<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/4624</link>
        <description>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/4624</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Sat, 25 Apr 2026 04:30:15 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zuuoq_eppiqv" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>በጀልባ አደጋ ዘጠኝ ፍልሰተኞች ሞቱ</title>
            <description>ሜዲትሬንያን ባሕርን አቋርጠው ወደ አውሮፓ ለመሻገር በመሞከር ላይ የነበሩ ፍልስተኞች፣ ጀልባቸው ተገልብጦ አንድ ሕፃንን ጨምሮ ዘጠኙ ሲሞቱ፣ 15 የሚሆኑት ደግሞ የደረሱበት አለመታወቁን የጣሊያን የባሕር ጠረፍ ጥበቃ አስታውቋል።


ከላምፔዱሳ ደሴት 50 ኪ.ሜ. ላይ ማዕበል በማየሉ ትናንት ረቡዕ አደጋው ሲደርስ፣ ከማልታ የአደጋ ግዜ ሠራተኞች የትብብር ጥያቄ ደርሶት እንደነበር የጣሊያን የባሕር ጠረፍ ጥበቃ ጨምሮ ገልጿል።


ሃያ ሁለት ፍልሰተኞችን መታደጉን እንዲሁም አንድ ሕፃንን ጨምሮ የዘጠኝ ሰዎችን አስከሬን ማግኘቱን የባሕር ጠረፍ ጥበቃው አስታውቋል።


የሟቾቹ ዜግነት እስከ አሁን ያልተገለፀ ሲሆን፤ በቱኒዚያ፣ ማልታ እና ሲስሊ መካከል የምትገኘው ላምፔዱሳ ወደ አውሮፓ ለመሻገር ለሚሞክሩ ፍልሰተኞች የመጀመሪያ ማረፊያ ነች፡፡


በሌላ በኩል በላምፔዱሳ አቅራቢያ በትንሽ የእንጨት ጀልባ ላይ ሆነው ሲቀዝፉ የነበሩ 37 ፍልሰተኞችን ትናንት መታደጉን የባሕር ጠረፍ ጥበቃው ቡድን አስታውቋል።


በተያያዘ ዜና፣ ግሪክ የሶስት ታዳጊዎችን አስከሬን ማግኘቷን እና 19 ፍልሰተኞችን ደግሞ መታደጓን አስታውቃለች፡፡


ፍልሰተኞቹ ይጓዙበት የነበረው ጀልባ ከቋጥኝ ጋራ በመጋጨቱ አደጋው ሊደርስ እንደቻለ ተነግሯል።


ከአፍሪካ፣ እስያ እና መካከለኛው ምሥራቅ ወደ አውሮፓ ለመሻገር ለሚሹ ፍልሰተኞች ሌላዋ አማራጭ የሆነችው ግሪክ፣ ከ እ.አ.አ 2015 ወዲህ አንድ ሚሊዮን የሚሆኑ ፍልሰተኞች በደሴቶቿ ተቀብላለች፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/italy-mediterranean-capsize/7565806.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/italy-mediterranean-capsize/7565806.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 11 Apr 2024 16:59:56 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-5c78-08dc5a2ed50b_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በጀልባ መስጠም አደጋ 38 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ሞቱ</title>
            <description>ፍልሰተኞችን ይዛ፣ ትላንት ሰኞ ወደ የመን በመጓዝ ላይ የነበረች ጀልባ ሰጥማ የ38 ኢትዮጵያውያን ተሳፋሪዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ።




አደጋው የደረሰው በጅቡቲ የባሕር ዳርቻ እንደኾነ፣ በአገሪቱ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡


የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ በአደጋው ማዘኑን ገልጿል፡፡ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አቶ ነብዩ ተድላ፣ በሕገ ወጥ መንገድ ወደ ሳዑዲ አረቢያ የገቡ ዜጎችን ለማስመለስ ጥረት በሚደረግበት ወቅት አደጋው መድረሱ፣ የችግሩን አሳሳቢነት ያመለክታል፤ ብለዋል፡፡


