርድ ቤቱ ያቀረበው ፖሊስ፣ ሞዴል ቀነኒ፥ ሕይወቷ ባለፈበት ወቅት፣ ፍቅረኛዋ አርቲስት አንዱዓለም በቤት ውስጥ እንደነበር ጠቅሶ፣ የአስከሬን ምርመራ ውጤትን ጨምሮ የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎችን መርምሮ ለማቅረብ 14 ቀን የምርመራ ጊዜ ጠይቆ ነበር።
&quot;ለምርመራ የሚያበቃ በቂ ምክንያት የለም፤&quot; በሚል ተቃውሞ ማቅረባቸውን ለአሜሪካ ድምፅ የገለጹት፣ የአርቲስት አንዱዓለም ጎሣ ጠበቃ አቶ ሊባን አብዲ ሑሴን፣ የቀነኒ ሕይወት ያለፈው &quot;በአደጋ ነው&quot; የሚል ምላሽ መስጠታቸውን አስረድተዋል።
የግራ ቀኙን ክርክር ያደመጠው ፍርድ ቤቱ፣ የአስከሬን ምርመራ ውጤትን ጨምሮ የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎችን አጠናቅሮ እንዲያቀርብ፣ ለፖሊስ ተጨማሪ የ13 ቀናትን የጊዜ ቀጠሮ በመፍቀድ፣ ለመጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም. ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/andualem-gosa-court-/8009809.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/andualem-gosa-court-/8009809.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:29:03 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0c9fc9b2-79e6-4c5e-0eca-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሦስት አባላቱ መታሰራቸውን አስታወቀ</title>
            <description>የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት የተደረገውን የሕገ መንግሥት ማሻሻያ የተቃወሙትን አቶ ዮሐንስ ተሰማን ጨምሮ ሦስት አባላቱ እንደታሰሩበት አስታወቀ፡፡
የፓርቲው የውጭ እና ዓለም አቀፍ ዘርፍ ሓላፊ ዶር. መብራቱ ዓለሙ፣ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፣ የሕገ መንግሥት ማሻሻያውን በመቃወማቸው ታስረዋል የተባሉት አቶ ዮሐንስ ተሰማ፣ የክልሉ ምክር ቤት አባል እንደኾኑ ጠቅሰው፣ ያለመከሰስ መብታቸው ግን እንዳልተነሳ ገልጸዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ፣ ከክልላዊ መንግሥቱ አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/opposition-member-arrest-/8009806.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/opposition-member-arrest-/8009806.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:12:15 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ገ/ሚካኤል ገ/መድህን)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/99f407d2-515a-4873-0e9e-08dd5c8d307c_cx0_cy12_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተዘግቶ የቆየው የመቐለ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት በዶር. ደብረ ጽዮን ቡድን ቁጥጥር ሥር ዋለ</title>
            <description>      &quot;የመፈንቅለ መንግሥት ሒደት ቅጥያ ነው&quot; - የጊዜያዊ አስተዳደሩ ሹም
ከህወሓት አመራሮች ውዝግብ ጋራ በተያያዘ ላለፉት መቶ ቀናት በዝግ የቆየው የመቐለ ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት፣ ዛሬ ኀሙስ፣ በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል በሚመራው ቡድን ቁጥጥር ሥር ውሏል።
በጊዜያዊ አስተዳደሩ የከተማዋ ከንቲባ እንዲኾኑ የተሾሙት አቶ ብርሃነ ገብረ ኢየሱስ፣ &quot;ጽንፈኛ&quot; ሲሉ የጠሩት ቡድን በወታደራዊ አመራሮች ድጋፍ ጽሕፈት ቤቱን እንደተቆጣጠረ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል፤ &quot;የመፈንቅለ መንግሥት ሒደት ቅጥያ ነው፤&quot; ሲሉም ድርጊቱን ኮንነዋል።
በዶር. ደብረ ጽዮን ሊቀ መንበርነት በሚመራው የህወሓት ቡድን የመቐለ ከተማ ከንቲባ እንዲኾኑ ታጭተው በከተማዋ ምክር ቤት የተሾሙት ዶክተር ረዳኢ በርሀ በበኩላቸው፣ &quot;ወደ ጽሕፈት ቤቱ የገባነው በሰላማዊ መንገድ ነው፤&quot; ሲሉ ተናግረዋል።
ተቀማጭነታቸው በዐዲስ አበባ ከተማ የኾኑ የዩናይትድ ስቴትን ጨምሮ የ25 አገሮች ኤምባሲዎች፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እያገረሸ ያለውን ውጥረት በቅርበት እየተከታተሉት እንደሚገኙ ገልጸው፣ ችግሩ በውይይት እንዲፈታ ጠይቀዋል። 
ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ። 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/mekelle-mayor-take-over-/8009904.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/mekelle-mayor-take-over-/8009904.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 22:25:45 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/846c6708-ef34-447d-345c-08dd5c897904_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዶር. ደብረ ጽዮን ቡድን የመቐለ ከንቲባ ጽሕፈት ቤትን ተቆጣጠረ፤ አቶ ጌታቸው &quot;በትግራይ መፈንቅለ መንግሥት እየተካሔደ ነው” ብለዋል
