<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>ረሃብ በአፍሪካ - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/4688</link>
        <description>በድፍን አፍሪካ ሚሊዮኖች የሚበሉት የላቸውም፡፡ ሶማሊያን የበረታ ረሃብና ቸነፈር እያሰጋት ነው፡፡ ኬንያ በድርቅ ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ውስጥ ለመግባት ተገድዳለች፡፡ የሰሜን ምሥራቅ ናይጀሪያ አካባቢ ረሃብ ጠንቶባታል፡፡ በአንዳንድ የደቡብ ሱዳን አካባቢዎች ጠኔና ቸነፈር መግባቱ በይፋ ተነግሯል፡፡ በድፍን አፍሪካ ለምግብ መጥፋት አደጋ ከተጋለጡት በአሥሮች ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ቁጥራቸው እጅግ</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>ረሃብ በአፍሪካ - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/4688</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Sat, 25 Apr 2026 04:25:02 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zu-oqvepviqv" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>የእህል ርዳታ ወደ ቡግና ወረዳ መጓጓዝ መጀመሩን ባለሥልጣናት አስታወቁ</title>
            <description>በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ የሀገር ሽማግሌዎችና የኃይማኖት አባቶች በረኅብ ለተጎዱ ሰዎች የርዳታ እህል ወደ ወረዳው እንዲገባ ከመንግሥትና ከፋኖ ታጣቂዎች ጋራ ስምምነት ማድረጋቸውን አስታወቁ።


በስምምነቱ መሰረትም የርዳታ እህሉ እየገባ መኾኑን አንድ የኃይማኖት አባት ተናግረዋል። የሰሜን ወሎ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ይመር ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃል፣ አካባቢው በፋኖ ታጣቂዎች ስር በመኾኑ ለተከሰተው የምግብ እጥረት መንግሥት በቶሎ ምላሽ መስጠት አልቻለም ብለዋል።


የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎችና የኃይማኖት አባቶች በአደረጉት ጥረትም ከ110 ሺሕ በላይ ለሆኑ ሰዎች ከ16 ሺሕ ኩንታል በላይ የርዳታ እህል ወደ ስፍራው እየተጓጓዘ መኾኑን አስታውቀዋል።


የወረዳው ነዋሪ ያለበትን የምግብና የጤና ችግር ለፋኖ ታጣቂዎችና ለመንግሥት አካላት ለማስረዳት ከተመረጡት 18 ግለሰቦች መካከል “አንዱ ነበርኩ” ያሉት ቄስ ገብረ እግዚአብሔር ዝናቤ ይርዳው በአካባቢው የመንግሥት ባለሥልጣናትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በተደረሰው ስምምነት መድኃኒቶችንና አልሚ ምግቦች ወደ ወረዳው መግባት መቻላቸውን ተናግረዋል።




የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ሁለት የአይና ቡግና ወረዳ ነዋሪ እናቶች፣ ለሕፃን ልጆቻቸው አልሚ ምግቦችን ከጤና ተቋማት ተቀብለው ወደ ቤታቸው እየሄዱ እንደሆነ ተናግረዋል።


በሌላ በኩል አዲስ አበባ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ዛሬ ታኅሣሥ 11 ቀን 2017 ዓ.ም በፌስ ቡክ ገጹ በአወጣው መግለጫ በቡግና ወረዳ የምግብ እጥረት ቀውስ ሰለመኖሩ የወጡ ሪፖርቶችን እየተከታተለ መኾኑን አመልክቷል።




&quot;ሁኔታውን መከታተላችንን እና መገምገማችንን እንቀጥላለን&quot; ያለው መግለጫው ቀውሱ መወገዱን ለማረጋገጥ እንደሚሠራም ጠቅሷል።


ኤምባሲው በመግለጫው ቀውሱን በተመለከተ ዝርዝር መረጃዎችን አላካተተም።


የኢትዮጵያን ሕዝብ ለመደገፍ ፣ አጋሮቹ በአኹኑ ሰዓት በችግሩ በተጠቁት አብዛኞቹ ስፍራዎች የምግብ እና አልሚ ንጥረ ምግቦች ስርጭትን ያጠናከሩ መሆናቸውንም አክሏል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/food-aid-is-being-transported-to-people/7908905.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/food-aid-is-being-transported-to-people/7908905.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 20 Dec 2024 22:50:35 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (አስቴር ምስጋናው)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/BF762538-4979-41D0-95A7-E875E7FFE725_cx0_cy8_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>“ሱዳን ትልቁን ሰብአዊ ቀውስ የተሸከመች ሀገር ሆናለች” - ዓለም አቀፍ ነፍስ አድን ኮሚቴ</title>
            <description>በሱዳን በጦር ሠራዊቱ እና በፈጥኖ ደራሽ ኅይሎች መካከል ለ20 ወራት የዘለቀውን አስከፊ ጦርነት ተከትሎ “እስከዛሬ ከተመዘገቡት ሁሉ ትልቁን ሰብአዊ ቀውስ የተሸከመች ሀገር ሆናለች” ሲል የዓለም ነፍስ አድን ኮሚቴ አመለከተ፡፡


