<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>ኢትዮጵያ - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/3661</link>
        <description>Ethiopia related news and features</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>ኢትዮጵያ - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/3661</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2021 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Thu, 13 May 2021 00:43:40 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zy--yeqv$y" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>ዘሚ የኑስ በኮቪድ-19 አረፉ</title>
            <description>በእንግሊዝኛ ኦቲዝም ተብሎ ለሚጠራው የአእምሮ ሥራ ሂደት መዛባት ችግር ተጋላጭ ለሆኑ ልጆች ተሟጋችነታቸው እና ባደረጉትም ድጋፍ እጅግ ታዋቂ የሆኑት ወይዘሮ ዘሚ የኑስ በኮቪድ-19 ሳቢያ በዛሬው ዕለት ህይወታቸው ማለፉ ተዘግቧል።


የጆይ ኦቲዝም ማዕከል እንዲሁም የኒያ ፋውንዴሽን መስራች እና ሥራ አስኪያጅዋ ወይዘሮ ዘሚ የኑስ በአዲስ አበባ ሚሊኒየም የኮቪድ-19 ጽኑ ህክምና ማዕከል ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ማረፋቸው ታውቋል።


 ወ/ሮ ዘኒ የአዕምሮ ዕድገት ዝግመት እክል ተጋላጭ ከሆነው ወንድ ልጃቸውን በመንከባከብ ባገኙት ዕውቀት እና ተመክሮ ህብረተሰቡም በጥልቀት ግንዛቤ እንዲኖረው እና ለተመሳሳይ ችግር የተጋለጡ ሌሎች ልጆችም ድጋፍ እንዲያገኙ ለአያሌ ዓመታት በትጋት ሲሰሩ ኖረዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5886869.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5886869.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 May 2021 23:46:50 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5886869.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/C4BA7A75-B992-430D-8EA7-104CF09CEE98_cx0_cy4_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፌልትማን ኢትዮጵያ ናቸው</title>
            <description>የአውሮፓ ህብረት ለምርጫው የባለሞያዎች ቡድን ይልካል።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5886857.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5886857.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 May 2021 23:39:37 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ሀብታሙ ስዩም)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5886857.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/75EFCA55-7709-4E4B-8A3C-AA84B4C6CE51_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አሜሪካ ኢትዮጵያ ለምርጫው ሜዳውን ማመቻቸት ይኖርባታል አለች</title>
            <description>ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ የሚካሄደውን የዴሞክራሲ ሂደት አጥብቃ የምትደግፍ ሲሆን፣ እኤአ ሰኔ 5 የሚካሄደው ምርጫ “ነጻ ፍትሃዊና ተአማኒ ሊሆን የሚችለው ለመራጮች የተመቻቸ ሁኔታ ሲፈጠር ብቻ መሆኑን&quot; አስታውቃለች፡፡


በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ትናንት የተሰጠው መግለጫ የወጣው በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል ያለው ሰብአዊ ቀውስና ግጭት እየተካሄደ ባለበት ሁኔታ ውስጥ ነው፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ምኒስቴር አንተኒ ብሊንከንም ኢትዮጵያና ኤርትራ የኤርትራ ወታደሮች ከትግራይ “አሁኑኑ፣ ሙሉ ለሙሉ፣ ሊረጋገጥ በሚችል መልኩ” ለቀው እንዲወጡ ከዚህ ቀደም በሰጡት መግለጫ ብርቱ ግፊት አድርገዋል፡፡


የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባለፈው መጋቢት ወር ኤርትራ ከትግራይ ክልል ኃይሎችዋን ለማስወጣት መስማማቷን ገልጻ ነበር፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይም ወደ ኤርትራ በማምራት ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ተገናኝተው ኤርትራ ለቃ እንደምትወጣ ያረጋገጠችላቸው መሆኑን ያስታወቁ ቢሆንም የዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣናት ግን እስከዛሬ ድረስ ኤርትራ ለቃ ስለመውጣቷ ምንም ማረጋጋጫ አለመኖሩን ተናግረዋል፡፡ 