</title>
            <description>ከመቶ ቀናት በላይ በዝግ የቆየው የመቐለ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽሕፈት ቤት፣ በዶር. ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል በሚመራው የህወሓት ቡድን በተሾሙት ከንቲባ ቁጥጥር ሥር ውሏል።
በዶር. ደብረ ጽዮን ሊቀ መንበርነት በሚመራው የህወሓት ቡድን በኩል ታጭተው በከተማዋ ምክር ቤት የተሾሙት ዶር. ረዳኢ በርሀ፣ ዛሬ ኀሙስ፣ መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም. በከንቲባ ጽሕፈት ቤት ውስጥ ገብተው ሥራ መጀመራቸውን ይፋ አድርገዋል። 
&quot;ወደ ጽሕፈት ቤቱ የገባነው በሰላማዊ መንገድ ነው፤&quot; ያሉት ዶር. ረዳኢ፣ &quot;የከንቲባውን ጽሕፈት ቤት ሲጠብቁ የነበሩ የከተማዋ ዓይደር ክፍለ ከተማ ፖሊሶች፣ በቦታው መቆየታቸው ትክክል እንዳልኾነ አምነው፣ በመነሣታቸው ነው የገባነው፤&quot; ሲሉ አስረድተዋል።
ከ100 ቀናት በላይ ተዘግቶ በቆየው ጽሕፈት ቤት፣ ሕዝባዊ አገልግሎቶችን መስጠት እንደሚጀምሩም ዶክተር ረዳኢ ገልጸዋል።
በተመሳሳይ፣ የመቐለ 104.4 ኤፍ ኤም ራድዮ ጣቢያ፣ በዶር. ረዳኢ በርሀ በተሾሙት አቶ ዘመንፈስ ቅዱስ ፍሥሓ እና የከተማው አመራሮች ቁጥጥር ሥር መዋሉ ተገልጿል።
የራድዮ ጣቢያውን በታጣቂዎች ታጅበው እንደተቆጣጠሩት፣ አንድ የጣቢያው ሠራተኛ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጿል። በጉዳዩ ላይ፣ ከአቶ ዘመንፈስ ቅዱስ ማብራርያ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው፣ “መፈንቅለ መንግሥት እየተፈጸመ ነው፤” ብለዋል፡፡ 
ፕሬዝደንቱ ዛሬ ኀሙስ፣ በዐዲስ አበባ ሸራተን ዐዲስ ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በአኹኑ ሰዓት ትግራይ ውስጥ እየተፈጠረ ያለው፣ “አንድ የሕወሓት አንጃ ደጋፊዎቼ ያላቸውን የተወሰኑ ከፍተኛ መኰንኖችን በመያዝ ማኅተም የመንጠቅና ሥራዎች እንዳይሠሩ የማድረግ ሥራ እየሠራ ነው፤” ብለዋል።
“ይህን ሥርዐት ለማስያዝ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ዕድል ተነፍጓል፤” ያሉት አቶ ጌታቸው፣ በዚኽ ሰዓት የፌዴራል መንግሥቱ “አግባብነት ያላቸውን ርምጃዎች መውሰድ አለበት፤” ብለዋል። ይህ ማለት ግን “ጦር አዝምቶ ጦርነት ይቀስቅስ ማለት አይደለም” ያሉት አቶ ጌታቸው፣ ነገር ግን፣ ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጋራ በመኾን፣ አሁን በክልሉ ባለው ኹኔታ ምክንያት ጦርነት እንዳይፈጠር የሚያስችሉ ርምጃዎችን መውሰድ የፌዴራል መንግሥት ኃላፊነት ነው፤” ሲሉ አመልክተዋል። 
“በምክር ቤት ደረጃ ተሰብስበን የፌዴራሉ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ ያቀረብነው ጥያቄ የለም፤” ካሉ በኋላ “ጥያቄውም ያስፈልገዋል የሚል እምነት የለኝም፡፡ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሠረት በጋራ ያቋቋምነውን ጊዜያዊ አስተዳደር መታደግ የፌዴራሉ መንግሥት ሓላፊነት ነው፤” ብለዋል።
በክልሉ የሚንቀሳቀሱት ዓረና ትግራይ፣ ባይቶና እና ወድብ ናፅነት ትግራይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በጋራ ባወጡት መግለጫ፣ ወታደራዊ ኀይል በመጠቀም የመንግሥት ሥልጣን ለመቆጣጠር የሚደረግ እንቅስቃሴን እንቃወማለን፤ ብለዋል።
ተቀማጭነታቸው በዐዲስ አበባ የኾኑ የዩናይትድ ስቴት ኤምባሲን ጨምሮ የ25 ሀገራት ኤምባሲዎች፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እያገረሸ ያለውን ውጥረት እየተከታተሉት እንደኾነ ጠቅሰው፣ የፕሪቶርያው ግጭትን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት፣ የጥይትን ድምፅ ያጠፋ በመኾኑ ገቢራዊነቱን እንደሚደግፉ ገልጸዋል። 
ዳግመኛ ወደ ግጭት መግባት አይገባም፤ ያሉት ኤምባሲዎቹ፣ ኹሉም ተቀናቃኝ ኀይሎች ውጥረቱን እንዲያረግቡና ወደ ውይይት እንዲገቡ ጠይቀዋል፤ ለዚኽም ድጋፋቸውን እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/mekelle-mayor-take-over-/8009438.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/mekelle-mayor-take-over-/8009438.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 17:40:01 +0300</pubDate>
            <category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/b3cd0b74-22b3-497a-33ef-08dd5c897904_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፌደራል መንግሥቱን ጣልቃ ገብነት ጠየቀ</title>