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7563154.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7563154.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 09 Apr 2024 21:46:26 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-2207-08dc58c46a96_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የስፓኝ የባሕር ጠረፍ ጠባቂዎች የ73 ፍልሰተኞችን ሕይወት አዳኑ</title>
            <description>የስፓኝ የባሕር ጠረፍ ጥበቃ አገልግሎት ሠራተኞች ትላንት ኅሙስ ከእንጨት በተሠራ ጀልባ ተሳፍረው በካናሪ ደሴቶች ላይ ይጓዙ የነበሩ 73 ስደተኞችን ህይወት አድነዋል።


ከሥፍራው የተገኙት የቪዲዮ ምስሎች፣ የባሕር ጠረፍ ጠባቂዎቹ የእንጨት ጀልባዋን ጎትተው ግራን ካናሪያ ደሴት ላይ ወደሚገኘው የአርጊንጊን ወደብ ከወሰዱ በኋላ፣ የተወሰኑ ጉዳት የደረሰባቸውን ፍልሰተኞች እና አንድ ሕፃን ሲረዱ አሳይተዋል።


በተያዘው የአውሮፓውያኑ 2024 ዓም ከጥር 1 እስከ መጋቢት 31 ባለው ጊዜ ውስጥ አደገኛውን የባሕር ጉዞ አልፈው ወደብ ላይ የደረሱ ሰዎች ቁጥር 13 ሺሕ 115 ሲደርስ፣ ይህም አሃዝ 2 ሺሕ 178 ፍልሰተኞች ከተመዘገቡበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ጭማሬ ማሳየቱን የስፓኝ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።


የአውሮፓ ኅብረት የድንበር ጉዳዮች ድርጅት ፍሮንቴክስ እንዳስታወቀው፣ በአትላንቲክ ባሕር አድርጎ ወደ ካናሪ ደሴቶች የሚወስደው የባሕር መስመር በአሁኑ ወቅት ፍልሰተኞች ከምዕራብ አፍሪካ ተነስተው ወደ አውሮፓ ኅብረት አገሮች ለመግባት በሚያደርጉት ጉዞ ዋናው እና በርካታ ጉዞዎች የሚደረግበት መንገድ ነው።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/spanish-coast-guard-rescues-/7558388.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/spanish-coast-guard-rescues-/7558388.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 05 Apr 2024 19:01:56 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-e3ba-08dc5589926d_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኒው ዮርክ የደረሱት የሴኔጋል ፍልሰተኞች ፈተና</title>
            <description>ከሁለት ዓመታት በፊት ጀምሮ፣ ከቬንዙዌላ እና ከሌሎችም የላቲን አሜሪካ ሀገራት በመጡ ፍልሰተኞች የተጥለቀለቀቸው የኒው ዮርክ ከተማ፣ ባለፈው አንድ ዓመት ደግሞ በሦስት እጥፍ ጭማሪ ያሳዩትንና ከምዕራብ አፍሪካ የመጡትን ፍልሰተኞች በማስተናገድ ላይ ትገኛለች።


አረን ራነን ከኒው ዮርክ ከተማ የላከውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ⤵️ 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/west-african-migrants-find-that-struggles-continue-after-arriving-in-new-york-/7538405.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/west-african-migrants-find-that-struggles-continue-after-arriving-in-new-york-/7538405.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 22 Mar 2024 16:35:08 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-c25f-08dc49448936_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከሊቢያ የተነሱ ፍልሰተኞች ሜዲቴራኒያን ባህር ላይ ሰጥመው ሞቱ</title>
            <description>ሊቢያን ለቀው ይጓዙ ከነበሩ ፍልስተኞች መካከል 50 የሚጠጉ ፍልሰተኞች ሜዲቴራኒያን ባህር ላይ ሰጥመው መሞታቸውን ኤስ ኦ ኤስ ሜድትሬኒያን የተባለው ነፍስ አድን ድርጅት ዛሬ ሐሙስ አስታወቀ፡፡


ባላፈው ሳምንት በሜዲቴራኒያን ባህር ላይ ከተገለበጠችው ጀልባ የተረፉት ሰዎች፣ ከሊቢያ አብረዋቸው ጉዞ ከጀመሩት 75 ሰዎች መካከል 50 የሚሆኑት የደረሱበት እንዳልታወቀ መናገራቸውን ድርጅቱ ገልጿል፡፡