መራጮች ምዝገባ ላይ ችግር በመኖሩ ፣ ኢትዮጵያ እኤአ ሰኔ 5 ለምታደርገው ጠቅላላ ምርጫ ለመዘጋጀት እየተጣጣረች ነው፡፡ ካለፈው ነሀሴ ጀምሮም በኮቪድ 19 የተነሳ ጠቅላላው ምርጫ ሳይካሄድ መዘግየቱ ይታወቃል፡፡ የአዲስ አበባና ድሬዳዋ አስተዳደሮችም ምርጫውን ለማካሄድ ያቀዱት እኤአ ሰኔ 12 መሆኑን ተመልክቷል፡፡


የውጭ ጉዳይ ምኒስቴር ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስ ትናንት ሰኞ በሰጡት መግለጫቸው ላይ ፣ ምርጫው የሚካሄደበት ምቹ ሁኔታ ከተሟላ የኢትዮጵያ መንግሥት የመሰብሰብና የንግግር ነጻነትን መፍቀድ፣ የፖለቲካ ተሳትፎንና እንዲሁም ሰዎች ኢንተርኔትና የመረጃ አገልግሎትን እንዲያገኙ ማድረግ ይኖርበታል” ብለዋል፡፡


አያይዘውም “የፖለቲካ ፓርቲዎችም ሁከትና ጥቃትን ማበረታት እንደሌለባቸው እናውቃለን፣ የጸጥታ አስከባሪ ኃይሎችም የኃይል እምርጃዎችና መውሰድና በተቃዋሚዎች ላይ የማስፈራሪያ ስልቶችን መጠቀም የለባቸውም” ብለዋል፡፡ ቃል አቀባዩ ከቪኦኤ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ


“ከዓለም አቀፍ አጋሮቻችን ጋር ምርጫውን ተከትሎ ሁከትና ጥቃትን ለማስወገድ በማህበረሰቡ መካከል መነጋገር እንዲኖር እናበረታታለን፡፡” ብለዋል፡፡


ይሁን እንጂ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሁን ባለው ሁኔታ ምርጫው ሊካሄድ ይችላል ብሎ ስለማመን አለማመኑ የገለጸው ነገር የለም፡፡


የኢትዮጵያ የቀድሞ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር የነበሩት ዴቪድ ሽን ለቪኦኤ እንደተናገሩት &quot;በትግራይ ክልል ምርጫውን ለማካሄድ አይቻልም፡፡ ከትግራይም ውጭ ኢትዮጵያ ውስጥ “ የሰኔ አምስቱ ምርጫ የሚያዋጣ ስለመሆኑ የሚያሳስቡ አንዳንድ ተጨባጭ ስጋቶች አሉ፡፡” ብለዋል፡፡


የሚታዩ አለመረጋጋቶችና በውጭ ታዛቢዎች ላይ የተጣሉ ገደቦች የምርጫው ሂደት ላይ አንዳንድ ጥያቄዎችን እንዲያነሱ አድርገዋል፡፡ እኤአ ግንቦት 3 የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ተወካይ የሆኑት ጆሴፍ ቦረል በሰጡት መግለጫ “ቁልፍ በሆኑ ጉዳዮች ላይ” ስምምነት ባለመደረሱና “አስፈላጊ ሁኔታዎች ያልተሟሉ በመሆናቸው ወደ ኢትዮጵያ የሚሄዱት የምርጫ ታዛቢዎችን የመላኩ እቅድ የተሰረዘ መሆኑን” አስታወቀው ነበር፡፡


ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ የአውሮፓ ህብረት 6 ታዛቢዎችን ለመላክ መስማማቱን አስታውቀዋል፡፡


ትናንት ሰኞ የዩናይትድ ሴትትስ ከሁለቱም የዴሞክራትና የሪፐብሊካን ፓርቲ ወገኖች የሆኑት የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት ደግሞ በጋራ ባወጡት መግለጫ ትግራይ ውስጥ ያሉ የኤርትራ ኃይሎች ጉዳይ አሁንም እጅግ ያሳሰባቸው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡


በዩናይትድ ስቴትስ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ሊቀመንበር ማይክ መካውል ስለዚሁ ሲናገሩ


፣“ግጭትና ጠበኝነትን አስወግዶ ሁሉን አሳታፊ ወደ ሆነው የፖለቲካ ንግግር ሊያመጣ የሚችለው ወታደራዊ እርምጃ አይደለም፡፡ አሁንም ትግራይ ውስጥ ያሉት የኤርትራ ወታደሮች በክልሉ የሚፈጽሙ የሰአብዊ መብት ጥሰት ግጭቱን ለማስወገድ ትልቁ እንቅፋት እንደሆነ ቀጥሏል&quot; ብለዋል፡፡፡፡


