<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>የሱዳን ቀውስ  - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/7470</link>
        <description>Sudan Crisis </description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>የሱዳን ቀውስ  - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/7470</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Wed, 08 Apr 2026 19:11:23 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zvgjqtl-vomx-tpeumror" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>“ሱዳን ትልቁን ሰብአዊ ቀውስ የተሸከመች ሀገር ሆናለች” - ዓለም አቀፍ ነፍስ አድን ኮሚቴ</title>
            <description>በሱዳን በጦር ሠራዊቱ እና በፈጥኖ ደራሽ ኅይሎች መካከል ለ20 ወራት የዘለቀውን አስከፊ ጦርነት ተከትሎ “እስከዛሬ ከተመዘገቡት ሁሉ ትልቁን ሰብአዊ ቀውስ የተሸከመች ሀገር ሆናለች” ሲል የዓለም ነፍስ አድን ኮሚቴ አመለከተ፡፡


በተቃናቃኞቹ ጀኔራሎች መካከል በቀጠለው ጦርነት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ 12 ሚሊዮን የሚሆኑት ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን የተቋሙ ዘገባ ጠቅሷል፡፡


ወደ ዘጠኝ ሚሊዮን የሚጠጉት በሀገር ውስጥ የተፈናቀሉ ናቸው፡፡ አብዛኛዎቹ መሠረተ ልማቶች በወደሙባቸው አካባቢዎች የሠፈሩ ሲሆን የጅምላ ረሃብ ሥጋትም ተጋርጦባቸዋል።


ዓለም አቀፉ ድርጅት በሱዳን ወደ 26 ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ ለከባድ ረሃብ መጋለጡን ገልጾ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ታይቶ የማይታወቅ ሰብአዊ ቀውስ ገጥሟታል ብሏል፡፡


“ከዓለም ሕዝብ ከአንድ ከመቶ ያነሰ የሕዝብ ብዛት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/sudan-has-become-the-biggest-humanitarian-crisis-ever-recorded-irc/7897430.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/sudan-has-become-the-biggest-humanitarian-crisis-ever-recorded-irc/7897430.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 11 Dec 2024 17:44:47 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/70632e21-ef95-43cb-bc51-fc3de3b99897_cx0_cy4_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሱዳን ሴቶች በጦርነቱ የደረሰባቸውን ስቃይ ይገልጻሉ</title>
            <description>ከተለያዩ አካባቢዎች የተሰባሰቡ ሱዳናውያን ሴቶች፣ ላለፉት ሰባት ወራት በሀገራቸው ላይ እየተካሄደ ስላለው አስከፊ ጦርነት ለመነጋገር ናይሮቢ ላይ ተሰባስበው ነበር። ማቆሚያ ያለው በማይመስለው ጦርነት ድምፃቸው መታፈኑን ያመለከቱት እነዚህ ሴቶች፣ ከሚያዚያ ጀምሮ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን የገደለውን እና በሚሊየን የሚቆጠሩትን ያፈናቀለውን ግጭት ለመፍታት የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ለማድረግ ያላቸውን ፍላጎት ገልፀዋል።


የአሜሪካ ድምፅ የናይሮቢ ቢሮ ኃላፊ ማሪያማ ዲያሎ ያደረሰችንን ዘገባ፣ ስመኝሽ የቆየ ወደ ዐማርኛ መልሳዋለች።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7377417.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7377417.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 29 Nov 2023 22:45:58 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-4e16-08dbf113587b_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሱዳን በዜጎች ላይ ለተፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶች የሰብአዊ መብት ተሟጋቶች የፈጥኖ ደራሽ ልዩ ኃይሉን በተለይ ተጠያቂ አደረጉ</title>
            <description>አንድ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ቡድን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለሞያዎች በየበኩላቸው ባወጧቸው መግለጫዎች፡ ሁከት ባልተለየው የምዕራብ ዳርፉር ግዛት ‘ፈጽሟል’ ባሏቸው በሴቶች ላይ የተነጣጠሩ ጥቃቶች በተለይ የሱዳኑን ፈጥኖ ደራሽ ልዩ ኃይል ወነጀሉ።