በባህር ላይ ቅኝት የሚያደርገው የአውሮፓ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርከብ ትናንት ረቡዕ 25 ሰዎች የያዘችውን ትንሽ ጀልባ ተመልክቷል።


በውስጡ ከነበሩት ሰዎች መካከል ራሳቸውን የሳቱት ሁለት ሰዎች ለህክምና ወደ ጣሊያን ወታደራዊ ሆስፒታል የተላኩ ሲሆን የተቀሩት 23ቱ በከባድ ሁኔታ ላይ የሚገኙ፣ የደከሙና በጀልባዋ ላይ በነበረው ነዳጅ ፣ ቃጠሎ የደረሰባቸው እንደሆነ ዘገባው አመልክቷል፡፡


የኤስ ኦ ኤስ ቃል አቀባይ ፍራንሴስኮ ክሬዞ እንደተናገሩት በህይወት የተረፉት ሁሉም ወንዶች ሲሆኑ 12 የሚሆኑት ህጻናትና ሁለቱ ታዳጊ ወጣቶች ናቸው፡፡


ፍልሰተኞቹ ከሴንጋል ማሊ እና ጋምቢያ መሆናቸውም ተገልጿል። ጀልባዪቱን ተሳፍረው ከነበሩት 75 ስዎች መካከል ቢያንስ አንድ ህጻንን ጨምሮ ሴቶች ነበሩበት ተብሏል።


ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት (አይ ኦ ኤም) እንደገለጸው በዚህ ዓመት እስከ መጋቢት መጀመሪያ ድረስ 227 ሰዎች አደገኛ በሆነው በማዕከላዊ ሜዲቴራኒያን ባህር ላይ ሞተዋል፡፡


ይህ በቅርቡ ሞተዋል ወይም አድራሻ ጠፍቷል የተባሉትን ሰዎች አይጨምርም። አይ ኦ ኤም እንደገለጸው በዚህ ዓመት እስከ መጋቢት 11 ድረስ 227 ሰዎች በአደገኛው መካከለኛው የሜዲቴራኒያን ባህር መስመር ላይ ሞተዋል፡፡


ካለፈው ጥር ወር መጀመሪያ ጀምሮ ተመሳሳዩን የሜዲቴራኒያን ባህር አቋርጠው ጣልያን ከገቡት 19 ሺሕ ሰዎች መካከል 279ኙ ሞተዋል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ap-eu-migrants-europe-3rd-ld-writethru/7528156.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ap-eu-migrants-europe-3rd-ld-writethru/7528156.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 14 Mar 2024 22:52:32 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-ca0c-08dc446002a9_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሊቢያ ለብርቱ እንግልት ተዳርገው ከለላ ፍለጋ ላይ ከነበሩ ፍልሰተኞች 97ቱ ጣሊያን ገቡ</title>
            <description>በጣሊያን መንግሥት እና በሌሎች በርካታ ድርጅቶች መካከል የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ ሊቢያ ውስጥ የነበሩ ቁጥራቸው አንድ መቶ የሚጠጋ ፍልሰተኞች ትናንት ማክሰኞ ጣሊያን ገብተዋል። ከዚህም ውስጥ በርካቶቹ ሴቶች እና ህጻናት የሆኑባቸው የኤርትራ፣ የኢትዮጵያ፣ የሶሪያ፣ የሶማሊያ እና የደቡብ ሱዳን ተወላጆች ይገኙባቸዋል።


ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/first-2024-humanitarian-corridor-brings-97-refugees-to-italy-ap/7516428.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/first-2024-humanitarian-corridor-brings-97-refugees-to-italy-ap/7516428.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 06 Mar 2024 22:05:56 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-feec-08dc3e1002d3_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፍልሰተኞችን ለመታደግ የሚደረገው ጥረት በባሕር ጠረፍ ጠባቂዎች መስተጓጎሉ ተገለፀ</title>
            <description>በሜዲትራኒያን ባሕር ላይ ለአደጋ የተጋለጡ ፍልሰተኞችን በማዳን ሥራ በተሰማሩ ሠራተኞች ላይ የሊቢያ የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች የሚሰዝሯቸው የማስፈራሪያ ጥቃቶች፣ ለአንድ ፍልሰተኛ ህይወት ማለፍ ምክኒያት እንደሆነ የጀርመን የበጎ አድራጎት ድርጅት አስታወቀ።