ዩናይትድ ስቴትስ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግሥት፣ በትግራይ የሚደረገውን ግፍ እንዲቆም እንዲያደርጉ ጫና ለማሳደር፣ ከሰአብአዊ ድጋፍ ውጭ ያለውን እርዳታ ማቋረጧን የምትቀጥልበት መሆኑም ተመልክቷል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግን ለአገሪቱ የሚሰጠውን የሰብአዊ እርዳታ መሰጠቱን የሚቀጥልበት መሆኑ አስታውቋል፡፡፡፡


የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፕራይስ ይህንኑ ሲገልጹ


 “ ለኢትዮጵያ እርዳታውን ለመስጠት ስናስብ፣ በዚያ አስቸጋሪ መከራ ውስጥ በሚገኘው የትግራይ ህዝብ ላይ ሌላ ተጨማሪ ጫና የሚያሳድር ነገር ማድረግ አንፈልግም፡፡ እንዲያውም ወደፊት የበለጠ ልንግዛቸው የምንችልበት መንገድ መኖሩን ማረጋገጥ እንፈልጋለን፡፡&quot; ብለዋል፡፡


በቅርቡ ለንደን ውስጥ የተገናኙት የቡድን 7 የበለጸጉ አገር ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች ከተነጋገሩባቸው ጉዳዮች አንዱ የትግራይ ጉዳይ ነበር፡፡


የውጭ ጉዳይ ምኒስትሮቹ ባወጡት የጋራ መግለጫ “ሁሉም ወገኖች ግጭቱን በአስቸኳይ እንዲያቆሙ፣ የሰላማዊ ዜጎች ደህንነት መጠበቁን እንዲያረጋግጡ፣ ዓለም አቀፍን የሰአብአዊ መብት እና ዓለም አቀፍ ህግጋትን እንዲጠብቁ የሚዲያ ነጻነት እና ተደራሽነት እንዲኖር፣ አስገድዶ መድፈረና ጥቃትን ጨምሮ በሰ አብዊ መብት ጥሰትና ጥቃት የፈጸሙት ሁሉ ተጠያቂ እንዲሆኑ ማሳሰባቸው የሚታወስ ነው፡፡


(የቪኦኤ ዘጋቢ ኒክ ቺንግ ካጠናቀረችው ዘገባ የተወሰደ፡፡)

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-ethiopia-election-5-11-2021/5886875.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-ethiopia-election-5-11-2021/5886875.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 May 2021 23:34:00 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/us-ethiopia-election-5-11-2021/5886875.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/20670AA1-34C0-44B1-9727-2CBD4866CE1C_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አዲሱ የትግራይ ሥራ አስፈጻሚ መግለጫ ሰጡ</title>
            <description>በቅርቡ የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ሥራ አስፈፃሚ ሆነው የተሾሙት ዶ/ር አብርሃም በላይ በክልሉ ህዝብን ማእከል ያደረገ የተረጋጋ ሰላም ለማስፈንና አስተዳደር ለማረጋገጥ የክልሉ ህዝብና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት እንዲያግዙ ጥሪ አቀረቡ።


ዶ/ር አብርሃም በወቅታዊ ጉዳይና ቀጣይ እቅዳቸው አስመልክተው የፅሁፍ መግለጫ አውጥተዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡








 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5886827.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5886827.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 May 2021 23:15:49 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5886827.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/AF1B4CDA-2F48-4920-8090-48AA8F69A745_cx7_cy8_cw82_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአክሱም ጉዳይ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ገለፀ</title>
            <description>በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ ህዳር 19 /2013 ዓ.ም በተካሄደ ውጊያ “በውጊያው የተሳተፉ 93 ሰዎች የወታደር የደንብ ልብስ ያልለበሱ ሞተዋል” ሲል የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ገልጿል።


“ከተማው ውስጥ በመከላከያ ሠራዊትና በኤርትራ ወታደሮች ንፁሀን ተገድለዋል” ተብሎ የቀረበውን ክስ መሥሪያ ቤታቸው ለሁለት ወር ገደማ ሲመረምር መቆየቱን ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህጉ አቶ ፍቃዱ ፀጋ ዛሬ በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።