በሃገሪቱ ጦር እና በተቀናቃኙ የፈጥኖ ደራሽ ልዩ ኃይል መካከል በተቀሰቀሰው እና አምስተኛ ወሩን በያዘው ግጭት፡ ቡድኑ አረብ ያልሆኑ ዜጎች በሚኖሩበት የምዕራብ ዳርፉር ክልል በሴቶች እና ልጃገረዶች፤ እንዲሁም በማሕበረሰብ አንቂዎች ላይ የተነጣጠሩ ጥቃቶችን መፈጸሙን ዋና መቀመጫውን በኒው ዮርክ ያደረገው ሂዩማን ራይትስ ዎች በትላንትናው ዕለት ይፋ አድርጓል።


የመብቶች ተሟጋቹ ቡድኑ አክሎም ግጭቱ ከተቀሰቀሰበት ካለፈው የሚያዝያ ወር አጋማሽ አንስቶ እስከ ሰኔ ወር አጋማሽ በነበረው ጊዜ ውስጥ ቁጥራቸው...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/rights-group-and-un-experts-single-out-sudanese-paramilitary-with-accusations-of-sexual-violence/7230933.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/rights-group-and-un-experts-single-out-sudanese-paramilitary-with-accusations-of-sexual-violence/7230933.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 18 Aug 2023 19:07:12 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/aa14c2dd-3498-4b49-870e-14396f3d3765_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>“በሱዳን የስደተኞች ቁጥር እየጨመረ ነው፡  የጤና ሁኔታው እያሽቆለቆለ ነው” ተመድ</title>
            <description>እየተባባሰ የመጣውን ጦርነት ሸሽተው አገር ጥለው የሚሰደዱት ሰዎች  ቁጥር እየጨመረ በሚገኝባት በሱዳን እና በአጎራባቾቿ ሀገራት የጤና ሁኔታ እያሽቆለቆለ መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተቋማት አስጠነቀቁ፡፡


ጦርነቱ ከመቀስቀሱ በፊት 4.5 ሚሊዮን ሱዳናውያን ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን ከ 3ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት እዚያው ሱዳን ውስጥ ሌሎች 800,000 ደግሞ ወደ ቻድ ፣ ደቡብ ሱዳን ፣ ግብፅ እና ኢትዮጵያ ተሰድደዋል፡፡


ተቃናቃኞቹ ጄኔራሎች ወደ ጦርነት ከገቡ ወዲህ፣  ከአራት ሚሊዮን የሚበልጡ ተጨማሪ ሰዎች  መፈናቀላቸውን የ ተ መ ድ የስደተኞች ኮሚሽን አስታውቋል፡፡


 “የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን አባላት በሚገኙበት በሱዳን  ያለው ችግር አሁን በእጃችን ባለው ዓቅም ሊሰጥ ከሚችለው ዕርዳታ በእጅጉ የገዘፈ ነው”  ሲሉ የ ዩ ኤን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/unhcr---sudan---health/7218477.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/unhcr---sudan---health/7218477.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 09 Aug 2023 22:10:25 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-a2fe-08db98e6d096_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ወደ ደቡብ ሱዳን የተሰደዱ ሱዳናውያን አሳሳቢ ችግር ገጥሟቸዋል</title>
            <description>በሀገራቸው የሚካሄደውን ጦርነት ሸሽተው ወደ ደቡብ ሱዳን የተሰደዱ 19ሺሕ ሱዳናውያን አሳሳቢ ችግር ገጥሟቸዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል፡፡ በያዝነው የፈረንጆች ዓመት መጨረሻ ላይ ቁጥራቸው እጥፍ እንደሚሆን ግምቱን አስቀምጧል። 


የሱዳኑ  ጦርነት ባለፈው ሚያዚያ ከጀመረ ወዲህ፣ 100 ሺሕ የሚሆኑ ስደተኞች ደቡብ ሱዳን ገብተዋል፡፡አብዛኞቹ የደቡብ ሱዳን ዜጎች ሲሆኑ፣ 19 ሺሕ የሚሆኑት ደግሞ ሱዳናውያን ናቸው ተብሏል። 