በተቃናቃኞቹ ጀኔራሎች መካከል በቀጠለው ጦርነት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ 12 ሚሊዮን የሚሆኑት ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን የተቋሙ ዘገባ ጠቅሷል፡፡


ወደ ዘጠኝ ሚሊዮን የሚጠጉት በሀገር ውስጥ የተፈናቀሉ ናቸው፡፡ አብዛኛዎቹ መሠረተ ልማቶች በወደሙባቸው አካባቢዎች የሠፈሩ ሲሆን የጅምላ ረሃብ ሥጋትም ተጋርጦባቸዋል።


ዓለም አቀፉ ድርጅት በሱዳን ወደ 26 ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ ለከባድ ረሃብ መጋለጡን ገልጾ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ታይቶ የማይታወቅ ሰብአዊ ቀውስ ገጥሟታል ብሏል፡፡


“ከዓለም ሕዝብ ከአንድ ከመቶ ያነሰ የሕዝብ ብዛት ያላት ሱዳን በዓለም የሰብአዊ ርዳታ ከሚያስፈልጋቸው ተረጅዎች መካከል 10 በመቶውን ትሸፍናለች” ሲል እአአ የአጣዳፊ ርዳታ ፈላጊዎችን የሚከታተለውና መሠረቱን በኒው ዮርክ ያደደረገው ድርጅት እአአ በቀጣዩ 2025 የአጣዳፊ ሁኔታ ክትትል በሚያስፈልጋቸው ቀውሶች ዘገባው አስታውቋል፡፡




የዓለም ነፍስ አድን ኮሚቴ ዘገባ በየዓመቱ ለሰብአዊ ቀውስ ተጋላጭነት ከፍተኛ ሥጋት ያለባቸውን 20 ሀገራት ለይቶ በማጉላት የሚያሳይ ሲሆን ሱዳን ለሁለት ተከታታይ ዓመታት በቀዳሚነት ደረጃ ላይ እንደምትገኝ አመልክቷል፡፡


በሀገሪቱ በጠቅላላው 30.4 ሚሊዮን ሰዎች በሰብአዊ እርዳታ ፈላጊዎች መሆናቸውን የገለጸው ኮሚቴው የተረጅዎችን ቁጥር መመዝገብ ከጀመረ ወዲህ ይህ “ከምንጊዜውም ትልቁ የሰብአዊ ቀውስ” መሆኑን ገልጿል።


ኮሚቴው በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም ወደ 305 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች የሰብአዊ እርዳታ የሚሹ መሆኑን ዘግቧል፡፡ ከእነዚህ 82 ከመቶ የሚሆኑት በኃይል በተያዙት የፍልስጤም ግዛቶች፣ ሚያንማር፣ ሦሪያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ሊባኖስ በመሳሰሉት ክትትል ያስፈልጋቸዋል ተብለው በተመዘገቡ የቀውስ አካባቢዎች እንደሚገኙ ዘገባው አመልክቷል፡፡


የዓለም ነፍስ አድን ኮሚቴ ኃላፊ ዴቪድ ሚሊባንድ ‘ዓለም እሳት ላይ ነች’ ይህ በመቶ ሚሊዮን ለሚቆጠሩ ሰዎች የዕለት ተዕለት እውነታ እንደሆነ ግልጽ ነው።” ብለዋል፡፡


ሚሊባንድ አክለውም &quot;ዓለማችን በሁለት ካምፖች እየተከፈለች ነው፤ ባልተረጋጋ እና ግጭት ባለበት ቦታ በተወለዱት እና በተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ የመኖር እድል ባላቸው መካከል&quot; ማለታቸውን ኤኤፍፒ ጠቅሷል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/sudan-has-become-the-biggest-humanitarian-crisis-ever-recorded-irc/7897430.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/sudan-has-become-the-biggest-humanitarian-crisis-ever-recorded-irc/7897430.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 11 Dec 2024 17:44:47 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><category>የሱዳን ቀውስ </category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/70632e21-ef95-43cb-bc51-fc3de3b99897_cx0_cy4_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በጦርነትና የአየር ንብረት ለውጥ ምክኒያት ረሃብ እየተስፋፍ መኾኑን ተመድ አስታወቀ</title>
            <description>ጦርነትና የአየር ንብረት ለውጥ አኹንም በመላው ዓለም እየተስፋፋ ላለው ረሃብ ምክኒያት መኾናቸውን በተባበሩት መንግሥታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት።


