<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/4624</link>
        <description>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/4624</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Wed, 08 Apr 2026 19:11:22 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zuuoq_l-vomx-tpegimqv" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>በጀልባ አደጋ ዘጠኝ ፍልሰተኞች ሞቱ</title>
            <description>ሜዲትሬንያን ባሕርን አቋርጠው ወደ አውሮፓ ለመሻገር በመሞከር ላይ የነበሩ ፍልስተኞች፣ ጀልባቸው ተገልብጦ አንድ ሕፃንን ጨምሮ ዘጠኙ ሲሞቱ፣ 15 የሚሆኑት ደግሞ የደረሱበት አለመታወቁን የጣሊያን የባሕር ጠረፍ ጥበቃ አስታውቋል።


ከላምፔዱሳ ደሴት 50 ኪ.ሜ. ላይ ማዕበል በማየሉ ትናንት ረቡዕ አደጋው ሲደርስ፣ ከማልታ የአደጋ ግዜ ሠራተኞች የትብብር ጥያቄ ደርሶት እንደነበር የጣሊያን የባሕር ጠረፍ ጥበቃ ጨምሮ ገልጿል።


ሃያ ሁለት ፍልሰተኞችን መታደጉን እንዲሁም አንድ ሕፃንን ጨምሮ የዘጠኝ ሰዎችን አስከሬን ማግኘቱን የባሕር ጠረፍ ጥበቃው አስታውቋል።


የሟቾቹ ዜግነት እስከ አሁን ያልተገለፀ ሲሆን፤ በቱኒዚያ፣ ማልታ እና ሲስሊ መካከል የምትገኘው ላምፔዱሳ ወደ አውሮፓ ለመሻገር ለሚሞክሩ ፍልሰተኞች የመጀመሪያ ማረፊያ ነች፡፡


በሌላ በኩል በላምፔዱሳ አቅራቢያ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/italy-mediterranean-capsize/7565806.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/italy-mediterranean-capsize/7565806.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 11 Apr 2024 16:59:56 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-5c78-08dc5a2ed50b_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በጀልባ መስጠም አደጋ 38 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ሞቱ</title>
            <description>ፍልሰተኞችን ይዛ፣ ትላንት ሰኞ ወደ የመን በመጓዝ ላይ የነበረች ጀልባ ሰጥማ የ38 ኢትዮጵያውያን ተሳፋሪዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ።




አደጋው የደረሰው በጅቡቲ የባሕር ዳርቻ እንደኾነ፣ በአገሪቱ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡


የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ በአደጋው ማዘኑን ገልጿል፡፡ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አቶ ነብዩ ተድላ፣ በሕገ ወጥ መንገድ ወደ ሳዑዲ አረቢያ የገቡ ዜጎችን ለማስመለስ ጥረት በሚደረግበት ወቅት አደጋው መድረሱ፣ የችግሩን አሳሳቢነት ያመለክታል፤ ብለዋል፡፡


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7563154.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7563154.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 09 Apr 2024 21:46:26 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-2207-08dc58c46a96_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የስፓኝ የባሕር ጠረፍ ጠባቂዎች የ73 ፍልሰተኞችን ሕይወት አዳኑ</title>
            <description>የስፓኝ የባሕር ጠረፍ ጥበቃ አገልግሎት ሠራተኞች ትላንት ኅሙስ ከእንጨት በተሠራ ጀልባ ተሳፍረው በካናሪ ደሴቶች ላይ ይጓዙ የነበሩ 73 ስደተኞችን ህይወት አድነዋል።


ከሥፍራው የተገኙት የቪዲዮ ምስሎች፣ የባሕር ጠረፍ ጠባቂዎቹ የእንጨት ጀልባዋን ጎትተው ግራን ካናሪያ ደሴት ላይ ወደሚገኘው የአርጊንጊን ወደብ ከወሰዱ በኋላ፣ የተወሰኑ ጉዳት የደረሰባቸውን ፍልሰተኞች እና አንድ ሕፃን ሲረዱ አሳይተዋል።