ስደተኞቹ በየግላቸው ከገጠማቸው ሰቆቃ በተጨማሪ፣ የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን አለማወቃቸው አሳስቧቸዋል ሲል የቪኦኤው ሄንሪ ዊልኪንስ ከደቡብ ሱዳን በላከው ዘገባ አመልክቷል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/s-sudan-sudan-refugees-/7205096.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/s-sudan-sudan-refugees-/7205096.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 31 Jul 2023 17:50:47 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-c0a8-0242-945c-08db71b6774e_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በዳርፉር  ሚሊሽያዎች ግድያ እና አስገድዶ መድፈርን ጨምሮ  የበረታ ግፍ እየፈጸሙ ነው</title>
            <description>አምና አል-ኑር ሁለት ጊዜ ለጥቂት ከሞት አምልጣለች። የመጀመሪያው በሱዳኗ የዳርፉር ግዛት የቤተሰቦቿን  ቤት ሚሊሽያዎች ባጋዩበት ወቅት ሲሆን፤  ከሁለት ወራት በኋላ  ደግሞ  እርሷንና እና ሌሎች ጦርነቱን በመሸሽ  ከቻድ ጋር የሚያዋስነው ድንበር ለመድረስ ሲሞክሩ ሚሊሻዎች ይዘዋቸዋል።

 



“እንደ በግ ጨፈጨፉን” ስትል ባለፈው ሚያዝያ ወር መጨረሻ በትውልድ ከተማዋ ጀኒና ስለደረሰው ጥቃት የተናገረችው የ32 ዓመቷ መምሕርት &quot;ሁላችንንም ከቀያችን ለመንቀል ያደረጉት ነው።&quot; ብላለች፣

 

አል ኑር እና ሶስት ልጆቿ አሁ ን ያሉት ቻድ ውስጥ ወደ ስደተኞች ካምፕ የተለወጠ ትምህርት ቤት ውስጥ ነው። ከእልቂቱ የተረፉት እና ሁኔታውን በቅርብ የሚከታተሉ የመብት ተሟጋቾች  “የጭካኔ መዓት” ካሉት ጥቃት  የሸሹ፣ የሚበዙቱ ሴቶች እና ህጻናት የሆኑ  ከ260 ሺህ በላይ ሱዳናውያን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7202435.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7202435.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 28 Jul 2023 21:32:32 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-bd2d-08db8edbf3b7_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በናይሮቢ የስደተኞችን የቋንቋ ውስንነት የሚቀርፍ ትምህርት እየተሰጠ ነው</title>
            <description>በናይሮቢ የሚኖሩ በርካታ ስደተኞች፣ ኬንያውያን በስፋት የሚግባቡባቸውን ሁለቱን ቋንቋዎች፣ እንግሊዘኛንም ኾነ ስዋሂሊን፣ አጥርተው አይናገሩም።

 

ይኸው የቋንቋ ተግባቦት ውስንነት፣ ስደተኞች፣ ከኅብረተሰቡ ጋራ ለመዋሐድ ጥረት በሚያደርጉት ወቅት፣ ብርቱ እክል ይጋርጥባቸዋል።

 

ኹኔታውን ለመቀየር እየተደረገ ስላለው የአንድ ዩኒቨርሲቲ ጥረት፣ ሁባህ አብዲ ከናይሮቢ ያጠናቀረችውን ዘገባ ዝርዝር፣ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7202397.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7202397.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 28 Jul 2023 21:18:19 +0300</pubDate>
            <category>ቪድዮ</category><category>የቪዲዮ ዘገባ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-39d3-08db8f95d632_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ካርቱም በፈጥኖ ደራሽ ኀይሉ ድሮኖች ስትደበደብ ዋለች </title>
            <description>የሱዳን ዋና መዲና ካርቱም፣ በዛሬው ዕለት በሮኬትና በድሮን ስትደበደብ ዋለች። ፈጥኖ ደራሽ ኀይሉ፣ በመዲናዪቱ ሰሜን አቅጣጫ የሚገኝን ቁልፍ የአየር ኃይል ማረፊያ ማጥቃቱንና በደርዘን የሚቆጠሩ የሠራዊት አባላትን መግደሉን አስታውቋል። 


በዋና ከተማዋ ሰሜናዊ ምዕራብ አቅጣጫ፣ የከባድ መሣሪያ ድብደባ እንደነበርና የፈጥኖ ደራሽ ኀይሉ ድሮኖች፣ በሰሜን ካርቱም የሚገኝ የአየር ኃይል ማረፊያን ማጥቃታቸውን፣ ኤኤፍፒ የነዋሪዎችን ቃል ጠቅሶ ዘግቧል። 


ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ባወጣው መግለጫ፥ ሦስት ተዋጊ ጄቶችን፣ በርካታ መሣሪያዎችን፣ ወታደራዊ ቁሳቁሶችንና አቅርቦቶችን ማውደሙን አስታውቋል። በደርዘን የሚቆጠሩ የአገሪቱ ሠራዊት አባላትንም መግደሉን ወይም ማቁሰሉን አክሎ ገልጿል። 


በካርቱም እና በምዕራብ ዳርፉር፣ ከሚያዝያ 15 ቀን ጀምሮ እየተካሔደ ባለው ውጊያ፣ 3ሺሕ 900...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/rockets-hit-khartoum-air-force-base-attacked/7200574.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/rockets-hit-khartoum-air-force-base-attacked/7200574.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 27 Jul 2023 19:21:39 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-c0a8-0242-1cb7-08db8d2d84b1_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሱዳን ግጭት ከሦስት ሚሊዮን በላይ ሰዎች እንደተፈናቀሉ ተመድ አስታወቀ</title>
            <description>በሱዳን በመባባስ ላይ ባለው ግጭት ሳቢያ፣ ወደ ጎረቤት አገሮች የሸሹትን ከ700 ሺሕ በላይ ሰዎችን ጨምሮ፣ 3ነጥብ1 ሚሊዮን ሰዎች እንደተፈናቀሉ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዛሬ ሲያስታውቅ፣ ግጭቱ ሙሉ ለሙሉ ወደለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት እንዳያመራ ስጋቱ አይሏል።


ግጭቱ፣ ባለፈው ሚያዝያ ሰባት ቀን ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ፣ ከሦስት ሺሕ በላይ ሰዎች ሕይወታቸውን ሲያጡ፣ ከስድስት ሺሕ በላይ ደግሞ እንደቆሰሉ፣ የአገሪቱ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።


2ነጥብ4 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች በሀገር ውስጥ እንደተፈናቀሉ፣ ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት(IOM) አስታውቋል።


ወደ ጎረቤት ሀገራት ከሸሹት ውስጥ፣ ግብጽ፥ ከ255 ሺሕ በላይ በመቀበል ከፍተኛውን ቁጥር ስታስተናግድ፣ ኢትዮጵያም እስከ አሁን ከ62 ሺሕ በላይ እንደተቀበለች ታውቋል።


አራት የቀንዱ ሀገራት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7177890.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7177890.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Jul 2023 20:31:32 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/f40175ec-ecd0-4bd1-9408-954346a86730_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከዳርፉር ክልል ወደ ቻድ የሚሻገሩ ስደተኞች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን ተመድ አስታወቀ</title>
            <description>በሱዳን ሶስት ወራትን ያስቆጠረውን ግጭት በመሸሽ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ጎረቤት ወደምትገኘው ማዕከላዊ አፍሪካዊቷ ሀገር ቻድ እየተሰደዱ መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዓለም ምግብ ፕሮግራም አስታውቋል። የዓለም አቀፉ ሰብዓዊ ተቋም ኃላፊም በሱዳን ያለውን ሁኔታ &quot;እጅግ በጣም ጭካኔ የሞላበት&quot; የእርስ በእርስ ጦርነት ሲሉ ገልፀውታል።


የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ ባለፈው ሳምንት ብቻ፣ ከሱዳን ዳርፉር ክልል የተነሱ 20 ሺህ ሰዎች በቻድ ድምበር ላይ ወደምትገኘው አድሬ የተሰኘች ትንሽ ከተማ መግባታቸውን ገልጿል።




በሱዳን ያለው ግጭት ጎሳን መሰረት እያደረገ መምጣቱን ተከትሎ እየሸሹ ያሉ ሰላማዊ ዜጎች ሆን ተብለው ዒላማ ይደረጋሉ የሚሉ ሪፖርቶች እየወጡ ባሉበት ወቅት፣ ከዳርፉር ወደ ቻድ የሚገቡት ስደተኞች አብዛኞቹ በጠና የቆሰሉ መሆናቸውን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un-food-agency-says-growing-number-of-refugees-from-sudan-s-darfur-region-are-crossing-into-neighboring-chad/7176102.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un-food-agency-says-growing-number-of-refugees-from-sudan-s-darfur-region-are-crossing-into-neighboring-chad/7176102.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Jul 2023 18:54:59 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-fe34-08db5bbb6e95_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሱዳን ወጣቶች በውጊያ እንዲሳተፉ ለቀረበላቸው ብሔራዊ ጥሪ ተፃራሪ አቋም ይዘዋል</title>
            <description>የሱዳን የጦር ኃይሉ መሪ ጄኔራል አብዱል ፋታሕ አል ቡርሃን፣ ባለፈው ሳምንት፣ የአገሪቱ ወጣቶች፣ ከፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ጋራ በሚካሔደው ውጊያ እንዲሳተፉ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ አንዳንዶች ጥሪውን “ብሔራዊ ግዴታችን ነው” ብለው ሲቀበሉ ሌሎች ደግሞ፣ “ጦርነቱን ያራዝመዋል” የሚል ስጋት አሰምተዋል፡፡