አዲስ አበባ ውስጥ ሲካሄድ ቆይቶ ዛሬ በተጠናቀቀው ዓለምን ከረሃብ  ነጻ የማድረግ ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት፣የድርጅቱ ዋና ሓላፊ ጌራልድ ሙሌር፣  ረሃብ የዓለምን ሕዝብ እየጎዳ ያለው የበለፅጉት ሃገራት ከዓመት ገቢያቸዉ በየዓመቱ ለአዳጊ ሀገራት ሊያደርጉ የሚገባቸዉን ድጋፍ ባለመስጠታቸውና በአዳጊ ሀገራትም የፖለቲካ ውሳኔ  ባለመኖሩ መኾኑን ገልፀዋል። የአፍሪካ ኅብረት በበኩሉ ከአራቱ አንዱ አፍሪቃው ለረሃብ ችግር የተጋለጠ መሆኑን ገልፆ፣ ግጭት አሁንም ለረሃብ መስፋፋት ምክንያት እንደሆነ ተናግሯል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/addis-ababa-world-without-hunger-conference-/7855603.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/addis-ababa-world-without-hunger-conference-/7855603.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 08 Nov 2024 02:02:44 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ገልሞ ዳዊት)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/c0dbb7ed-9860-4c9a-8c54-5d7e88f005f2_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የርዳታ በሮች ለተዘጉበትና ለተራበው የሱዳን ሕዝብ ሾርባ የሚመግቡ የማኅበረሰብ አባላት</title>
            <description>በጦርነት በታመሰችው ሱዳን ኡምዱርማ ውስጥ የሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎች፣ ከግል ለጋሾች ባገኙት ጥቂት ድጋፍ  ሾርባ እየሠሩ የተራቡትን በመመገብ ላይ ናቸው።


ዩናይትድ ስቴትስን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት በቅርቡ ባወጡት መግለጫ፣ “በሱዳን የሚገኙ ሁሉም ተፋላሚ ኃይሎች ለጋሽ ድርጅቶች የርዳታ እህል እዳያስገቡ በተቀነባበረ ሁኔታ ክልከላ ያደረጉ ነው ባሉበት በአኹኑ ሰዓት ከለጋሽ ድርጅቶች ገደብ የሌለው ማለፊያ እንዲሰጡ እየወተወቱ ባለበት በዚህ ወቅት አንዱ የሱዳን ክፍል በከፍተኛ ርሃብ ተጠቅቷል” ሲል የአሜሪካ ድምጽ ዘጋቢ ሄነሪ ዊልከንስ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሯል።


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/sudan-aid-access/7845189.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/sudan-aid-access/7845189.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 30 Oct 2024 22:27:41 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a1dbd048-330a-4d67-a383-1ececea955d2_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በዓለም ዙሪያ ከአንድ ቢሊዮን የሚበልጥ ሕዝብ በከባድ ድሕነት ውስጥ እንደሚኖር ትላንት ሐሙስ የወጣ ሪፖርት አመለከተ</title>
            <description>የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም እና የብሪታኒያው ኦክስፈርድ ዩኒቨርስቲ ያወጡት ሪፖርት ሲሆን ከመካከላቸው ከግማሽ የሚበልጡት ሕጻናት መሆናቸውን አስታውቋል።


አርባ ከመቶ የሚሆኑት የሚኖሩት በጦርነት በሚታመሱ እና በአስተዳደር እና በምጣኔ ሀብት ደካማ በሆኑ ሀገሮች መሆኑን ሪፖርቱ ጠቁሟል።


የመንግሥታቱ ድርጅት ተቋም እና የኦክስፈርድ ዩኒቨርስቲው የድህነት እና የሰብዓዊ ዕድገት መርሐ ግብር ያወጡት የዘንድሮው ሪፖርት በጠቅላላው ስድስት ነጥብ ሦስት ቢሊዮን ሕዝብ የሚኖርባቸው 112 ሀገሮችን መረጃ ያካተተ ነው።


በሪፖርቱ ሰንጠረዥ መሠረት በከፋ ድሕነት ከሚኖሩት 1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ሰዎች ውስጥ ግማሽ ገደማ የሚሆኑት የሚኖሩት በአምስት ሀገሮች እንደሆነ ተጠቁሟል። ህንድ 234 ሚሊዮን፥ ፓኪስታን 93 ሚሊዮን፥ ኢትዮጵያ 86 ሚሊዮን፥ ናይጄሪያ 74 ሚሊዮን እንዲሁም በኮንጎ 66 ሚሊዮን ሰዎች መሆናቸውን ሪፖርቱ አመልክቷል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/more-than-1-billion-people-live-in-poverty-half-are-children-and-many-in-conflict-zonesin-/7827591.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/more-than-1-billion-people-live-in-poverty-half-are-children-and-many-in-conflict-zonesin-/7827591.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 18 Oct 2024 18:18:48 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/223b1ea6-7e94-49f1-b18a-20e9f53b0d6e_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>‘የአየር ንብረት ለውጥ እና የምግብ ዋስትና እጦት በአፍሪካ በፍጥነት እያደገ ለመጣው የሕዝብ ቁጥር ስጋት ጋርጧል’ - ባለሞያዎች</title>
            <description>የአየር ንብረት ለውጥ እና የዓለም ሕዝብ ቁጥር በከፍተኛ ፍጥነት መጨመር የምግብ ዋስትናን አደጋ ላይ ሊጥል የመቻሉ ዕጣ እያነጋገረ ነው። እንደ ባለሞያዎችም እምነት የዓለም ህዝብ ቁጥር ከ10 ቢሊዮን በላይ ሲደርስ የሰብል ምርት በአንጻሩ በ30 በመቶ ሊቀንስ ይችላል።