ኤስኦኤስ ሂውማኒቲ የተሰኘው በሰብአዊነት ላይ የሚሠራው የጀርመን በጎ አድራጎት ድርጅት፣ ቅዳሜ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ የሊቢያ ባህር ጠረፍ ጠባቂዎች፣ ለሕይወት አስጊ በሆነው የነፍስ ማዳን ሥራ ወቅት ተኩስ በመክፈታቸው ምክኒያት በተቀሰቀሰ ሁከት  ለአደጋ የተጋለጡ ፍልሰተኞችን የማዳን ሥራን ማስተጓጎላቸውን ገልጿል።  


ድርጅቱ ሦስት በአግባቡ ባልተሠሩ ጀልባዎች ላይ ተሳፍረው ወደ አውሮፓ ለማቅናት ጥረት በማድረግ ላይ ከነበሩት ፍልሰተኞች በርካቶቹ ወደ ባሕሩ ለመዝለል መገደዳቸውን አመልክቷል።


በነፍስ አድን ጥረቱ 77 ፍልሰተኞችን መታደግ መቻሉን እና ቁጥራቸው የበዛ ሌሎች በኃይል ከሊቢያ የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች ጀልባ ላይ እንዲሳፈሩ መደረጋቸውን አክሎ ገልጿል። በዚህም ምክኒያት ስድስት የቤተሰብ አባላት መነጣጠላቸውን አስታውቋል። የሊቢያ የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች ቃል አቀባይ ስለ ጉዳዩ እንዲያብራሩ ለተደረጉላቸው የስልክ ጥሪዎች እና የኢሜል መልዕክቶች ምላሽ አልሰጡም።


በተያያዘ ባለፈው የአውሮፓውያኑ 2023 ከሊቢያ የተነሱ 962 ፍልሰተኞች ባሕር ላይ መሞታቸው እና ቁጥራቸው 1ሺህ563 የሚደርሱት የገቡበት ሳይታወቅ መቅረቱን ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት አይኦኤም አስታውቋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/migrants-jump-in-the-sea-as-libyan-coast-guard-tries-to-prevent-rescue/7514617.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/migrants-jump-in-the-sea-as-libyan-coast-guard-tries-to-prevent-rescue/7514617.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 05 Mar 2024 19:52:16 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-e95f-08db2bba6ce7_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፍልሰተኞችን ያሳፈረው መርከብ ሲሲሊ ወደብ ደረሰ</title>
            <description>ዋሽንግተን ዲሲ — ከስምንት መቶ በላይ ፍልሰተኞችን ከሜድትራኒያን ባህር ህይወታቸውን አትርፎ፣ አሳፍሮ ባህሩ ላይ ሲጠባበቅ የቆየው የጀርመን የሰብዓዊ ርዳታ መርከብ ከጣሊያን ባለሥልጣናት ፈቃድ አግኝቶ ሲሲሊ ወደብ መድረሱ ተገለጸ። 


ሲአይ የተባለው ግብረ ሰናይ ድርጅት ያሰማራው ሲአይፎር የተባለው መርከብ ከትናንት በስቲያ ምዕራብ ሲሲሊ ትራፓኒ ወደብ ገብቷል። አብዛኞቹ አዋቂዎቹ ፍልሰተኞች ለጥንቃቄ ለኮቪድ-19 ማቆያ ወደተመደበ መርከብ የሚዛወሩ ሲሆን ከአንድ መቶ ስድሳ በላይ የሚሆኑ ህፃናት ደግሞ የብሱ ላይ ወዳሉ  ወደመጠለያዎች እንደሚገቡ ተገልጿል።


የጀርመኑ ነፍስ አድን መርከብ ላይ ከነበሩት ፍልሰተኞች መካከል ግማሽ የሚሆኑት በወሩ መጀመሪያ ላይ እየሰጠመ ከነበረ የእንጨት ጀልባ ላይ የተደረሰላቸው ሲሆኑ የተቀሩት ደግሞ በተለያዩ የነፍስ አድን መርከብ እንቅስቃሴዎች የተደረሰላቸው መሆናቸው ተመልክቷል።