በተያዘው የአውሮፓውያኑ 2024 ዓም ከጥር 1 እስከ መጋቢት 31 ባለው ጊዜ ውስጥ አደገኛውን የባሕር ጉዞ አልፈው ወደብ ላይ የደረሱ ሰዎች ቁጥር 13 ሺሕ 115 ሲደርስ፣ ይህም አሃዝ 2 ሺሕ 178 ፍልሰተኞች ከተመዘገቡበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ጭማሬ ማሳየቱን የስፓኝ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።


የአውሮፓ ኅብረት የድንበር...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/spanish-coast-guard-rescues-/7558388.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/spanish-coast-guard-rescues-/7558388.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 05 Apr 2024 19:01:56 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-e3ba-08dc5589926d_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኒው ዮርክ የደረሱት የሴኔጋል ፍልሰተኞች ፈተና</title>
            <description>ከሁለት ዓመታት በፊት ጀምሮ፣ ከቬንዙዌላ እና ከሌሎችም የላቲን አሜሪካ ሀገራት በመጡ ፍልሰተኞች የተጥለቀለቀቸው የኒው ዮርክ ከተማ፣ ባለፈው አንድ ዓመት ደግሞ በሦስት እጥፍ ጭማሪ ያሳዩትንና ከምዕራብ አፍሪካ የመጡትን ፍልሰተኞች በማስተናገድ ላይ ትገኛለች።


አረን ራነን ከኒው ዮርክ ከተማ የላከውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ⤵️ 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/west-african-migrants-find-that-struggles-continue-after-arriving-in-new-york-/7538405.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/west-african-migrants-find-that-struggles-continue-after-arriving-in-new-york-/7538405.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 22 Mar 2024 16:35:08 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-c25f-08dc49448936_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከሊቢያ የተነሱ ፍልሰተኞች ሜዲቴራኒያን ባህር ላይ ሰጥመው ሞቱ</title>
            <description>ሊቢያን ለቀው ይጓዙ ከነበሩ ፍልስተኞች መካከል 50 የሚጠጉ ፍልሰተኞች ሜዲቴራኒያን ባህር ላይ ሰጥመው መሞታቸውን ኤስ ኦ ኤስ ሜድትሬኒያን የተባለው ነፍስ አድን ድርጅት ዛሬ ሐሙስ አስታወቀ፡፡


ባላፈው ሳምንት በሜዲቴራኒያን ባህር ላይ ከተገለበጠችው ጀልባ የተረፉት ሰዎች፣ ከሊቢያ አብረዋቸው ጉዞ ከጀመሩት 75 ሰዎች መካከል 50 የሚሆኑት የደረሱበት እንዳልታወቀ መናገራቸውን ድርጅቱ ገልጿል፡፡


በባህር ላይ ቅኝት የሚያደርገው የአውሮፓ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርከብ ትናንት ረቡዕ 25 ሰዎች የያዘችውን ትንሽ ጀልባ ተመልክቷል።


በውስጡ ከነበሩት ሰዎች መካከል ራሳቸውን የሳቱት ሁለት ሰዎች ለህክምና ወደ ጣሊያን ወታደራዊ ሆስፒታል የተላኩ ሲሆን የተቀሩት 23ቱ በከባድ ሁኔታ ላይ የሚገኙ፣ የደከሙና በጀልባዋ ላይ በነበረው ነዳጅ ፣ ቃጠሎ የደረሰባቸው እንደሆነ ዘገባው...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ap-eu-migrants-europe-3rd-ld-writethru/7528156.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ap-eu-migrants-europe-3rd-ld-writethru/7528156.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 14 Mar 2024 22:52:32 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-ca0c-08dc446002a9_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሊቢያ ለብርቱ እንግልት ተዳርገው ከለላ ፍለጋ ላይ ከነበሩ ፍልሰተኞች 97ቱ ጣሊያን ገቡ</title>
            <description>በጣሊያን መንግሥት እና በሌሎች በርካታ ድርጅቶች መካከል የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ ሊቢያ ውስጥ የነበሩ ቁጥራቸው አንድ መቶ የሚጠጋ ፍልሰተኞች ትናንት ማክሰኞ ጣሊያን ገብተዋል። ከዚህም ውስጥ በርካቶቹ ሴቶች እና ህጻናት የሆኑባቸው የኤርትራ፣ የኢትዮጵያ፣ የሶሪያ፣ የሶማሊያ እና የደቡብ ሱዳን ተወላጆች ይገኙባቸዋል።


ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/first-2024-humanitarian-corridor-brings-97-refugees-to-italy-ap/7516428.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/first-2024-humanitarian-corridor-brings-97-refugees-to-italy-ap/7516428.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 06 Mar 2024 22:05:56 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-feec-08dc3e1002d3_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፍልሰተኞችን ለመታደግ የሚደረገው ጥረት በባሕር ጠረፍ ጠባቂዎች መስተጓጎሉ ተገለፀ</title>
            <description>በሜዲትራኒያን ባሕር ላይ ለአደጋ የተጋለጡ ፍልሰተኞችን በማዳን ሥራ በተሰማሩ ሠራተኞች ላይ የሊቢያ የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች የሚሰዝሯቸው የማስፈራሪያ ጥቃቶች፣ ለአንድ ፍልሰተኛ ህይወት ማለፍ ምክኒያት እንደሆነ የጀርመን የበጎ አድራጎት ድርጅት አስታወቀ።


ኤስኦኤስ ሂውማኒቲ የተሰኘው በሰብአዊነት ላይ የሚሠራው የጀርመን በጎ አድራጎት ድርጅት፣ ቅዳሜ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ የሊቢያ ባህር ጠረፍ ጠባቂዎች፣ ለሕይወት አስጊ በሆነው የነፍስ ማዳን ሥራ ወቅት ተኩስ በመክፈታቸው ምክኒያት በተቀሰቀሰ ሁከት  ለአደጋ የተጋለጡ ፍልሰተኞችን የማዳን ሥራን ማስተጓጎላቸውን ገልጿል።  


ድርጅቱ ሦስት በአግባቡ ባልተሠሩ ጀልባዎች ላይ ተሳፍረው ወደ አውሮፓ ለማቅናት ጥረት በማድረግ ላይ ከነበሩት ፍልሰተኞች በርካቶቹ ወደ ባሕሩ ለመዝለል መገደዳቸውን አመልክቷል።


በነፍስ አድን ጥረቱ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/migrants-jump-in-the-sea-as-libyan-coast-guard-tries-to-prevent-rescue/7514617.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/migrants-jump-in-the-sea-as-libyan-coast-guard-tries-to-prevent-rescue/7514617.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 05 Mar 2024 19:52:16 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-e95f-08db2bba6ce7_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፍልሰተኞችን ያሳፈረው መርከብ ሲሲሊ ወደብ ደረሰ</title>
            <description>ዋሽንግተን ዲሲ — ከስምንት መቶ በላይ ፍልሰተኞችን ከሜድትራኒያን ባህር ህይወታቸውን አትርፎ፣ አሳፍሮ ባህሩ ላይ ሲጠባበቅ የቆየው የጀርመን የሰብዓዊ ርዳታ መርከብ ከጣሊያን ባለሥልጣናት ፈቃድ አግኝቶ ሲሲሊ ወደብ መድረሱ ተገለጸ። 


ሲአይ የተባለው ግብረ ሰናይ ድርጅት ያሰማራው ሲአይፎር የተባለው መርከብ ከትናንት በስቲያ ምዕራብ ሲሲሊ ትራፓኒ ወደብ ገብቷል። አብዛኞቹ አዋቂዎቹ ፍልሰተኞች ለጥንቃቄ ለኮቪድ-19 ማቆያ ወደተመደበ መርከብ የሚዛወሩ ሲሆን ከአንድ መቶ ስድሳ በላይ የሚሆኑ ህፃናት ደግሞ የብሱ ላይ ወዳሉ  ወደመጠለያዎች እንደሚገቡ ተገልጿል።