መሀመድ ዩሱፍ ከናይሮቢ የመንግሥታቱን ድርጅት የዓለም ሕዝብ ቀን አስታኮ ባጠናቀረው ዘገባ እንደጠቆመው፤ ሁኔታው በተለይ በአፍሪካ የሚኖረውን ተጽዕኖ ለመቀነስ፤ በግብርናው ዘርፍ የሚደረግ ለውጥ ብቸኛው አማራጭ ነው።


ለዝርዝሩ አሉላ ከበደ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/food---population/7695908.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/food---population/7695908.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 12 Jul 2024 22:58:33 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a8312c1d-5687-4fdc-86e0-05b48e829000_cx0_cy3_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሱዳን ከ756 ሺሕ በላይ ሕዝብ የከፋ የምግብ እጥረት ሊገጥመው እንደሚችል ተሰግቷል</title>
            <description>በሱዳን የተከሰተው ረሃብ ከቸነፈር ደረጃ ላይ መድረስ ያለመድረሱን ለመወሰን የመንግሥታቱ ድርጅቶች የተለያዩ ተቋማት እና ሌሎች የእርዳታ ድርጅቶች ባቀረቡት የቅድመ ትንበያ ውጤት መሰረት፣ ከ756 ሺሕ ሕዝብ በላይ ለከፋ የምግብ እጥረት ሊጋለጥ  እንደሚችል ተሰግቷል።


የመጀመሪያው የትንበያ አሃዞች፤  እስካለፈው ግንቦት 24, 2016 ዓ.ም ድረስ ባለው ጊዜ በጦርነት በተበታተነችው አገር ውስጥ የታየውን &apos;በፍጥነት እያሽቆለቆለ ያለ ሁኔታ የሚያመላክቱ ናቸው’ ተብሏል።


የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከትላንት በስቲያ ረቡዕ በሰጡት አስተያት፣ በዓለም ግዙፍ የሰብአዊ ቀውስ በተከሰተበት የሱዳን ምስቅልቅል 12 ሚሊዮን ሕዝብ ከቀዬው መፈናቀሉን ተናግረዋል። 


&quot;በአንዳንድ ግዛቶች እጅግ መጠነ ሠፊ የረሃብ አደጋ በተንሰራፋበት ባሁኑ ወቅት ነዋሪዎች አስፈላጊ አገልግሎቶችን እና መድሃኒቶችን የማያገኙ በመሆናቸው ለሕልፈት እየተዳረጉ ነው&quot; ሲሉ አክለዋል።


በተቀናጀ የምግብ ዋስትና የደረጃ ምደባ አሰራር መሰረት በሰኔ እና በመስከረም ወር መሃከል ባለው ጊዜ ውስጥ ቁጥራቸው 756, 000 የሚጠጉ ሰዎች የከፋ ውድመት ሊያስከትል በሚችለው ደረጃ 5 ውስጥ እንደሚገቡ የቅርብ ጊዜያቱ ትንበያዎች ጠቁመዋል።


ይህ በእንዲህ እንዳለ በሱዳኑ ብሔራዊ ጦር እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ መካከል ባለፈው ዓመት የሚያዝያ ወር የተቀሰቀሰው ውጊያ አሁንም ተባብሶ መቀጠሉ ታውቋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/more-than-three-quarters-of-a-million-people-could-face-catastrophic-food-shortages-in-sudan-by-september/7656310.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/more-than-three-quarters-of-a-million-people-could-face-catastrophic-food-shortages-in-sudan-by-september/7656310.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Jun 2024 19:37:02 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-b708-08dc828d989f_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሰሃላ ሰየምት ወረዳ ከረኀብ ጉዳት ጋራ በተያያዘ አንድ ሰው መሞቱ ተገለጸ</title>
            <description>በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን በሰሃላ ሰየምት ወረዳ፣ ባለፈው የመኸር ምርት ዘመን የተከሠተው ድርቅ ባስከተለው ረኀብ ምክንያት የተጎዱ ሰዎች ለኅልፈት መዳረጋቸውን የአካባቢው ባለሥልጣናት አስታውቀዋል፡፡


የሰሀላ ሰየምት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሲሳይ ብሩ ለአሜሪካ ድምፅ ሲናገሩ፣ በወረዳው ያጋጠመውን ድርቅ ተከትሎ አስቸኳይ የምግብ ርዳታ የሚያስፈልጋቸው ከ24ሺሕ በላይ ሰዎች መኖራቸውን ገልጸዋል፤ ባለፈው ሚያዝያ ወር፣ ከረኀብ ጉዳት የተነሣ የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉን፣ ከጤና ተቋማት ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል፡፡


በሰሃላ ሰየምት ወረዳ የቢላዛ ቀበሌ አስተዳዳሪ አቶ ማለደ ብሬ በበኩላቸው፣ በቢላዛ ቀበሌ ብቻ ባለፈው ወር ሁለት ሰዎች ከረኀብ ጉዳት ምክንያት መሞታቸውን ጠቁመዋል፡፡ የርዳታ መቆራረጥ፣ የጸጥታ እና የመንገድ አለመኖር ችግሩን እንዳባባሰውም አስተዳዳሪው አክለዋል፡፡