            <description>የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በትግራይ ክልል የተፈጠረውን ቀውስ ተከትሎ የፌደራል መንግሥቱን ጣልቃ ገብነት ጠየቀ። የክልሉ መንግሥት ባወጣው መግለጫ፣ “የፕሪቶሪያ ስምምነት ሲፈርስ እና የትግራይ ሕዝብ ወደ ዳግም እልቂት ሲገባ ዝም ብሎ ማየት አይገባውም” ብሏል። በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራ ህወሓት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ሦስተኛ ወገን ወደ ክልሉ እንዲገባ መጥራት ተቀባይነት የሌለው እና የፕሪቶርያው ስምምነት የሚጥስ ነው ብሏል።
በተያያዘ ዜና በክልሉ ደቡብ ምስራቃዊ ዞን ዓዲጉደም በተባለ ከተማ የፀጥታ ኃይሎች ወሰዱት በተባለ ርምጃ፣ አራት ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት እና በርካቶች ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን የዞኑ አስተዳደር አስታውቋል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በክልሉ ተፈጠረ ያለውን ቀውስና የፌደራል መንግሥቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ የጠየቀበትን መግለጫ ተከትሎ እስካሁን ከአዲስ አበባ በይፋ የተሰጠ ምላሽም ይሁን አስተያየት የለም።
የአሜሪካ ድምፅ ከመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት እና ከሌሎች የፌደራል መንግሥት አካላት ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ጥረትም አልተሳካም።
ከሰሜኑ ጦርነት መጠናቀቅና ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ባለፈው መጋቢት 2016 ዓ.ም ከትግራይ ክልል ከመጡ የተለያዩ የኅብረተሰብ ተወካዮች ጋራ የተወያዩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ክልሉን እንደገና ወደ ጦርነት ለመመለስ የሚሠሩ ያሏቸውንና በስም ያልጠቀሷቸውን አካላት በማንሳት የማሳሰቢያ መልዕክት ማስተላለፍቸው ይታወሳል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ira-calls-for-intervention/8008487.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ira-calls-for-intervention/8008487.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 22:10:05 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a65439be-f4b7-462b-8cc3-04cf369e70f6_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሳዑዲ አረቢያ በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን መመለስ ዳግም ተጀመረ</title>
            <description>ዛሬ በሦስት በረራዎች ከ1 ሺሕ በላይ ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ አረቢያ ተመልሰዋል
በሳዑዲ አረቢያ በእስር ቤት እና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በዘመቻ የማስመለስ ተግባር ሲካሔድ የአሁኑ ለ4ኛ ዙር እንደሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ገልጸዋል፡፡
ከሳዑዲ አረቢያ መንግሥት ጋራ በተደረሰ ስምምነት መሰረት የተጀመረው የአሁኑ ዜጎችን የማስመለስ ተግባር፣ በሳምንት ውስጥ በሦስት ቀናት ዘጠኝ በረራዎችን በማድረግ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል፡፡
ዛሬ የተመለሱ ዜጎች በአየር መንገድ አቀባበል ከተደረግላቸው በኋላ ቃለመጠይቅ ለማድረግ ሞክረን የነበረ ሲኾን፣ ከአስተባባሪዎቹ ሁኔታዎች ሊመቻቹልን ባለመቻሉ ፣ አስተያየታቸውን ማካተት አልቻልንም፡፡
ይኹን እንጂ፣ “ለሦስ ዓመት እና ከዚያም በላይ በሳዑዲ አረቢያ መታሰራቸውን እና ለተለያየ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተጋልጠው መቆየታቸውን” አንዳንድ ተመላሾች ከአውሮፕላን በሚወርዱበት ወቅት ነግረውናል፡፡
አሁንም በርካታ መሰል ችግር ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ እንደሚገኙም ገልፀዋል፡፡
የተለያዩ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች እና ሀገራት፣ ሰነድ የሌላቸው ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ አረቢያ እስከሞት የሚደርስ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየተፈፀመባቸው እንደሚገኝ በተለያዩ ጊዜያት መግለጻቸው ይታወቃል፡፡
ከእዚህ መካከል የሆነው ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ የሳዑዲ ድምበር ጠባቂዎች ከመጋቢት 2014 እስከ ሰኔ 2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ “የየመን እና የሳዑዲ ድንበርን ለማቋረጥ የሞከሩ በትንሹ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ገድለዋል” ማለቱ አይዘነጋም።