&quot;እስካሁን ባለው የተጣራ መረጃ መሠረት ስድስት ስዎች በመከላከያ ሠራዊቱ መገደላቸውን” ማረጋገጣቸውን አቶ ፍቃዱ ገልፀዋል።


በሌላ በኩል ግን በተመሳሳይ ጊዜ አክሱም ከተማ ውስጥ በተካሄደ ውጊያ “በመቶዎች የሚቆጠሩ” ሰዎች በተቀነባበረ ሁኔታ ተጨፍጭፈዋል” ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ቀደም ሲል ባወጣው ሪፖርት ጠቁሞ ነበር።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5886822.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5886822.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 May 2021 23:11:08 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ፀሐይ ዳምጠው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5886822.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/1027109B-B0A6-4B21-A1F1-4F1EE591AD79_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ም/ጠቅላይ ዐቃቤ ህጉ በሽብርተኝነት ስለተፈረጁ ድርጅቶች</title>
            <description>በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ላለፉት ሦስት ዓመታት የጥፋት ድርጊት ሲያከናውኑ ነበር ተብለው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት የተፈረጁ ሁለት አካላትን ተግባር በተመለከተ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ማብራሪያ ሰጥቷል።


ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ አቶ ፍቃዱ ፀጋ አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀውን ሸኔ የተባለ ቡድን እና ህወሓትን በተመለከተ ነው ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ የሰጡት።


በሽብር ህጉም አሸባሪ ከተባሉ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት ያላቸው አካላት እና ድጋፍ የሚያደርጉ ተጠያቂ ይሆናሉ ሲሉ አስታውቀዋል አቶ ፍቃዱ።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5886793.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5886793.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 May 2021 22:48:53 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ፀሐይ ዳምጠው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5886793.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/C7D0DCF9-631A-4B6E-B182-0C90595CDFE6_cx33_cy29_cw41_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ መልዕክት እና የሲኖዶስ ምላሽ</title>
            <description>በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ፓትርያርኩን አነጋገሩ</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5885468.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5885468.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 May 2021 00:04:00 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5885468.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9622F5D2-B330-433F-ADE8-62F8B92FCCEF_cx24_cy5_cw50_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ደምቢ ዶሎ ውስጥ አንድ ጋዜጠኛ ተገደለ</title>
            <description>በቄለም ወለጋ ዞን ደምቢ ዶሎ ከተማ ውስጥ የኦሮምያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ /ኦቢኤን/ ጋዜጠኛ ሲሳይ ፊዳ በጥይት ተመትቶ መገደሉን የቄለም ወለጋ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።


የዞኑ ፖሊስ ፀጥታ ማስከበር ምክትል ኃላፊ ግድያውን የፈፀመው ሸኔ እና አባ ቶርቤ ናቸው ብለዋል።


የመንግሥቱ ባለሥልጣናት &apos;ሸኔ&apos; እያለ የሚጠራቸው የምዕራብ ዞን ሸማቂዎች ቃል አቀባይ በበኩላቸው &apos;ግድያውን አልፈፀምንም&apos; ሲሉ አስተባብለዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5885386.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5885386.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 May 2021 23:38:11 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5885386.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/BAD7F7CB-5B02-4E6D-B06F-9CA8A2C23FF1_cx11_cy1_cw68_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ወደ ደቡብ ወሎ የሚገቡ ተፈናቃዮች ቁጥር መጨመሩ ተገለጸ</title>
            <description>በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተውን አለመረጋጋት ተከትሎ ወደ ደቡብ ወሎ የሚገቡት ተፈናቃዮች ብዛት እየጨመረ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ፡፡


ዞኑ አራት ሳምንታት ባለሞላ ጊዜያት ውስጥ ብቻ ከ8 ሽህ በላይ ተፈናቃዮችን ተቀብሏል፡፡ እስካሁን 18 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የምግብ፣ የአልባሳትና የገንዘብ ድጋፍ በመንግሥት፣ በውጭ አገራት በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣ በአካባቢው ኗሪዎችና በባለሃብቶች ተደርጓል፡፡