የጀርመኑ ነፍስ አድን መርከብ ላይ ከነበሩት ፍልሰተኞች መካከል ግማሽ የሚሆኑት በወሩ መጀመሪያ ላይ እየሰጠመ ከነበረ የእንጨት ጀልባ ላይ የተደረሰላቸው ሲሆኑ የተቀሩት ደግሞ በተለያዩ የነፍስ አድን መርከብ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/migrants-reaches-Sicilian-port/6306173.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/migrants-reaches-Sicilian-port/6306173.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 09 Nov 2021 19:24:44 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/ede5e9db-c2a8-4128-9d92-e31b5b4aecbf_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፍልሰተኞች ከመስጠም ዳኑ</title>
            <description>ዋሺንግተን ዲሲ — ከትናንት በስተያ ቅዳሜ በሜዲትራኒያን ባህር አደጋ ላይ የነበሩ ቢያንስ ስድሳ አምስት የሚሆኑ ስደተኞች የኢጣሊያ ዕቃ ጫኝ መርከብ ደርሶላቸው ህይወታቸውን ማትረፉ ተዘገበ።


የአሶ ቬንቲኖቬ መርከበኞች ሲናገሩ የሚበዙት በተዳከመ የእንጨት ጀልባ ተሳፍረው የነበሩት ሴቶች እና ልጆች መሆናቸውን ገልጸው በመልካም የጤና ሁኔታ ላይ እንዳሉ ገልጸዋል።


መጠን በላይ የተጨናነቀው ጀልባ ሞተሩ ተበላሽቶ ባህሩ ላይ ሲዋልል፤ ሲበርድ የተባለው የበጎ አድራጎት ድርጅት ሜዲትራኒያን ባህር መሃል ላይ አደጋ ላይ ያሉ ፍልስተኞችን እንዲቃኝ የሚያሰማራው አውሮፕላን እንዳየው ተገልጿል።


ፍልሰተኞቹ አንዳቸውም ውሃ ላይ መንሳፈፊያ ሰደሪያ ያልለበሱ እንደነበሩ መርከበኞቹ ገልጸዋል። በሌላም በኩል ባለፈው ቅዳሜ ሌሊት የስፔይን ሲቪላዊ የባህር ጥበቃ አገልግሎት አርባ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/italian-vessel-rescues-65-from-migrant-boat-fleeing-libya-10-4-2021/6256371.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/italian-vessel-rescues-65-from-migrant-boat-fleeing-libya-10-4-2021/6256371.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 04 Oct 2021 17:14:11 +0300</pubDate>
            <category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/cb68f802-b0c2-4ddc-bf7c-4867e03fd190_cx0_cy4_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በጀርመን አንጌላ መርከልን ማን እንደሚተካ የሚወስነው የፓርላማ ምርጫ ተካሄደ</title>
            <description>ለአስራ ስድስት ዐመት ጀርመንን የመሯትአንጌላ መርከል ይሰናበታሉ። የህዝብ አስተያየቶች መርከልን ለመተካት የቀረቡት ዕጩዎች ብርቱ ፉክክር ላይ መሆናቸውን አሳይተዋል።


ስድሳ ሚሊዮኑ የጀርመን ብቁ መራጭ ዛሬ አዲስ የምክር ቤት አባላቱን ሲመርጥ ውሏል። የዚህ ምርጫ ውጤት በአውሮፓ ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ የሆነችውን ሃገር ለአስራ ስድስት ዐመት የመሩዋትን አንጌላ መርከልን ማን እንደሚተካ ይወስናል።


በአርሚን ላቼት የሚመራው ቀኝ ዘመሙ የመርከል ክሪስቲያን ዲሞክራቶች አንድነት ፓርቲ እና በተሰናባቹ ምክትል ቻንስለር ኦላፍሾልዝ የሚመሩት ግራ ዘመሞቹ ሶሻል ዲሞክራቶች እጅግ ተቀራራቢ በሆነ የመራጭ ድጋፍ በብርቱ ፉክክር ተጣምደዋል።