የጀርመኑ መርከብ ያሳፈራቸው አብዛኞቹ ፍልሰተኞች የምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች እንዲሁም የግብጽ ወይ የሞሮኮ ተወላጆች በጣሊያን የህጻናት አድን ድርጅት ባለሥልጣኑ ጂዮቫኒ ዲ ቤኔዲቶ ገልጸዋል።


ይህ በእንዲህ እንዳለ ሦስት መቶ ስምንት ፍልሰተኞችን ያሳፍረው ኦሽን ቫይኪንግ የተባለው መርከብ ከሲሲሊ በስተደቡብ የምትገኘው ላምፔዱሳ ወደብ ለመግባት አሁንም ፈቃድ እየጠበቀ መሆኑ በዘገባው አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ አስታውቋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/migrants-reaches-Sicilian-port/6306173.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/migrants-reaches-Sicilian-port/6306173.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 09 Nov 2021 19:24:44 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/ede5e9db-c2a8-4128-9d92-e31b5b4aecbf_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፍልሰተኞች ከመስጠም ዳኑ</title>
            <description>ዋሺንግተን ዲሲ — ከትናንት በስተያ ቅዳሜ በሜዲትራኒያን ባህር አደጋ ላይ የነበሩ ቢያንስ ስድሳ አምስት የሚሆኑ ስደተኞች የኢጣሊያ ዕቃ ጫኝ መርከብ ደርሶላቸው ህይወታቸውን ማትረፉ ተዘገበ።


የአሶ ቬንቲኖቬ መርከበኞች ሲናገሩ የሚበዙት በተዳከመ የእንጨት ጀልባ ተሳፍረው የነበሩት ሴቶች እና ልጆች መሆናቸውን ገልጸው በመልካም የጤና ሁኔታ ላይ እንዳሉ ገልጸዋል።


መጠን በላይ የተጨናነቀው ጀልባ ሞተሩ ተበላሽቶ ባህሩ ላይ ሲዋልል፤ ሲበርድ የተባለው የበጎ አድራጎት ድርጅት ሜዲትራኒያን ባህር መሃል ላይ አደጋ ላይ ያሉ ፍልስተኞችን እንዲቃኝ የሚያሰማራው አውሮፕላን እንዳየው ተገልጿል።


ፍልሰተኞቹ አንዳቸውም ውሃ ላይ መንሳፈፊያ ሰደሪያ ያልለበሱ እንደነበሩ መርከበኞቹ ገልጸዋል። በሌላም በኩል ባለፈው ቅዳሜ ሌሊት የስፔይን ሲቪላዊ የባህር ጥበቃ አገልግሎት አርባ ስምንት ፍልሰተኞችን አውጥቶ ሞትሪል ወደተባለች የስፔን ደሴት በማድረስ ህይወታቸውን ማትረፉ ተዘግቧል።


እአአ በ2021 ብቻ ቢያንስ 44,000 አውሮፓ ገብተን የተሻለ ኑሮ እናገኛለን በሚል ጉጉት ህይወታቸውን በህገ ወጥ አዘዋዋሪዎች እጅ ለአደጋ በማጋለጥ ከሊቢያ እና ከቱኒዥያ ሜዲትራኒያን ባህርን እንዳቋረጡ ተገልጿል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/italian-vessel-rescues-65-from-migrant-boat-fleeing-libya-10-4-2021/6256371.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/italian-vessel-rescues-65-from-migrant-boat-fleeing-libya-10-4-2021/6256371.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 04 Oct 2021 17:14:11 +0300</pubDate>
            <category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/cb68f802-b0c2-4ddc-bf7c-4867e03fd190_cx0_cy4_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በጀርመን አንጌላ መርከልን ማን እንደሚተካ የሚወስነው የፓርላማ ምርጫ ተካሄደ</title>
            <description>ለአስራ ስድስት ዐመት ጀርመንን የመሯትአንጌላ መርከል ይሰናበታሉ። የህዝብ አስተያየቶች መርከልን ለመተካት የቀረቡት ዕጩዎች ብርቱ ፉክክር ላይ መሆናቸውን አሳይተዋል።