የቪኦኤ አማርኛን ዋትስአፕ ቻናል ይከተሉ  
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-returnees-arrive-home/8008477.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-returnees-arrive-home/8008477.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 22:09:27 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/25af83c4-25cf-489f-0d8f-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ያገለገሉ 800 ሠራተኞች መታገዳቸውን ገለጹ</title>
            <description>በማኅበር ተደራጅተው በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚሠሩ 800 የሚደርሱ ሠራተኞች ዩኒቨርሲቲውን የደሞዝ ጭማሪ በመጠየቃቸው ከሥራች መታገዳቸውን ለአሜሪካ ድምጽ ገለጹ።
የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የልማት እና የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንት ዶክተር ሳሙኤል ጅሎ፣ከሥራ የተቀነሰ ሠራተኛ የለም ሲሉ ከአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል።
በሕጉ አግባብ ዩኒቨርሲቲው ጭማሪ፣ ለቋሚ ሠራተኞች እንጂ ለኮንትራት ሠራተኞች እንደማያደርግ ምክትል ፕሬዝደንቱ ተናግረዋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/hu-employees-suspension-/8008176.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/hu-employees-suspension-/8008176.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 18:57:31 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ዮናታን ዘብዴዎስ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a469da5d-eef1-4716-32c8-08dd5c897904_cx0_cy18_cw0_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በቀነኒ አዱኛን አሟሟት ዙሪያ  ፖሊስ ባለቤቷን ድምፃዊ አንዷለምን አስሮ እየመረመረ መኾኑን አስታወቀ</title>
            <description>በኦሮምኛ ቋንቋ ዘፈኑ የሚታወቀው አንዷለም ጎሳ ባለቤት፣ ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ ዋቆ ፣ ሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 10 ሰዓት  አካባቢ ከቤቷ ማብሰያ ክፍል በኩል ካለው በረንዳ 5ኛ ፎቅ ላይ ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ወድቃ ለሕክምና ርዳታ ወደ ያኔት ሆስፒታል እየተወሰደች ባለበት ወቅት ሕይወቷ ማለፉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዛሬ አስታውቋል፡፡ 