ማይክል አቲት ከጁባ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/sudan-military-youth-pkg-mp4/7175800.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/sudan-military-youth-pkg-mp4/7175800.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Jul 2023 15:38:48 +0300</pubDate>
            <category>ቪድዮ</category><category>የቪዲዮ ዘገባ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-745f-08db820b6ad2_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሱዳን አየር ኃይል ተዋጊ ጄት በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ተመትቶ መውደቁ ተሰማ</title>
            <description>በሱዳን ዋና መዲና ካርቱም፣ ዛሬ ማክሰኞ፣ በከባድ መሣሪያ የታገዘ ከፍተኛ ውጊያ በበርካታ መንደሮች እንደተደረገ ሲገለጽ፣ አንድ ተዋጊ ጄት ተመትቶ ሲወድቅ እንደተመለከቱ፣ የዐይን ምስክሮች፣ ለኤኤፍፒ ዜና ወኪል ተናግረዋል።


“ጄቱ ወደ መሬት ሲወድቅ፣ አብራሪዎቹ በጃንጥላ ሲወርዱ አይተናል፤” ሲል፣ እንደ ሌሎቹ ምስክሮች ኹሉ ስለ ደኅንነቱ ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ፣ አንድ የሰሜን ካርቱም ነዋሪ ለኤኤፍፒ ተናግሯል።


ተዋጊ ጄቱን፣ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ መትቶ እንደጣለ፣ አንድ በልዩ ኃይሉ ውስጥ ያሉ ምንጭ፣ ለዜና ወኪሉ ተናግረዋል።


የተዋጊ ጄት አብራሪው፣ በፓራሹት ከወረደ በኋላ በቁጥጥር ሥር እንዳዋለው ጨምሮ የገለጸው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ፣ የሱዳን አየር ኃይልን፥ “እልቂት ፈጽሟል፤” ሲል ወጅሏል።


ከወንዙ ማዶ ባለችው ኦምዱርማን፣ በተለያዩ መሣሪያዎች የታገዙ ከባድ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/sudan-security/7166539.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/sudan-security/7166539.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 04 Jul 2023 18:20:00 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-c0a8-0242-2c8a-08db6c3fa8fd_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የካርቱምን ፖሊስ ዋና ጽ/ቤት ለመቆጣጠር በተደረገው ውጊያ ሰላማዊ ሰዎች ሞቱ</title>
            <description>ጦርነት ባመሳት በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም  ተፋላሚዎች የፖሊስ ዋና ጽ/ቤትን ለመቆጣጠር  በሚያደርጉት ውጊያ ቢያንስ 14 ሰላማዊ ሰዎች መሞታቸውን ተሟጋቾች ዛሬ ሰኞ አስታወቁ፡፡


ካለፈው ሚያዝያ አጋማሽ አንስቶ ከሱዳን መደበኛ የጦር ሰራዊት  ጋር በመዋጋት ላይ የሚገኘው የፈጥኖ ደራሹ ጦር የፖሊስ ዋና መ/ቤቱን በመቆጣጠር በጦርነቱ ድል ማስመዝገቡን ትናንት እሁድ ረፋዱ ላይ አስታውቋል፡፡


የፈጥኖ ደራሹ ጦር ባወጣው መግለጫ “ዋና ጽ/ቤቱ በሙሉ ቁጥጥራችን ስር ነው... በርካታ ቁጥር ያላቸው ተሸከርካሪዎችን፣ መሳሪያዎችና ጥይቶችንም ይዘናል” ብሏል፡፡


ታንኮችን፣ፒክ አፕ መኪናዎችን እና ፣ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችንም መያዙን መግለጫው ጨምሮ ገልጿል፡፡