ስድሳ ሚሊዮኑ የጀርመን ብቁ መራጭ ዛሬ አዲስ የምክር ቤት አባላቱን ሲመርጥ ውሏል። የዚህ ምርጫ ውጤት በአውሮፓ ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ የሆነችውን ሃገር ለአስራ ስድስት ዐመት የመሩዋትን አንጌላ መርከልን ማን እንደሚተካ ይወስናል።


በአርሚን ላቼት የሚመራው ቀኝ ዘመሙ የመርከል ክሪስቲያን ዲሞክራቶች አንድነት ፓርቲ እና በተሰናባቹ ምክትል ቻንስለር ኦላፍሾልዝ የሚመሩት ግራ ዘመሞቹ ሶሻል ዲሞክራቶች እጅግ ተቀራራቢ በሆነ የመራጭ ድጋፍ በብርቱ ፉክክር ተጣምደዋል።


በቅርቡ በወጡ የመራጭ አስተያየት ግምገማዎች መሰረት ሶሻል ዲሞክራቶች በጥቂት የድምጽ ብልጫ እየመሩሲሆን የተፈጥሮ አካባቢ ደህንነት ተሙዋጋቹ ግሪንስ ፓርቲ እና መሪያቸው አናሌና ቤርቦክ በሶስተኛነት ይከተላሉ። 

 

የሚመረጡት የምክር ቤት አባላት ጥምር መንግሥት ማቋቋም ሳይኖርባቸው እንደማይቀርእየተገለጸ ሲሆን ከዚያም ተያይዞ መርከልን ማን እንደሚተካ የመወሰኑም ሂደት ሳምንታት ሊወስድ ይችላል። በአሰተያየት ግምገማዎች መሰረት ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያላቸው ከሰላሳ ከመቶ ያነሰ የመራጭ ድጋፍ በመሆኑ ማናቸውም አብላጫ ድምጽ ያገኛሉ ተብሎ አይጠበቅም። 


አንጌላ መርከል ሊተኩዋቸው ከሚፎካከሩት ዕጩዎች ውስጥ ለአንዳቸውም በይፋ ድጋፋቸውን ከመግለጽ ተቆጥበው ከርመዋል። ትናንት ግን ለክሪስቲያን ዲሞክራት ፓርቲው ዕጩ አርሚን ላሼት በተደረገ የድጋፍ ስብሰባ ላይ ተገኝተዋል። መርከል ተተኪያቸው እስከሚመረጥ በተጠባባቂ ቻንስለርነት ይቆያሉ። 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/german-parliament-election-angela-merkel/6246305.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/german-parliament-election-angela-merkel/6246305.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 26 Sep 2021 22:24:27 +0300</pubDate>
            <category>ዓለምአቀፍ</category><category>ዜና</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/7616b572-84a7-4a7f-a5a3-9249c44b9394_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያ መንግሥት መግለጫ በረድኤት ሠራተኞች ላይ ጫና እንደሚያሳድር ዩ.ኤስ. አይ. ዲ ገለፀ</title>
            <description>ዋሺንግተን ዲሲ — ኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ ዓለም አቀፍ የረድኤት ድርጅቶች፤ እርዳታውን ከማስተባበር ይልቅ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይማተኮርን መርጠዋል ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት ሰሞኑን ላሰማው ቅሬታ የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ (ዩ.ኤስ. አይ. ዲ) ቃል አቀባይ ትላንት በሰጡት ምላሽ “የኢትዮጵያ መንግሥት ያሰማው ማስፈራሪያ ትግራይ ውስጥ እየተንቀሳቀሱ ባሉ እርዳታ አድራሽድርጅቶች ላይ ጫና ያሳድራል” ብለዋል።


ሰብዓዊ ድርጅቶች ለዕለት ደራሽ እርዳታ የሚያደርሱት በሰብዕና መርሆዎች መሰረት መሆኑን የጠቆመው የኤጀንሲው ምላሽ “እንዲህ ዓይነትመግለጫዎች ሕይወታቸውን ለአደጋ አጋልጠው እየሠሩ ባሉ በጎ አድራጊዎች ላይ የአደጋውን ስጋት ያባብሰዋል” ብለዋል።