የአማራ ክልል አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ኮሚሽነር ዲያቆን ተስፋው ባታብል፣ ዛሬ ኀሙስ ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ በነበራቸው ቆይታ፣ ከረኀብ ጋራ በተያያዘ የሰዎች ሕይወት ስለማለፉ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ገልጸው፣ ነገር ግን “አጣራለኹ” ብለዋል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7624509.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7624509.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 23 May 2024 22:37:02 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (አስቴር ምስጋናው)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-8d46-08dc7b5dfcf4_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>&quot;በሱዳን የተደቀነው የረሃብ ቸነፈር አደጋ እየተባባሰ ነው&quot; የዓለም የምግብ ፕሮግራም</title>
            <description>በጦርነት በተጎዱት የሱዳን አካባቢዎች ቁጥሩ ወደ አምስት ሚሊዮን በሚጠጋ ህዝብ ላይ የተደቀነው የረሃብ ቸነፈር አደጋ ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ ነው ሲል የዓለም የምግብ ፕሮግራም አስጠነቀቀ። በዚህ ሳምንት ሱዳንን ጎብኝተው የተመለሱት የዓለም የምግብ ፕሮግራም ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ካርል ስካዉ ትናንት ረቡዕ ባወጡት መግለጫ የረሃቡ ሁኔታ በፍጥነት እያሽቆለቆለ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ የከበደ ቸነፈር አፋፍ ላይ ለሚገኘው ህዝብ የሰብዓዊ ረድዔት ተደራሽነትን እናመቻቻለን ብለው ቃል የገቡት ወገኖች በሙሉ አሁኑኑ በተግባር ሊተረጉሙት  ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡


ዳርፉር እና ኮርዶፋን አካባቢ የክረምቱ ዝናብ ወቅት ገብቶ መንገዶች ከመዘጋጋታቸው በፊት የምግብ አቅርቦት ለማከማቸት ያለው የጥቂት ሳምንታት ጊዜ ብቻ መሆኑን የዓለም የምግብ ፕሮግራም ባለስልጣኑ መግለጫ አስጠንቅቋል፡፡ ገበሬዎችም ዝናቡ ከመጀመሩ አስቀድሞ ደህንነታቸው ተጠብቆ የእርሻ መሬታቸው  ደርሰው መዝራት እንደሚኖርባቸው አክለዋል፡፡


የዓለም የምግብ ፕሮግራም የውጊያው መቀጠል የድንበር ኬላዎች መዘጋት እና ፍተሻን የመሳሰሉ ችግሮች ቢኖሩም በአሁኑ ጊዜ ሁለት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ለሚሆኑ ሱዳናውያን እርዳታ እያቀረበ መሆኑን ገልጿል፡፡


ይህ በእንዲህ እንዳለ በሰሜናዊ ዳርፉር ያለው ሁኔታ ባለፉት ሳምንታት እየተባባሰ መሆኑን ተመድ በማስጠንቀቅ ላይ ነው፡፡ ባለፉት ቀናት  የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ተዋጊዎች  ዋና ከተማዋ ኤል ፋሸር  ወደሚገኙት የሱዳን የጦር ሠራዊት ኃይሎች መገስገስ መጀመራቸውን ዘገባዎች አመልክተው ከተማዋ ያሉት ከ8 መቶ ሺህ በላይ ሲቪሎች አደጋ ላይ እንዳሉ ገልጠዋል፡፡


ባለፈው ሰኞ የተመድ ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዥ ተፋላሚዎቹ ወገኖች በአስቸኳይ ውጊያውን አቁመው የተኩስ አቁም ድርድሩን እንዲቀጥሉ ጥሪ አሰምተዋል፡፡


ዳርፉር ውስጥ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ያልተያዘች ከተማ ኤልፋሸር ብቻ ነች፡፡ ኤል ፋሸር ላይ የለየለት ውጊያ ከተቀሰቀሰ  እአአ በ2000 ዓም ዳርፉር ውስጥ የአረብ ጃንጃዊድ ታጣቂዎች  በዛግዋ፡ ማሳሊት ፡ ፉር እና ሌሎችም አረብ ያልሆኑ ጎሣዎች ላይ  የፈጸሙትን የዘር ማጥፋት የመሰለ ጭካኔ የተመላበት ጥቃት ሊደርስ እንደሚችል ተመልክቷል፡፡


ኤል ፋሸር ውስጥ በምግብ ዕጥረት እና በዋጋው ማሻቀብ የተነሳ 330 ሺህ ህዝብ ለከባድ የረሐብ ቀውስ መጋለጡን ተ መ ድ አስታውቋል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un-sudan-famine/7614823.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un-sudan-famine/7614823.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 16 May 2024 18:41:42 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/37b7822f-1cab-436f-b95d-f2777e8e4dac_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተመድ ለኢትዮጵያ ሰብአዊ ርዳታ የሚውል 1 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ አቅዷል</title>
            <description>የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በግጭት ለምትታመሰው፣ በጎርፍ እና ድርቅ ለተጠቃችው ኢትዮጵያ የሚያስፈልገውን የሰብአዊ ርዳታ አቅርቦት ከፍ ለማድረግ 1 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ማቀዱን ዛሬ ማክሰኞ አስታወቀ።