ስማቸውን ለመግለጽ ያልፈለጉ አንድ የቀድሞ ጦር መኮንን በሃምዳን ደጋሎ የሚመራው የፈጥኖ ደራሹ ጦር ስትራቴጂክ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/Sudan-civilians-killed-in-battle-for-Khartoum-police-hq/7153232.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/Sudan-civilians-killed-in-battle-for-Khartoum-police-hq/7153232.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 26 Jun 2023 17:51:24 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-c0a8-0242-5340-08db75cbab90_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሱዳን ከሶስት ቀናት ተኩስ ማቆም በኋላ ውጊያው ቀጥሏል </title>
            <description>የ72 ሰዓታት የተኩስ ማቆም በተጠናቀቀ በደቂቃዎች ውስጥ፣ የሱዳን መዲና ካርቱም ዛሬ ማለዳ በከባድ መሣሪያ ተኩስ ተንጣለች፡፡


ከተኩስ ማቆሙ ፍጻሜ ቀደም ብሎ ማክሰኞ ምሽት፣ የሱዳን የስለላ ተቋም በእሳት ጋይቷል። ለእሳት ቃጠሎው አንዱ ተፋላሚ ወገን ሌላውን ይከሳል።


በአብደል ፋታህ አል ቡርሃን በሚመራው የሱዳን ሠራዊት ውስጥ ያሉ አንድ ምንጭ፣ ለእሳቱ የሞሃመድ ሃምዳን ደጋሎን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ተጠያቂ አድርገዋል። በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ውስጥ ያሉ ሌላ ምንጭ ደግሞ ፣ የኃይሉ ወታደሮች ተሰባስበው በሚገኙበት የስለላ ተቋም ላይ ሠራዊቱ በድሮን ጥቃት ፈጽሟል ሲሉ ለኤኤፍፒ ዜና ወኪል ተናግረዋል።


ከናይል ባሻገር ባለችው ኦምዱርማን ከተማ ያሉ ነዋሪዎች ደግሞ ዛሬ ማለዳ የከባድ መሣሪያ ልውውጥ መስማታቸውን ተናግረዋል። የጦር አውሮፕላኖችም ዝቅ ብለው ሲበሩ ነበር...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/Sudan-fighting-resumes-minutes-after-latest-truce-ends/7146787.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/Sudan-fighting-resumes-minutes-after-latest-truce-ends/7146787.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 21 Jun 2023 18:50:22 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-2ffb-08db7242a0e9_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሱዳን ግጭት ከሁለት ሚሊዮን በላይ ሰዎች ማፈናቀሉን ተመድ አስታወቀ</title>
            <description>- በዳርፉር የከፋው ጥቃት “በሰብእና ላይ የተፈጸመ ወንጀል”ን ወደ ማቋቋም እያመራ ነው፤ ተብሏል


በሱዳን እየተካሔደ ያለው ግጭት፣ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ሰዎች ማፈናቀሉን፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ ትናንት ረቡዕ አስታውቋል። በዳርፉር እየተባባሰ የመጣው ጥቃት፣ “በሰብእና ላይ የተፈጸመ ወንጀል”ን ለማቋቋም ወደሚችልበት ደረጃ እያመራ እንደኾነ፣ አንድ የመንግሥታቱ ድርጅት ባለሥልጣን አስታውቀዋል።




ከሚያዝያ ወር አጋማሽ ጀምሮ፣ በጦር ኃይሉ እና በተቀናቃኙ የፈጥኖ ደራሽ ጦር መካከል፣ በዋና ከተማዪቱ ካርቱም እና አካባቢዋ በተቀሰቀሰ ውጊያ፣ ሱዳን ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ገብታለች። ከባዱ ውጊያ ሲካሔድባቸው በሰነበቱት በዋና ከተማዋ ክፍሎች እና በዳርፉር፣ ትላንትም ውጊያው ቀጥሏል።


እስካለፈው ሰኞ ድረስ፣ በጦርነቱ ቢያንስ 959 ሰዎች ሲሞቱ፣ 4ሺሕ750 የሚደርሱ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un-sudans-war-displaces-over-2-million/7138777.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un-sudans-war-displaces-over-2-million/7138777.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 15 Jun 2023 19:05:24 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/95db0003-4e19-4bc1-85bf-46a374cb6bb1_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በጦርነት በምትታመሰው ሱዳን ጾታዊ ጥቃቱ ተባብሷል፤ አንዷ ተጠቂ ዜይነብ ትናገራለች</title>
            <description>በጦርነት ከተበጠበጠችው የሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም፣ ለቅቃ በመሸሽ ላይ የነበረችው ዜይነብ እንደምትናገረው፣ አንድ የፈጥኖ ደራሽ ልዩ ኃይል አባል ደረቷ ላይ መሣሪያ ደግኖባት ደፈራት፡፡