መልዕክቱ እርዳታ ማድረሱን ፈታኝ እንደሚያደርገው የቃል አቀባዩ መግለጫ አመልክቷል። በጎ አድራጊዎቹ ሥራቸውን እንዳይሠሩየሚያደናቅፋቸው ማንኛውም ነገር ሕይወት የማዳኑን ሥራ ይበልጥ እንደሚያከብደውና እንዲሁም አሳሳቢ የሆነውን ሁኔያእንደሚያባብሰው አሳስቧል።


በክልሉ ውስጥ ካለው 6 ሚሊዮን ሰው 5 ሚሊዮኑ አፋጣኝ እርዳታ እንደሚያስፈልገውና 900 ሺሕ የሚሆነው ሰው ለበረታ የረሃብ አደጋመጋለጡን ቃል አቀባዩ አክለው ጠቁመዋል።


ሁሉም ወገኖች የረድኤት ድርጅቶቹ መተላለፍ እንዲችሉ እንዲያደርጉ ኤጀንሲያቸው መጠየቁን እንደሚቀጥል አመላክተው፤ “እርዳታውፈጥኖ ያለማቋረጥ እና ያለመደናቀፍ መድረስ አለበት” ብለዋል።


“በተጨማሪም የነዳጅ፣ የኤሌትሪክ የቴሌኮምዩኒኬሽንስና የባንክ አገልግሎቶች ፈጥነው መመለስ ይኖርባቸዋልም” ብለዋል ቃል አቀባዩ።


በመጨረም ሁሉም ወገኖች የፀብ ሁኔታዎችን እንዲያቆሙና ተኩስ ለማቆም እንዲደራደሩ ጥሪ አሰምተዋል።


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5970752.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5970752.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 19 Jul 2021 08:57:23 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a7195911-a0d8-4471-adb7-0ba907aa1503_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለሰብዓዊ ረድኤት ሥራ ከአዲስ አበባ መቀሌ በረራ ማድረጉ ታወቀ</title>
            <description>የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) በትግራይ ክልል ለሚገኙ የሰብዓዊ ረድኤት ፈላጊዎች በፍጥነት እርዳታ ለማድረስ እንዲያግዘው የአየርበረራ ለማግኘት በጠየቀው መሰረት ከአዲስ አበባ ወደ መቀሌ በረራ እንዲያደርግ እንደተፈቀደለትና ቅዳሜ ሐምሌ 10/2013 ዓ.ም በረራማድረጉን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ከምስል ጋር አያይዞ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።


አያይዞም መንግሥት የእርዳታ ሥራው በተቀላጠፈ መንገድ እንዲደረግ አስፈላጊውን ሁሉ ያመቻቻል ብሏል። በሌላ በኩል  በዚሁ ጉዳይ ላይየኢዜአ ምንጮቹን ጠቅሶ ባስነበበው ዘገባ  ከአዲስ አበባ ወደ መቀሌ በተደረገው በረራ በምግብና ስነ-ምግብ አቅርቦት ለሚሳተፉ በክልሉከሚገኙ ወረዳዎች መካከል በ21 ወረዳዎች ለሚሠሩ ሠራተኞች ደመወዝ ፣ ለስራ ማስኬጃ፣ ለምግብ ቁሳቁስ መጫኛና ማውረጃ የሚውልገንዘብ መሆኑ ምንጮች ጠቁመዋል። አውሮፕላኑም ትላንቱኑ መመለሱን ዘግቧል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5970750.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5970750.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 19 Jul 2021 08:53:06 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/677db18a-48f4-4e65-bc05-49a54f507b83_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ትግራይን እያስተዳድሩ ያሉ ኃይሎች የኢትዮጵያ ወታደሮችን መልቀቃቸውን ገለፁ</title>
            <description>ዋሺንግተን ዲሲ  — ትግራይ ክልልን እያስተዳደሩ ያሉ ኃይሎች ይዘዋቸው የነበሩ 1,000 የመንግሥት ወታደሮችን መልቀቃቸውን የሕወሓት መሪ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በሳተላይት ስልክ እንደተናገሩ ሮይተርስ ዘገበ። 


ወታደሮቹ በደቡብ ትግራይ ከአማራ ክልል ጋር ወደሚያዋስን አካባቢመሸኘታቸውን ዶ/ር ደብረ ጽዮን ቢናገሩም ወታደሮቹን የመልቀቁን ድርድር እንዴት እንደተካሄደና ማን እንደተቀበላቸው እንዳልነገሩትየዜና አገልግሎቱ አመልክቷል። 