በቅርቡ በወጡ የመራጭ አስተያየት ግምገማዎች መሰረት ሶሻል ዲሞክራቶች በጥቂት የድምጽ ብልጫ እየመሩሲሆን የተፈጥሮ አካባቢ ደህንነት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/german-parliament-election-angela-merkel/6246305.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/german-parliament-election-angela-merkel/6246305.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 26 Sep 2021 22:24:27 +0300</pubDate>
            <category>ዓለምአቀፍ</category><category>ዜና</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/7616b572-84a7-4a7f-a5a3-9249c44b9394_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያ መንግሥት መግለጫ በረድኤት ሠራተኞች ላይ ጫና እንደሚያሳድር ዩ.ኤስ. አይ. ዲ ገለፀ</title>
            <description>ዋሺንግተን ዲሲ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5970752.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5970752.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 19 Jul 2021 08:57:23 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a7195911-a0d8-4471-adb7-0ba907aa1503_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለሰብዓዊ ረድኤት ሥራ ከአዲስ አበባ መቀሌ በረራ ማድረጉ ታወቀ</title>
            <description>የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) በትግራይ ክልል ለሚገኙ የሰብዓዊ ረድኤት ፈላጊዎች በፍጥነት እርዳታ ለማድረስ እንዲያግዘው የአየርበረራ ለማግኘት በጠየቀው መሰረት ከአዲስ አበባ ወደ መቀሌ በረራ እንዲያደርግ እንደተፈቀደለትና ቅዳሜ ሐምሌ 10/2013 ዓ.ም በረራማድረጉን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ከምስል ጋር አያይዞ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።


አያይዞም መንግሥት የእርዳታ ሥራው በተቀላጠፈ መንገድ እንዲደረግ አስፈላጊውን ሁሉ ያመቻቻል ብሏል። በሌላ በኩል  በዚሁ ጉዳይ ላይየኢዜአ ምንጮቹን ጠቅሶ ባስነበበው ዘገባ  ከአዲስ አበባ ወደ መቀሌ በተደረገው በረራ በምግብና ስነ-ምግብ አቅርቦት ለሚሳተፉ በክልሉከሚገኙ ወረዳዎች መካከል በ21 ወረዳዎች ለሚሠሩ ሠራተኞች ደመወዝ ፣ ለስራ ማስኬጃ፣ ለምግብ ቁሳቁስ መጫኛና ማውረጃ የሚውልገንዘብ መሆኑ ምንጮች ጠቁመዋል። አውሮፕ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5970750.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5970750.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 19 Jul 2021 08:53:06 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/677db18a-48f4-4e65-bc05-49a54f507b83_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ትግራይን እያስተዳድሩ ያሉ ኃይሎች የኢትዮጵያ ወታደሮችን መልቀቃቸውን ገለፁ</title>
            <description>ዋሺንግተን ዲሲ  — ትግራይ ክልልን እያስተዳደሩ ያሉ ኃይሎች ይዘዋቸው የነበሩ 1,000 የመንግሥት ወታደሮችን መልቀቃቸውን የሕወሓት መሪ ዶ/ር ደብረጽዮን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5970748.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5970748.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 19 Jul 2021 08:48:17 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0d1bd986-3326-416d-b11c-800baa5881cc_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሞት በሜዲትራንያን ባህር</title>
            <description>ዋሺንግተን ዲሲ — ስደተኞችና ፍልሰተኞች በሀገሮቻቸው ከሚገጥሟቸው ግጭቶች፣ ወከባዎችና የኢኮኖሚ ችግር ሸሽተው በማዕከላዊ ሜዲትራንያን ባህር በኩል ወደ አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ጥረት የሚሞቱት ሰዎች ብዛት እየጨመረ እንደሄደ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አገልግሎቶች እየገለጹ መሆኑን ሊሳ ሽላይን ከጄኔቫ በላከችው ዘገባ ጠቁማለች።


ካለፈው ጥር ወር አንስቶ፣ አደገኛ በሆነው የማዕከላዊ ሜዲትራንያን ባህር መስመር በኩል፣ አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ጥረት፣ ቢያንስ 500 የሚሆኑ ሰዎች ህይወታቸውን እንዳጡ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አገልግሎቶች ጠቁሟል።


ባለፈው ዓመት በዚሁ ጊዜ ወደ አውሮፓ ለመግባት ባደረጉት ጥረት 150 ሰዎች ነበር የሞቱት።


130 የሚሆኑት ባለፈው ወር፣ በሊብያ የባህር ጠረፍ ላይ በደረሰ የመርከብ አደጋ ህይወታቸው አልፏል።...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5880947.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5880947.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 06 May 2021 22:05:00 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/1fbabb7d-5298-4a1f-a7a4-3108e3f238df_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>