በጊዜያዊ መዋጮና የእለት ደራሽ ድጋፍ ተፈናቃዮቹን በዘላቂነት ማቋቋም አይቻልም የሚለው የዞኑ አስተዳደር የፌዴራሉም ሆነ የክልሉ መንግሥት በዚህ በኩል ትኩረት ሰጥተው እንዲንቀሳቀሱ ጥሪ አስተላልፏል፡፡


የክለልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን 878ሽህ የሚደርሱ የአማራ ተወላጆች በክልሉም ሆነ ከክልሉ ውጭ መፈናቀላቸውን ይፋ አድርጓል፡፡


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5885234.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5885234.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 May 2021 21:41:26 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (መስፍን አራጌ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5885234.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/E8A904EC-68D2-411C-9C6D-98355FC3EE8B_cx5_cy0_cw92_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፓርቲዎች ህወሓት “አሸባሪ” መባሉን ተቃወሙ</title>
            <description>ሦስት የትግራይ ፓርቲዎች ህወሓት “አሸባሪ” ተብሎ መሰየሙ ተቃወሙ።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5885229.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5885229.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 May 2021 21:35:41 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5885229.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/4A61C918-36D7-423F-827E-A37C12657B5D_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያ ሚዲያ በሴት ጋዜጠኞች ዓይን ሲቃኝ</title>
            <description>ኮሮናቫይረስና የፖለቲካ አለመረጋጋት ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የከተቱት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ውስጥ የሚሰሩ ጋዜጠኞች ከሚደርስባቸው ጫና በተጨማሪ ሴት ጋዜጠኞች በሥራ ቦታቸው መድሎ፣ ለኃላፊነት አለመታጨት፣ የፆታ ትንኮሳና በተለይ ከቅርብ ግዜ ወዲህ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች አማካኝነት ፆታቸውን መሰረት ያደረገ ጥቃት እንደሚደርስባቸው ይናገራሉ። ስመኝሽ የቆየ ሴት ጋዜጠኞች በሥራቸው ውስጥ የሚያጋጥሟቸውን ዘርፈ ብዙ ችግሮች እንዴት ይቋቋሟቸዋል ስትል በአሻም ቲቪ ረዳት አዘጋጅ ከሆነችው ካሳዬ ዳምጤ ጋር ቆይታ አድርጋለች።


(ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ)






 


 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5885264.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5885264.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 May 2021 21:32:52 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>ጋቢና ቪኦኤ</category><author> voadigital@voanews.com (ስመኝሽ የቆየ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5885264.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/334C9524-FFC9-40D8-8C18-F802E4A1077B_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>እንጉዳይ እንደ ስጋ ፦ ቆይታ ከእንጉዳይ አምራቹ ወጣት ጋር </title>
            <description>ዮናታን በቀለ ብዙም ባልተለመደው  የእንጉዳይ ማብቀል ስራ ውስጥ የተሰማራው ሺታኪ  ድርጅት መስራች   ነው።የዛሬ 9 ዓመት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የድህረ ምረቃ ተማሪ በነበረበት ሰዓት የጀመረው ስራ ከእንጀራ በተጨማሪ በተለያዩ ዓለም ከተሞች እየተዟዟረ ልምድ የሚቀስምበትን መልካም ዕድል ፈጥሮለታል።


 ሀብታሙ ስዩም  ከዮናታን ጋር አጭር ቆይታ በማድረግ ስለ ስራው እና በስራው ውስጥ ስላሉ ውጣ ውረዶች ለማወቅ ሞክሯል። ዮናታን አስቀድሞ አጀማመሩን ያጫውተናል።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5883953.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5883953.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 09 May 2021 20:01:49 +0300</pubDate>
            <category>ኢትዮጵያ</category><category>ጋቢና ቪኦኤ</category><author> voadigital@voanews.com (ሀብታሙ ስዩም)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5883953.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0657BD6C-F575-4DF8-99A7-3A5EBBD3BDA4_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>&quot;እኛ ኢትዮጵያውያን&quot; ስለምርጫው የህዝብ አስተያየት - ከሀዋሳ </title>
            <description>ኢትዮጵያ ስድስተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ትገኛለች። በአንድ በኩል ይሄንን ዴሞክራሲያዊ ክንውን ለማሳካት እየሰራች ያለችው ሀገር በተለያዩ ፈተናዎች ውስጥ እያለፈች መሆኗም ይታያል።


የዚህች ሀገር ዜጎች ተስፋና ሥጋቶች እንደዚሁም የወደፊት ምኞቶች ምንድን ናቸው?