ክስተቱ በተፈጸመበት ወቅት በቤት ውስጥ ነበረ ያለውን ባለቤቷን፣ ድምፃዊ አንዷለም ጎሳን  በቁጥጥር ስር አውሎ  እየመረመረ መሆኑንም ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል። 
ለቤተሰቡ ቅርበት ያላቸውን ምንጮች፣ ጥንዶቹ በሕግ ትዳር አለመመስረታቸውን ጠቅሰው የፍቅር አጋር መኾናቸውን ትላንት ለአሜሪካ ድምጽ የገለጹ ሲኾን፣ በአንድ ቤት ውስጥ ሦስት ዓመት አብረው እንደኖሩንም ነግረውናል። ነገር ግን ፖሊስ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አርቲስ አንዷለም ጎሳ የቀነኒ አዱኛ ባለቤት መኾኑን ጠቅሷል። 
ፖሊስ በፌስ ቡክ ገጹ ላይ ባወጣው በዚኽ መግለጫ፣ የምርመራ ቡድን በማዋቀርና ቦታው ድረስ በመሄድ ለምርመራ ሥራ የሚጠቅሙት ተገቢ መረጃዎች ማሰባሰቡን ገልጿል።
የሟችንም አስከሬን ወደ ዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታል ለተጨማሪ ምርመራ መላኩን እማ  የመጨረሻውን የምርመራ ውጤትም በቀጣይ ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።  
ምዕራብ ሐረርጌ ውስጥ የተወለደችው ቀነኒ፣ ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ ነበረች። የባህላዊ አልባሳትን በመልበስ በተለይም በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በይበልጥ ትታወቅ ነበር። 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8007944.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8007944.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 16:03:53 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9cb4d574-cdb5-4c69-0d02-08dd5c8d307c_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የወጣቷ ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ አሟሟት በመጣራት ላይ መኾኑን ፖሊስ አስታወቀ</title>
            <description>ትላንት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም. በድንገት ሕይወቷ ያለፈው ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ ቀነኒ አዱኛ አሟሟት እየተጣራ መኾኑን ፖሊስ ጠቆመ
በኦሮምኛ ቋንቋ ዘፈኑ የሚታወቀው አንዷለም ጎሳ የፍቅር አጋር እና ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ ቀነኒ አዱኛ፣ ትላንት ሌሊት በአዲስ አበባ ከተማ ፣ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው በድንገት ሕይወቷ ማለፉን ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉና ለቤተሰብ ቅርብ የኾኑ ምንጮች ተናገሩ። 
ምስራቅ ሐረርጌ ውስጥ የተወለደችው ቀነኒ እና ድምፃዊ አንዷለም መኖሪያ ቤታቸው ህንጻ ላይ እንደሚገኝና፣ &quot;ከአምስተኛ ፎቅ ራሷን ወርውራ&quot; ሕይወቷ ማለፉን እኚኽ ለቤተሰቡ ቅርብ የኾኑ ምንጭ ገልጸዋል። ነገር ግን አሟሟቷን በተመለከተ ቪኦኤ ከፖሊስም ኾነ ለሌላ ገለልተኛ ምንጭ አላረጋገጠም። 
የባህላዊ አልባሳትን በመልበስ በተለይም በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በይበልጥ የምትታወቀው ቀነኒ፣ ከታዋቂው አንዷለም ጎሳ ጋራ ለሦስት ዓመታት በአንድ ቤት ይኖሩ የነበሩ የፍቅር አጋር መኾናቸውን እኚኹ ግለሰብ ነግረውናል።
አርቲስት አንዷለምን ፖሊስ ለጥያቄ ፈልጎ እንደወሰደውና ይኽ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ፣ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር እንደሚገኝ ምንጫችን ነግረውናል።
በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን፣ የጠየቅናቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ፣ በጉዳዩ ላይ መረጃ ለመስጠት ጊዜው ገና መኾኑን ተናግረዋል።
ማምሻውን ያገኘናቸው አንድ የአዲስ አበባ ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ባልደረባ፣ ፖሊስ በጉዳዩ ላይ ምርመራ እያደረገ መኾኑን ከመግለጽ ውጭ ምንም መረጃ እንደማይሰጡን ነግረውናል።
የወጣት ቀነኒ አዱኛ አስከሬን ዛሬ ጠዋት ዳግማዊ በሚኒልክ ሆስፒታል የአስከሬን ምርመራ ከተደረገለት በኋላ ዛሬ ከሰዓት፣ 9 ሰዓት አካባቢ ሱሉልታ ወደሚገኘው እህቷ ቤት እንደተወሰደ ምንጩ ለቪኦኤ ተናግረዋል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/keneni-adugna-killing/8007280.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/keneni-adugna-killing/8007280.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 23:56:45 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/67e17927-d557-46f5-0bee-08dd5c8d307c_cx0_cy35_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የአውሮፓ ኅብረት በትግራይ ያለው ውጥረት እንደሚያሳስበው ገለፀ</title>
            <description>በትግራይ ክልል ያለው ውጥረት በንግግር እንዲፈታ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት አምባሳደር ጠይቀዋል።
አምባሳደሯ ሶፊ ፍሮም፣ በኅብረቱ እና በኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያ ዛሬ መግለጫ በሰጡበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ ለሰብአዊ መብቶች መሻሻልም መሥራት እንዳለባት ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኤመንስበርገር ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 2 በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮችን አንስተዋል፡፡