ከአምስት ሺሕ በላይ ወታደሮች አሁንም በእጃቸው እንደሚገኙ፣ በእጃችን አሉ የሚሏቸው ከፍተኛ የጦርአዛዦችን እንደማይለቁና ለፍርድ እንደሚያቀርቧቸው መግለፃቸውን ሮይተርስ አክሎ ዘግቧል። 


ከኢትዮጵያ መከላከያ ኃይሎች ቃል አቀባይእና ትግራይን በሚመለከት ከተቋቋመው ግብረ ኃይል እንዲሁም ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ሙከራእንዳልተሳካለት የጠቆመው ሮይተርስ የአማራ ክልል አስተዳደር ቃል አቀባይ ግን መረጃ እንደሌላቸው መናገራቸውን ገልጿል።


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5970748.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5970748.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 19 Jul 2021 08:48:17 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0d1bd986-3326-416d-b11c-800baa5881cc_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሞት በሜዲትራንያን ባህር</title>
            <description>ዋሺንግተን ዲሲ — ስደተኞችና ፍልሰተኞች በሀገሮቻቸው ከሚገጥሟቸው ግጭቶች፣ ወከባዎችና የኢኮኖሚ ችግር ሸሽተው በማዕከላዊ ሜዲትራንያን ባህር በኩል ወደ አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ጥረት የሚሞቱት ሰዎች ብዛት እየጨመረ እንደሄደ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አገልግሎቶች እየገለጹ መሆኑን ሊሳ ሽላይን ከጄኔቫ በላከችው ዘገባ ጠቁማለች።


ካለፈው ጥር ወር አንስቶ፣ አደገኛ በሆነው የማዕከላዊ ሜዲትራንያን ባህር መስመር በኩል፣ አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ጥረት፣ ቢያንስ 500 የሚሆኑ ሰዎች ህይወታቸውን እንዳጡ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አገልግሎቶች ጠቁሟል።


ባለፈው ዓመት በዚሁ ጊዜ ወደ አውሮፓ ለመግባት ባደረጉት ጥረት 150 ሰዎች ነበር የሞቱት።


130 የሚሆኑት ባለፈው ወር፣ በሊብያ የባህር ጠረፍ ላይ በደረሰ የመርከብ አደጋ ህይወታቸው አልፏል። ሰዎቹ ለህልፈት የተዳረጉት፣ በባህሩ የነበሩት የመድህን መርከቦች፣ አድኑን ለሚለው ጥሪያቸው፣ ምላሽ ባለመስጠታቸው ነው ሲል፣ ዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት አስገንዝቧል።


የተባበሩት መንግሥታቱ የፍልሰተኞች አገልግሎት ቃል አቀባይ ካርሎታ ሳሚ፣ ጥሩነቱ በቅርቡ በከባድ ሁኔታ ይጓዙ የነበሩ፣ 1,500 የሚሆኑ ሰዎች ያሰሙት የአድኑን ጥሪ፣ ምላሽ እንዳገኘ ተናግረዋል።


የኢጣልያ ጠረፍ ጥበቃ ክፍል፣ ከአንድ ሺህ በላይ የሚሆኑ ፍልሰተኞችን ከአደጋ በማትረፉ፣ ባለፈው ቅዳሜ ትራፓኒ በተባለው የሲሲሊ ወደብ፣ ለመግባት እንደቻሉ ታውቋል።


የባህር ጥበቃ የተባለው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት፣ ባለፈው ማክሰኞ 450 ሌሎች ስደተኞችንና ፍልሰተኞችን ሲያድን በዐይናቸው ማየታቸውን፣ ቃል አቀባይዋ ተናግረዋል። አብዛኖቹ ከሊብያ በደካማ ጀልባዎች የተነሱ እንደሆነና በተደጋግሚ የአድኑን ጥሪ ሲያቀርቡ እንደነበር፣ ካርሎታ ሳሚ ጠቁመዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5880947.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5880947.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 06 May 2021 22:05:00 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ፍልሰት ወደ አውሮፓ ሞት ወይም ሽረት</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/1fbabb7d-5298-4a1f-a7a4-3108e3f238df_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>