የአሜሪካ ድምፅ ዘጋቢ ከሀዋሳ በተለያየ ሙያ ላይ የተሰማሩ ዜጎችን አነጋግሯል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5882515.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5882515.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 May 2021 23:03:31 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>ምርጫ 2013</category><author> voadigital@voanews.com (ዮናታን ዘብዴዎስ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5882515.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/04A7F01D-0C8C-4748-9F11-5D9ACE531312_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የአቶ ዳዉድ ኢብሳ መኖሪያ ቤት …</title>
            <description>የፖሊስ ባልደረቦች ባለፈው ሰኞ ሌሊት ወሰዱ በተባለ እርምጃ አዲስ አበባ የሚገኘውን ኦሮሞ ነፃነት ግንባር ሊቀመንበር አቶ ዳዉድ ኢብሳ መኖሪያ ቤት በር ሰብረው መግባታቸውንና የጥበቃ አባላቱን ትጥቅ አስፈትተው በቁጥጥር ሥር ማዋላቸውን የአቶ ዳዉድ ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ዶክተር ሽጉጥ ገለታ ለቪኦኤ ገልፀዋል።


አድራጎቱ “ህገወጥ ነው” ሲሉ ዶ/ር ሽጉጥ ኮንነዋል።


ከፖሊስና ከመንግሥት ባለሥልጣናት ምላሽ ለማግኘት በተከታታይ ቀናት ያደረግነው ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/dawud-ibsa-police-5-7-2021/5882437.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/dawud-ibsa-police-5-7-2021/5882437.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 May 2021 22:03:16 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (በፍቃዱ ሞረዳ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/dawud-ibsa-police-5-7-2021/5882437.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/6E9F7088-F4D2-4075-861E-8DF47244B601_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>“ኢትዮጵያዊያን ከዘረኝነትና ከጥላቻ መውጣት አለባቸው” ብፁዕ አቡነ አብርሐም</title>
            <description>“ኢትዮጵያዊያን ከዘረኝነትና ከጥላቻ መውጣት አለባቸው” ሲሉ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተክርስትያን ቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ አብርሐም አሳስበዋል።


የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ አብርሐም ሰሞኑን ያረፉት የቀድሞው የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ አበረ አዳሙ አስከሬን በተሸኘበት ሥርዓተ ቀብር ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ አሁን ከገጠማት ከባድ ፈተና የምትወጣው


“ህዝቦቿ ከዘረኝነት እና ከጥላቻ ወጥተው በአንድነት ሲቆሙ ብቻ ነው” ሲሉ አሳስበዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5882422.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5882422.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 May 2021 21:59:19 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (አስቴር ምስጋናው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5882422.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/B72E162C-833F-491E-BA58-136313A20773_cx0_cy3_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የጄፍሪ ፌልትማን የአፍሪካ ጉዞ</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ትናንት በአስመራ ከኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋራ ተነጋግረዋል።


የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረ መስቀል በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ ፕሬዚዳንት ኢሳያስና የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ ልዑኩ ትናንት ከቀትር በኋላ አራት ሰዓት የፈጀ ውይይት እንዳካሄዱ ገልጸዋል።


ፕሬዚዳንት ኢሳያስ የአፍሪካ ቀንድ ችግሮች ለመፍታት በሚደረጉ ጥረቶች ኤርትራ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኗን ለዩናይትድ ስቴትስ ልዩ ልዑኩ ያረጋገጡላቸው መሆኑን የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።


አምባሳደር ፌልትማን በበኩላቸው ዩናይትድ ስቴትስ በአፍሪካ ቀንድ ባሉ አበይት ችግሮች ዙሪያ የዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር ያለውን አመለካከት ያብራሩ መሆኑን የአቶ የማነ ገብረ መስቀል የትዊተር ጽሁፍ አመልክቷል።


አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ረቡዕ በካይሮ ከግብጹ ፕሬዚዳንት አብደልፋታህ ኤል ሲሲ እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሳሜህ ሹክሪ ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸውን ዘገባዎች አመልክተዋል።