ከኢትዮጵያ እና ከእንግሊዝ መንግሥታት ጋራ በመተባበር የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጄኔቫ ላይ ያካሄደው የገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻ ለ15.5 ሚሊዮን ሰዎች የሚሆን የነብስ አድን ርዳታ እና ለተጨማሪ 10 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሰዎች የሚሰጠውን የምግብ ዕርዳታ መጠን ለማሳደግ የታለመ መሆኑ ተመልክቷል።


“የአስቸኳይ ርዳታ የሚጠይቁት ሁኔታዎች በድርቅ እና በጎርፍ እንዲሁም በግጭት እየተባባሱ የመጡ ናቸው” ሲል ተመድ አስታውቋል።


&quot;ኤልኒኞ በሰሜናዊ የሃገሪቱ ክፍል በሚገኙ ደጋማ አካባቢዎች ያለውን ድርቅ በማባባሱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የውሃ አቅርቦት ዕጥረት፤ የግጦሽ ሳር እጦት እና የምርት መጠን ማሽቆልቆል ያስከተሏቸውን ፈተናዎች ለመቋቋም እየተጣጣሩ ነው&quot; ብሏል።


በዚህ ዓመት በግጭቶች እና የአየር ንብረት ለውጥ ባስከተሏቸው ችግሮች የተነሳ ቁጥራቸው ከ21 ሚሊየን በላይ የሚደርሱ ሰዎች በኢትዮጵያ ሰብአዊ ርዳታ እንደሚፈልጉ የገለጸው ኦቻ፣ ከሐምሌ እስከ መስከረም ባሉት ወራት ቁጥራቸው 10 ነጥብ 8 ሚሊዮን የሚደርስ ሰዎች ለከፋ የምግብ ዋስትና ዕጥረት መጋለጣቸውንም ገልጿል።


በተያያዘ እንግሊዝ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን ርዳታ መጠን ለማሳደግ ተጨማሪ 100 ሚሊዮን ፓውንድ (124 ነጥብ 58 ሚሊዮን ዶላር) እንደምትሰጥ አስታውቃለች።


በብሪታኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር  የልማት እና የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ሚኒስትር አንድሪው ሚሸል ሲናገሩ ለኢትዮጵያ ተጨማሪ ርዳታ ለመስጠት የተገባው ቃል የባህረ ሰላጤውን አገሮች ጨምሮ “ሌሎች ሃገራት እንዲሳተፉ ያበረታታል” የሚል እምነት እንዳደረባቸው ተናግረዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un-seeks-to-raise-1-billion-to-boost-aid-to-ethiopia-/7572451.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un-seeks-to-raise-1-billion-to-boost-aid-to-ethiopia-/7572451.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 16 Apr 2024 21:10:14 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/c36c0000-0aff-0242-f00f-08d9efda1365_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ድርቅ የብሄራዊ አደጋ ሥጋት የደቀነባት ማላዊ የርዳታ ጥሪ አሰማች</title>
            <description>በተፈጥሮ የሚከሰተው ኤልኒኞ፣ በፓስፊክ ምሥራቃዊ ውቅያኖስ አካባቢ ከሚታየው ያልተለመደ የውሃ ግለት የሚነሳው ሙቅ አየር በዓለም ዙሪያ የአማካይ ሙቀት መጠን እንዲጨምር በማድረጉ እና እንዲሁም ወደ ከባቢ ዓየር የሚለቀቀው በካይ የካርቦን መጠን የከሰቷቸው ሁኔታዎች ተደራርበው ድፍን ደቡባዊ አፍሪቃ ባለፉት ዓመታት አጋጥሞት በማያውቅ አስከፊ ድርቅ እየተናጠ ይገኛል። ይህንንም ተከትሎ ማላዊ፣ ዝምባብዌ እና ዛምቢያ ባለፈው ወር አከባቢውን በመታው ድርቅ ሳቢያ የአስቸኳይ ጊዜ አውጀዋል።


የምግብ አቅርቦት ምንጮች እየነጠፉ ባሉባት ማላዊ፡ የማሳ ሰብል ስርቆት ብርቱ ችግር እየሆነ ነው። የበቆሎ አምራች የነበሩ ኡላሊያ ላፑሶኒ የተባሉ አንዲት ገበሬ ሲናገሩ፡ በድርቁ ሳቢያ የዘሩት በቆሎ ባለማፍራቱ በአሁኑ ወቅት የረሃብ አደጋ ተጋርጦባቸዋል።


&quot;እስኪ አስቡት ለዚህ ወር የሚሆን ምግብ የለንም፤ እንዴ አድርገን ተርፈን እስከሚቀጥለው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ መድረስ እንችላለን? ከባድ ነው የሚሆነው” ብለዋል የደረቀ ማሳቸውን እያሳዩ።


ከዚሁ በተያያዘም፡ የማላዊው ፕሬዝዳንት ላዛረስ ቻክዌራ ሃገራቸውን ከረሃብ አደጋ ለመታደግ አለም አቀፍ ለጋሾች እጃቸውን እንዲዘረጉ ጠይቀዋል። በዓለም ዙሪያ በ2023 አዲስ ሪከርድ ያስመዘገበው የአየር ንብረት ለውጥ ኤልኒኞ የሚያሳድረውን ተፅእኖ ማባባሱም ተዘግቧል።