አምባሳደሯ፣ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ኅብረት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበትን 50ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በሰጡት መግለጫ ላይ፣ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶችን እና ውጥረቶችን በተመለከተ ተጠይቀው መልስ ሰጥተዋል፡፡
በዋናነት፣ በፕሪቶሪያው ግጭትን በዘላቂነት የማቆም የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ግምገማ እና ከህወሓት ሕጋዊ ቁመና ጋራ በተገናኘ ያለውን አለመግባባት ተከትሎ በትግራይ ክልል ያለው ውጥረት የአውሮፓ ኅብረትን እንደሚያሳስብ አምባሳደሯ ገልፀዋል፡፡
በክልሉ ያለው ውጥረት እንዲሁም በአማራ ክልል የቀጠለው ግጭት ሰላማዊ መፍትሔ እንዲያገኝም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/eu-in-ethiopia-concerned-of-tigray-tension/8007132.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/eu-in-ethiopia-concerned-of-tigray-tension/8007132.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 22:02:38 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/1fc8b462-7018-4b5d-05c3-08dd5c8b1668_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የህወሓት የዓዲግራት ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ውዝግብና የጄነራሎች እግድ</title>
            <description>የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አመራሮች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ተካሮ፣ ዛሬ በዓዲግራት ከተማ የከንቲባ ጽሕፈት ቤት ይገባኛል ጥያቄ ውዝግብ መፍጠሩ ተገለጸ።
በዶ.ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው የህወሓት ቡድን፣ ለዓዲግራት ከተማ የሾማቸውን ከንቲባ፣ ጽሕፈት ቤቱን በኃይል በመስበር አስገብቷል ሲል ፣ የትግራይ ምስራቃዊ ዞን የፀጥታ ሓላፊ አቶ ኪዱ ገብረ ፃድቅ ለአሜሪካ ድምፅ ገለፁ።
በዛሬው ዕለት ከንቲባው ጽሕፈት ቤት ገቡ የተባሉት፣ አቶ ረዳኢ ገብረ እግዚአብሔር፣ “ወደ ጽሕፈት ቤቱ በር ሰብረን አልገባንም፣ ህዝብ በምክርቤት የተመረጠ ከንቲባ ይግባ ብሎ በሰልፍ ስለመጣ ነው ወደ ፅሕፈት ቤት የገባነው ብለዋል።
በሌላ ዜና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት፣አቶ ጌታቸው ረዳ ሦስት የትግራይ ሠራዊት ከፍተኛ አዛዦችን አገዱ።
በትላንትናው ዕለት በአቶ ጌታቸው ረዳ ፊርማ የተጻፈ ደብዳቤ፣ ሜጀር ጄነራል ዮሐንስ ወ/ጊዮርጊሰ፣ ሜጀር ጄነራል ማሾ በየነ እና ብርጋዴር ጄነራል ምግበይ ኅይለ በጊዜያዊነት ታግደዋል በማለት ያስረዳል።
ውሳኔው በደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የህወሓት ቡድን እና የክልሉ የፀጥታ እና ሰላም ቢሮ ተቃውመውታል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/tigray-political-tension/8007137.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/tigray-political-tension/8007137.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 22:00:04 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/3890ac4c-6bb3-47d0-3210-08dd5c897904_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የምስጋና እና አንድነት ኢፍጣር በአሜሪካ</title>
            <description>ከዋሺንግተን ዲሲ እና ከአቅራቢያው ግዛቶች የተሰባሰቡ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዓመታዊውን የ&quot;ምስጋና እና አንድነት ኢፍጣር&quot;  በቨርጂኒያ አካሒደዋል። 
የእስልምና እምነት ተከታዮች በአንድ ስፍራ ተገናኝተው  ማዕድ በተጋሩበት ምሽት፣ ለማኅበረሰቡ ለሚበጁ ግንባታዎች የሚውል ድጋፍም ተሰባስቦበታል። የረመዳን ጾምን ድባብ የሚያጎሉ መልዕክቶች ተላልፈውበታል ፣ ኃይማኖታዊ ሥርዓቶችም ተከናውነውበታል።
በአናንዴል ቨርጂኒያ የተከናወነውን ሥነ ስርዐት የተከታተለው ሀብታሙ ስዩም በአጭሩ ያስቃኘናል። 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethio-american-muslim-community-annual-iftar/8007060.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethio-american-muslim-community-annual-iftar/8007060.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 21:42:04 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሀብታሙ ስዩም)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/f038ae8b-91d2-481d-05b2-08dd5c8b1668_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በራያ አላማጣ ጥሙጋ ቀበሌ አንድ የቤተክርስቲያን መምሕርና አራት ተማሪዎች ተገደሉ</title>
            <description>በራያ ኣላማጣ ጥሙጋ በተባለ ቀበሌ ውስጥ ባለፈው አርብ፣ በአንድ ቤተ ክርስትያን መምህር እና ተማሪዎች በተፈፀመ ጥቃት አምስት ሰዎች መገደላቸውን የወረዳው አስተዳዳሪ ገለጹ።


የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ሕሉፍ፣ በሌሎች አራት ሰዎች ላይም በጥቃቱ ጉዳት መስረሱን ተናግረዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።




 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8005708.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8005708.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 22:04:48 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/BF762538-4979-41D0-95A7-E875E7FFE725_cx0_cy9_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title> በኮሬ ዞን ታጣቂዎች ፈፀሙት በተባለ ጥቃት ሁለት ሲቪሎች መገደላቸው ተገለጸ</title>
            <description>በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ “በኦሮሞ ነፃነት ታጣቂዎች” ትላንት ተፈፀመ በተባለ ጥቃት ሁለት ሰዎች ሲሞቱ አንዲት ነዋሪ መቁሰሏን ነዋሪዎችና ቤተሰቦቻቸው ለአሜሪካ ድምፅ ገለጹ።


የኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ ሰላም እና ጸጥታ ጽሕፈት ቤት ሁለት ሲቪል ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል ምእራብ ጉጂ ዞን ወሰን በተሻገሩ ታጣቂዎች ስለመገደላቸው አረጋግጠዋል።


የኬሌ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ሸሪፍ አደም፣ በጥይት የቆሰሉ ሁለት ሰዎች ለሕክምና ሆስፒታላቸው ገብተው እንደነበርና ለተሻለ ሕክምና ወደ ሌላ ቦታ ከተላኩ በኋላ ሕይወታቸው ማለፉን ተናግረዋል።


የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ቃልአቀባይ አቶ ጅረኛ ጉዴታ፣ ታጣቂዎቻቸውን ሲቪሎችን ዒላማ እንደማያደርጉ ገልጸው አስተባብለዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡




 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8005698.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8005698.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 22:00:52 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ዮናታን ዘብዴዎስ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/A0B34EB6-FDEB-47C1-A3EF-9BEC2160F931_cx0_cy8_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሚያንማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ተመለሱ</title>
            <description>በሚያናማር በእገታ ሥር ቆይተው ወደ ታይላንድ ከተሻገሩ 133 ኢትዮጵያ መካከል 32ቱ ዛሬ ወደ አገራቸው መመለሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።


በዛሬው ዕለት ከገቡት መካከል አስተያየቱን የሰጠን አንድ ወጣት፣ በምያንማር ለዐሥር ወራት አስከፊ ጊዜ ማሳለፉን ተናግሯል።


ደርሶብኛል ካላቸው አካላዊ የመብት ጥሰቶች በተጨማሪ፣ በሥነ ልቡና ክፉኛ በመጎዳቱ ምክንያት ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀን ወጣቱ፣ ምንም እንኳን የእርሱ ወደ አገሩ መግባት ቢያስደስተውም፣ ነገር ግን ደስታው ምሉዕ እንዳለሆነ ይገልጻል፡


ከሚያንማር ወደ ታይላንድ የመግባት ዕድል ካገኙት 138 ኢትዮጵያውያን ውስጥ አምስቱ ከዚህ ቀደም ለብዙኅን መገናኛ በሰጡት አስተያየት ምክንያት በሚያንማር ኢሚግሬሽን ትፈለጋላችሁ ተብለው መወሰዳቸውን ከተመላሾቹ መካከል ያነጋገርነው ወጣት አመልክቷል፡፡ እነርሱን ጨምሮ መንግሥት፣ በታይላንድ በካምፕ ውስጥ የሚገኙትን እና በሚያንማር በችግር ላይ ያሉትን ኢትዮጵያውያን ለመታደግ “ከፍተኛ ጥረት ሊያደርግ ይገባል” ሲል ተማፅኗል፡፡




በጉዳዩ ላይ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት፣ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው የእጅ ስልክ ላይ ደውለን ባለመመለሳቸው ለአሁን አልተሳካም፡፡


ሆኖም፣ በዛሬው መገልጫው “43 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ምሽት ወደ አገር ቤት ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል” ያለው ሚኒስቴሩ፣ ቀሪዎቹን በታይላንድ ማቆያ የሚገኙ 58 ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው ለመመለስም በሕንድ ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲው ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡


በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ኢትዮጵያውያንን ወደ ታይላንድ በማሻገር ወደ አገራቸው ለመመለስ ደግሞ፣ ጃፓን በሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጥረት እያደረገ ነው ብሏል፡፡


በታይላንድ ጥሩ ክፍያ የሚያስገኝ ሥራ ትቀጠራላችሁ በሚል፣ በሕገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ተታለው በተለያዩ ጊዜያት ወደ አገሪቱ ከሄዱ በኋላ ማረፊያቸው ሚያንማር


የኾነ ኢትዮጵያውያን ቁጥር በይፋ ባይታወቅም በሺሕዎች እንደሚቆጠር ከተለያዩ ምንጮች የሚገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡


ከነዚህም አብዛኛው፣ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ማጭበርበር (ስካሚንግ) ወንጀል በሚፈጽሙ በሕገወጥ የተደራጁ ቡድኖች ቁጥር ስር ሆነው፣ በአስገዳጅ ሁኔታ በዚሁ ተግባር ላይ እንዲሰማሩ የተደረጉ ናቸው፡፡


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8005647.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8005647.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 21:37:25 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/4794d523-6d51-44be-0aaf-08dd5c8d307c_cx0_cy15_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማርች 8ትን በሴቶች ብቻ በሚደረጉ በረራዎች እያከበረ ነው</title>
            <description>ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን በተለያዩ ሥነ ሥርዐቶች ያከበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከትናንት የካቲት 28 ቀን 2017 አንስቶ በሴቶች ብቻ የሚመሩ ስድስት በረራዎችን ወደተለያዩ መዳረሻዎች ማድረግ ጀምሯል።


የበረራ ፕሮግራሙ ሴት ሞያተኞችን በዓለምአቀፍ አቪየሺን ኢንዱስትሪ ላይ እያሳረፉ ያለው ደማቅ አሻራ ጎልቶ እንዳታይ የሚያደርግ ነው ሲሉ የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ኃላፊ ለማ ያዴቻ ተናግረዋል ።