በእርሷ፣ በታናሽ እህቷ እና አብረዋቸው ይጓዙ በነበሩ ሁለት ሴቶች ላይ ስለተፈጸመው ወሲባዊ ጥቃት፣ ዜይነብ፣ ለአዣንስ ፍራንስ ፕሬስ በዝርዝር አውስታለች፡፡ አብራቸው የነበረችው አንደኛዪቱ ሴት፣ ሕፃን ልጅ ይዛ በመሰደድ ላይ እንደነበረች ዜይነብ ገልጻለች፡፡


እንደዜይነብ ሁሉ፣ ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ፣ በገዛ መኖሪያ ቤታቸው፣ በየመንገዱ ወይም ታጣቂዎች በወረሯቸው ሆቴሎች ውስጥ፣ እንደተደፈሩ የተናገሩ ሴቶች ብዙዎች ናቸው፡፡


“ጦርነቱ ከተቀሰቀሰ ከአንድ ወር በኋላ ካርቱምን ለቅቀን ወጣን፡፡ የተሳፈርንበትን ሚኒባስ፣ ፈጥኖ ደራሽ ልዩ ኃይሎች፣ በዘረጉት የፍተሻ ኬላ ላይ አስቆሙት፡፡...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/afp---no-woman-feels-safe-sexual-violence/7135141.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/afp---no-woman-feels-safe-sexual-violence/7135141.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 13 Jun 2023 17:41:55 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-a650-08db67b61523_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከሱዳን ጦርነቱን የሸሹ ከ41ሺሕ በላይ ሰዎች ኢትዮጵያ ገቡ</title>
            <description>ላለፉት ስምንት ሳምንታት፣ በጦርነት እየታመሰች ከምትገኘው ሱዳን፣ እስካለፈው ማክሰኞ ድረስ፣ ድንበር ተሻግረው ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ሰዎች ቁጥር፣ ከ41ሺሕ200 ይበልጣል ብሎ እንደሚገምት፣ የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበርያ ቢሮ(UN-OCHA) አስታወቀ።


ከእነርሱም የሚበዙት፣ ኢትዮጵያውያን ተመላሾች እንደኾኑ ገልጿል።


ቆንጅት ታየ ወደ አማርኛ መልሳዋለች።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/amh-news-cr-2-the-impact-of-the-situation-in-sudan-on-ethiopia-pkg-mp4/7130545.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/amh-news-cr-2-the-impact-of-the-situation-in-sudan-on-ethiopia-pkg-mp4/7130545.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 09 Jun 2023 20:46:17 +0300</pubDate>
            <category>ቪድዮ</category><category>የቪዲዮ ዘገባ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-b0fe-08db69113852_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ዳግም የተኩስ አቁም ንግግር ጀምረዋል</title>
            <description>የሱዳን ተፋላሚ ወታደራዊ ኃይሎች፣ በሳዑዲ አረቢያ እና በአሜሪካ አደራዳሪነት፣ ዳግም የተኩስ አቁም ውይይት መጀመራቸውን፣ አል አረቢያ የተሰኘው የቴሌቭዥን ጣቢያ ዘግቧል፡፡


ኾኖም ተፃራሪዎቹ ኃይሎች፣ በመዲናዋ ካርቱም፣ በአየር እና በምድር የሚያደርጉትን ፍልሚያ ቀጥለዋል።


በጦር ሠራዊቱ እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ መካከል የሚደረገው ውጊያ፣ ሲቪሎች መሠረታዊ አገልግሎት እንዳያገኙ አድርጓል፤ ሕገ ወጥነት እንዲበራከትም በር ከፍቷል፤ ተብሏል።


በሳዑዲ አረቢያ እና በአሜሪካ አደራዳሪነት ሰብአዊ ሥራዎችን ለማከናወን፣ ባለፈው ሳምንት መደረግ የነበረበት የተኩስ አቁም ሳይከበር ለበርካታ ጊዜያት ተጥሷል።