ልዩ ልዑኩ ዛሬ ወደሱዳን ያመሩ ሲሆን የፊታችን ዕሁድ ደግሞ ወደአዲስ አበባ እንደሚጓዙ ከዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ አመልክቷል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5882144.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5882144.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 May 2021 18:59:56 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5882144.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/EA9C5C44-B753-4DA2-833E-56BF56BCAA30_cx12_cy9_cw81_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኢሰመኮ በኦሮምያ ክልል የእስረኞች ሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ሁኔታ</title>
            <description>በኦሮምያ ክልል ሕግን የማስከበር እርምጃ ሕግን የተከተለ መሆን አለበት ሲል የኢትዮዽያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ።


ኢሰመኮ ለሦስት ወራት ገደማ በ21 ኦሮምያ ውስጥ በሚገኙ እስር ቤቶች ውስጥ የእስረኞችን አያያዝ በተመለከተ ክትትል አድርጊያለሁ ብሎ ባወጣው መግለጫ ነው የእስረኞች ሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ሁኔታ እንደሚያሳስበው ያስታወቀው።


በዚህ ዙሪያ ከኮሚሽኑም ሆነ ከኦሮምያ ክልል አመራሮች ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለአሁኑ አልተሳካም።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5882024.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5882024.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 May 2021 17:08:32 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5882024.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/4B36EA55-0302-4FB4-BDA0-8F5358D350B2_cx0_cy5_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባ አራዘመ</title>
            <description>ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በአብዛኞቹ ክልሎችና ሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች የመራጮች ምዝገባን አራዘመ። ቦርዱ ግጭት በነበረባቸው የተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎችም በመንግሥት የጸጥታ ድጋፍ ታግዞ በዛሬው ዕለት ምዝገባ መጀመሩን አስታውቋል።


ከሦስት ቀን በፊት በተሰበሰበ አሃዝ እስካሁን ለ6ኛው ብሔራዊ ምርጫ 28.7 ሚሊዮን መራጮች መመዝገባቸው ይፋ ሆኗል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5882017.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5882017.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 May 2021 17:03:19 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>ምርጫ 2013</category><author> voadigital@voanews.com (አዲስ ቸኮል)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5882017.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/4AB5A8CB-8287-40BE-8D55-ED87CC05D8D1_cx12_cy10_cw75_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>&quot;እኛ ኢትዮጵያውያን&quot; ስለምርጫው የህዝብ አስተያየት - ከአምቦ </title>
            <description>ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ግንቦት ወር ልታካሂደው ባቀደችው ምርጫ ለመምረጥ እንዲሁም ላለመምረጥ ያቀዱ የማኅበረሰብ ክፍል አባላት መኖራቸውን ከአምቦ ከተማ የተለያዩ ስፍራዎች ተዘዋውሮ ያነጋገረው ዘጋቢያችን አስተያየቶቹን ልኮልናል።


“ለመምረጥ ካርድ ወስደናል። ይበጀናል፣ ይሆናል ላልነው የፖለቲካ ድርጅት ድምጻችንን እንሰጣለን” ያሉ እንዳሉ ሁሉ ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ እንዳልወሰዱ የገለጹም አሉ።


የማይመርጡበትን ምክንያት ሲያስረዱ ደግሞ በአምቦም ሆነ እንደ ክልሉ ሌሎች አማራጭ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫው አለመሳተፍ እና ሌሎች ምክንያቶችን ገልጸዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5881886.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5881886.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 May 2021 15:11:48 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>ምርጫ 2013</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5881886.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/C55E0A2D-4009-4A30-B100-CE82AF7DF5CF_cx0_cy6_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፓርላማው ሁለት ድርጅቶችን በሽብርተኛነት ፈረጀ</title>
            <description>የኢትዮጵያ ፓርላማ “ህወሓት” እና “ሸኔ” ብሎ የጠራው ቡድን ስለ ሽብር የወንጀል ድርጊት የተሰጠውን ትርጓሜ አሟልተው መገኘታቸውን በመግለፅ በሽብርተኛነት እንዲፈረጁ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያቀረበለትን የውሣኔ ሃሳብ ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ አፅድቋል።


በሽብርተኛነት ከተፈረጁት ድርጅቶች የተሰማ ምላሽ የለም።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5880998.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5880998.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 06 May 2021 22:51:43 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ዮናታን ዘብዴዎስ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5880998.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5BBF897D-163C-4F79-A00B-411F98CAA7B2_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>