አየር መንገዱ፣ በሴቶች ብቻ የሚመሩ በረራዎቹን የሚያደርገው ወደ አቴንስ ፣ሳኦ ፖሎ፣ኒው ደልሂ፣ዊንድሆክ፣ዱባይና ባሕርዳር መኾኑን አስታውቋል ።


በሥነ ሥርዐቱ ላይ የተናገሩት የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ኃላፊ ለማ ያዴቻ፣ ሰድስቱ በረራዎች ከአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በሴቶች የሚመሩ መኾናቸውን አስታውቀዋል።


በረራዎቹ የአየር መንገዱን ሴት ሠራተኞች አስተዋጽኦ እንደሚያስተዋውቁም ጠቅሰዋል ።


በኹሉሞ ዘርፎች እየታያ ነው ያሉትን የሴት ሞያተኞች ተሳትፎ ያብራሩት አቶ ለማ፣ ይሄም የተቋቋሙ ጥንካሬ ማሳያ ነው ሲሉ ተናግረዋል።


በተለምዶ የወንዶች ተሳትፎ ልቆ በሚታይበት የአቪየሺን ዘርፍ ውስጥ የሴቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መኾኑን የገለፁት ኃላፊው አየር መንገዱ ሚናቸውን ይበልጥ ለማሳደግ እየሠራ መኾኑንም ጠቅሰዋል።


በረራዎቹ ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን አጉልቶ ለማሳየትና አጋርነትን ለመግለጽ ጭምር የተካሄዱ መኾናቸውንም ተናግረዋል።


ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን (ማርች 8) ዘንድሮ እየተከበረ ያለው &quot;መብት እኩልነትና አቅም መጎልበት ለሴቶች በሙሉ&quot; በሚል መሪ ቃል ነው።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8003762.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8003762.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 08 Mar 2025 21:44:22 +0300</pubDate>
            <category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/fee44d30-c92f-4292-0952-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በየመንና ጅቡቲ ጀልባዎች ሰጥመው ፍልሰተኞች መሞታቸውንና በርካቶች የደረሱበት አለመታወቁን ተመድ አስታወቀ </title>
            <description>የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፍልሰተኞች ኤጀንሲ እንደገለፀው በየመንና ጅቡቲ የባህር ዳርቻ አራት የፍልሰተኞች ጀልባዎች ሰጥመው ሁለት ሰዎች ሲሞቱ 186 የሚሆኑት ደግሞ የደረሱበት አልታወቀም።


የዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) ቃል አቀባይ ታሚም ኤሊየን እንዳሉት ሁለት ጀልባዎች በየመን ባህር ላይ የሰጠሙት ሀሙስ ምሽት ሲሆን የጠፉት 181 ፍልሰተኞችና አምስት የየመን የጀልባው ሰራተኞች መሆናቸውን ለአሶሼትድ ፕሬስ ተናግረዋል። ሁለት የጀልባው ሰራተኞችን ማትረፍ ተችሏል ብለዋል፡፡


ሌሎች ሁለት ጀልባዎች ደግሞ በትንሿ አፍሪካዊቷ ሀገር ጅቡቲ በተመሳሳይ ሰዓት ላይ ሰጥመዋል ሲሉ ተናግረዋል። የሁለት ፍልሰተኞች አስከሬን የተገኘ ሲሆን በጀልባው ውስጥ የነበሩ ሌሎች ሰዎችንም ማትረፍ መቻሉን ገልጸዋል፡፡


በደቡብ ምእራብ የመን ታይዝ ግዛት በዱባብ ወረዳ የተገለበጠችው ሶስተኛዋ ጀልባ 31 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችና ሶስት የመናውያን ሰራተኞችን አሳፍራ እንደነበረ ተናግረዋል፡፡


አራተኛዋ ጀልባ የሰጠመችው ደግሞ በዚሁ አካባቢ አቅራቢያ ወደሚገኘው የአቢያን ግዛት አህዋር ወረዳ ሲሆን 150 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችንና አራት ሰራተኞችን አሳፋራ የነበረች ናት፡፡


ባለፉት አስርት አመታት ከአፍሪካ ቀንድ ወደ የመን በሚወስደው በዚህ የፍልሰተኞች የባህር ጉዞ ሰጥመው መሞታቸው የተረጋገጡ 693 ሰዎችን ጨምሮ ቢያንስ 2ሽህ 82 ፍልሰተኞች ደብዛቸው ጠፍቷል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un-says-186-missing-and-at-least-2-dead-after-migrant-boats-capsize-off-yemen-and-djibouti-/8003609.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un-says-186-missing-and-at-least-2-dead-after-migrant-boats-capsize-off-yemen-and-djibouti-/8003609.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 08 Mar 2025 18:01:12 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/47136772-2e26-4d42-85e6-9a1f132ed136_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>