በሳዑዲ አረቢያ መንግሥት ባለቤትነት የተያዘው አል አረቢያ ቴሌቭዥን፣ ሁለቱ ወገኖች፣ በሦስተኛ ወገን ለመነጋጋር መስማማታቸውን ቢገልጽም፣ ዝርዝር መረጃ ግን አልሰጠም።...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/sudan-violence-/7126989.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/sudan-violence-/7126989.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 07 Jun 2023 18:48:05 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-bfbc-08db67317293_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሱዳን ተፋላሚዎች ለተኩስ አቁሙ ቁርጠኝነት እንዲያሳዩ ዩናይትድ ስቴትስ ጠየቀች</title>
            <description>የሱዳን ተፋላሚዎች በዩናይትድ ስቴትስ እና በሳዑዲ አረቢያ ሸምጋይነት የተስማሙበትን ተኩስ አቁም ካከበሩ በሁለቱ ወገኖች መካከል ንግግር ለማመቻቸት ዝግጁ መሆኑን የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡


የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ዛሬ ሐሙስ በሰጡት ቃል “ሁለቱ ኃይሎች ለተኩስ አቁም ስምምነቱ ከልባቸው ተገዢ መሆናቸውን በድርጊታቸው ግልጽ ካደረጉ፣ ዩናይትድ ስቴትስና ሳዑዲ አረብያ፣ ለግጭቱ ከድርድር የመነጨ መፍትሄ እንዲገኝ፣ ሁኔታዎችን እንደገና ለማመቻቸት ዝግጁ ናቸው” ብለዋል፡፡


ዩናይትድ ስቴትስ መግለጫውን ያወጣችው፣ የሱዳን የጦር ሠራዊት፣ “የሰላም ስምምነቱን በተደጋጋሚ ጥሷል” በሚል፣ ከከሰሰው ከተፋላሚው የፈጥኖ ደራሽ ጦር ጋር የሚያደርገውን ንግግር ማቋረጡን ባስታወቀ ማግሥት ነው፡፡


ሁለቱ ወገኖች የሰብዓዊ ዕርዳታ ተደራሽነትን ለመፍቀድ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/Sudan-conflict/7118827.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/Sudan-conflict/7118827.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 01 Jun 2023 20:34:45 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/d01420b8-2f4a-4c32-bec9-e9e565023b78_cx0_cy4_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በካርቱም ከወላጅ አልባ ህጻናት ማሳደጊያ መውጫ ያጡ በርካታ ህጻናት ሞቱ</title>
            <description>ውጊያ በሚካሄድባት የሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም ከነበሩበት ወላጅ አልባ ህጻናት ማሳደጊያ መውጫ አጥተው በአሰቃቂ ሁኔታ ከከረሙ ብዙ ህጻናት መካከል ቢያንስ 60 ጨቅላ እና ህጻናት መሞታቸው ተነገረ፡፡አብዛኞቹ ህጻናት የሞቱት በረሃብ እና በትኩሳት ምክንያት ሲሆን ሀያ ስድስቱ የሞቱት ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በሁለት ቀን ውስጥ መኾኑ ተዘግቧል፡፡


አል ማይኮማ በተባለው የወላጅ አልባ ህጻናት ማሳደጊያ በህጻናቱ ላይ የደረሰውን ከባድ ስቃይ አሶሺየትድ ፕሬስ ያነጋገራቸው በርካታ ሐኪሞች፣ በጎ ፈቃደኛ ሠራተኞች ፣ የጤና ባለሥልጣናት እና ሠራተኞች ገልጸዋል፡፡ ህጻናቱ የከረሙበትን አሰቃቂ ሁኔታ የሚያመለክቱ ሰነዶች፣ ምስሎችና የቪዲዮ መረጃዎች ማየቱን ገልጿል፡፡


በግጭቱ የደረሰውን ጉዳት የሚከታተለው የሱዳን ዶክተሮች ቡድን፣ እኤአ ከሚያዝያ 15 ወዲህ፣ ቢያንስ 190 ህጻናትን ጨምሮ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/trapped-by-sudan-fighting-dozens-of-infants-toddlers-and-children-died-in-khartoum/7118729.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/trapped-by-sudan-fighting-dozens-of-infants-toddlers-and-children-died-in-khartoum/7118729.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 01 Jun 2023 18:46:42 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-c0a8-0242-b49e-08db62b659bf_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>