ዓለም አቀፉ የረድኤት ድርጅት ኦክስፋም ባለፈው ሳምንት እንዳስጠነቀቀው፡ በደቡባዊ አፍሪቃ ከ24 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በድርቅ ሳቢያ ለረሃብ፣ የተመጣጠነ ምግብ እና የውሃ እጥረ ተጋልጠዋል።


በማላዊ በተከሰተው ድርቅ ሳቢያም ‘ዘጠኝ ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ተጎድተዋል’ ሲል ዩኒሴፍ አስታውቋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/malawi-appeals-for-aid-as-drought-sparks-national-disaster-/7563101.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/malawi-appeals-for-aid-as-drought-sparks-national-disaster-/7563101.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 09 Apr 2024 21:00:01 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ክምችት </category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-028b-08dc58be85db_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተመድ በኢትዮጵያ ለተረጂዎች ርዳታ ለማቅረብ የ998 ሚሊየን በጀት ክፍተት እንዳለበት አስታወቀ</title>
            <description>የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ) ትላንት ባወጣው መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ እስከ መስከረም ወር ባለው ጊዜ አስቸኳይ ርዳታ ያስፈልጋቸዋል ተብለው ከሚገመቱ ዘጠኝ ሚሊየን ተረጂዎች ውስጥ አምስት ሚሊየን ለሚሆኑት ብቻ የገንዘብ ድጋፍ ማግኘቱን እና ለቀሪዎቹ አራት ሚሊየን ተረጂዎች ተጨማሪ 998 ሚሊየን ዶላር እንደሚያስፈልገው አስታውቋል።


ኢትዮጵያ ውስጥ በቀጠሉ ግጭቶች እና ድርቅን እና ጎርፍን ጨምሮ የአየር ንብረት አደጋዎች አሉታዊ ተፅእኖ ምክንያት ኢትዮጵያ ውስጥ የምግብ ዋስትና እጦት እንዲባባስ በማድረጋቸው፣ እ.አ.አ በ2024 ከመጋቢት እስከ መስከረም ባለው ወር 9 ሚሊየን ሰዎች አስቸኳይ ርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ) በትላንቱ መግለጫው አስታውቋል።


ከነዚህ ውስጥ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በወር አምስት ሚሊየን ለሚሆኑ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና የምግብ ዋስትና የሌላቸው ሰዎች አስቸኳይ የምግብ ርዳታ ማድረግ የሚያስችል ድጋፍ ማግኘት ቢቻልም፣ በወር 4 ሚሊየን ለሚሆኑ ሰዎች የሚያስፈልገውን ወደ 468 ሺህ ሜትሪክ ቶን የሚጠጋ ምግብ ለማከፋፈል፣ የሰብል ምርትን ለመደገፍ፣ የውሃ አቅርቦት ለማሻሻል፣ ለጤና፣ ለትምህርት እና ለመሳሰሉት የበጀት እጥረት እንደገጠመው አመልክቷል።




ድርጅቱ ለተረጂዎቹ የሚፈለገውን ወደ 414 ሺህ የሚጠጋ እህል፣ ከ42 ሺህ በላይ ጥራጥሬ እና ከ12 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ የአትክልት ዘይት ለማከፋፈል ወደ 475 ሚሊየን ዶላር የሚጠጋ ተጨማሪ በጀት ጠይቋል።


ከሚያስፈልገው ርዳታ ውስጥ የተገኘው ግማሽ ለሆኑት ብቻ መሆኑ አሳሳቢ ክፍተት መፍጠሩን የጠቀሰው መግለጫው፣ &quot;ድጋፉ ካልተገኘ ተጋላጭ የሆኑት የኅብረተሰብ ክፍሎች እና የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች አደገኛ ወደሆነ የምግብ እጦት እንደሚገቡ&quot; አመልክቷል።


በከፍተኛ የሰብአዊ ቀውስ ነች ለተባለችው ኢትዮጵያ እኤአ በ2024 በመንግሥቱና አጋሮቹ የታለመው ጠቅላላው የሰብአዊ ምላሽ እቅድ 3.237 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ ሲሆን፣ ይህ 15 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን ለመደገፍ ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡


ድጋፉ የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመከላከል፣ ንፁህ ውሃና የንፅህና አቅርቦትን ለማረጋገጥ፣ የጤና አገልግሎት ለመስጠት፣ ትምህርትን ለመደገፍ እና የእንስሳት እርባታና የሰብል ምርት ድጋፎችን ለማሟላት የሚደረገውን ጥረት እንደሚያጠናክር በመግለጫው ተብራርቷል፡፡


ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/government-un-joint-statement/7524600.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/government-un-joint-statement/7524600.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 12 Mar 2024 21:14:20 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ክምችት </category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-804c-08dc42bfb3be_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የመንግስታቱ ድርጅት ለኢትዮጵያ የ17 ሚሊዮን ዶላር የአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ መደበ</title>
            <description>በኢትዮጵያ እየተባባሰ ለመጣው የምግብ ዋስትና እጦት የ17 ሚሊዮን ዶላር መመደቡን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ አስተባባሪ ማርቲን ግሪፊዝስ አስታወቁ። አዲስ የተመደበው ይህ የገንዘብ ድጋፍ ኢትዮጵያን ለተጨማሪ አደጋ ያጋለጠው ‘ኤልኒኞ’ የአየር መዛባት ያስከተለው ድርቅ በአፋር፣ በአማራ እና በትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች የከፋ ጉዳት ሊያስከትል መቻሉ ያሳደረውን ብርቱ ስጋት የሚያንጸባርቅ ነው ተብሏል።




ኢትዮጵያን የገጠመው የምግብ ዋስትና እጦት በመጭው ወራትም እየበረታ ሊሄድ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል። ከሐምሌ እስከ መስከረም ባሉት የክረምት ወራት ውስጥ በመላው ኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ተጨማሪ ሰዎች የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከዚህ ቀደም የተከሰተው ድርቅ እና በሃገሪቱ ያሉት ግጭቶች አሁንም ተጽዕኖ ማሳደራቸውን ቀጥለዋል። በሌላ በኩል የጎርፍ መጥለቅለቅ ተጨማሪ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል ተጠቁሟል።




ከ2013 እስከ 2015 ባለው ጊዜ በሰሜን ኢትዮጵያ የተካሄደውን ጦርነት ጨምሮ በሃገሪቱ በተከታታይ ለደረሱ ምስቅልቅል ሁኔታዎች የተጋለጡ ማሕበረሰቦችን ከገጠማቸው የከፋ ጉዳት ለመታደግ ያለው ዕድል አጭር ዕድሜ ዘላቂ መሆኑን የመንግስታቱ ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት አመልክቷል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un-allocates-17m-in-emergency-funds-for-ethiopia-food-insecurity-02-27-24/7504955.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un-allocates-17m-in-emergency-funds-for-ethiopia-food-insecurity-02-27-24/7504955.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 27 Feb 2024 23:25:53 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ክምችት </category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a0910f5b-142a-49fe-899b-77d0faec8b78_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኢትዮጵያ እያሻቀበ ላለው የተረጂዎች ቁጥር ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ያስፈልጋል ተባለ</title>
            <description>በኢትዮጵያ ለተረጂዎች የምግብ ርዳታ ለማቅረብ 3ነጥብ4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቁ። የተረጅዎች ብዛት በተያዘው ዓመት 10ነጥብ4 ይደርሳል ተብሏል።


የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ከፍተኛ የሕዝብ ግንኙነት ባለሞያ አቶ አታለለ አቡሃይ፣ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ያለው የተረጅዎች ብዛት 6ነጥብ6 ሚሊዮን መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በጎርፍ እና በሌሎችም ምክንያቶች ይኸው አኀዝ እንደሚጨምር ባለሞያው አመልክተዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-un-joint-humanitarian-appeal/7504767.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-un-joint-humanitarian-appeal/7504767.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 27 Feb 2024 21:34:27 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ክምችት </category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ገብረሚካኤል ገብረመድህን)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-d310-08dc37c0f943_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኢትዮጵያዉያንን እየፈተነ ያለው የኑሮ ውድነት</title>
            <description>በምግብ ፍጆታዎች ላይ ቀን በቀን በሚደረጉ የዋጋ ጭማሬዎች ምክንያት መማረራቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። የዋጋ ንረቱ እየጨነረ በሚሄድበት ጊዜ የነዋሪዎች ገቢ አለመጨመሩ ችግሩን የበለጠ እንዳወሳሰበው የተናገሩት ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት ረዳት ፕሮፌሰር ዶክተር ሰውአለ አባተ ናቸው። መፍተሄ የሚያመጡ ኢኮኖሚያዊ ፖሊሲዎችን ለመተግበርም በመጀመርያ ሰላም እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።




በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት ማብራርያ የሰጡት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ በሃገሪቱ አለ ያሉትን “የማክሮ ኢኮኖሚ ስብራት” ለመጠገን መንግሥታቸው የነደፈው የሪፎርም ፖሊሲ በኮቪድ 19፣ አለማቀፋዊ ጫናዎችና ውስጣዊ ጦርነቶች ምክንያት እንደታሰበው እንዳልሄደ ተናግረዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-inflation/7495342.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-inflation/7495342.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 20 Feb 2024 23:21:28 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (አስማማው አየነው)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-9528-08dc324e754b_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሱዳን በሚሊዮኖች የተቆጠሩ ዜጎች ለረሃብ መጋለጣቸውን ምግብ ፕሮግራም አስታወቀ</title>
            <description>በሱዳን በቀጠለው ቀውስ የተነሳ ቢያንስ በ25 ሚሊዮን ህዝብ ላይ ከባድ ረሐብ እና የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ስጋት መደቀኑን የዓለም የምግብ ፕሮግራም ገለፀ። ቀውሱ በቀጣናው በመዛመቱም በየሳምንቱ ብዙ ሺህ ሱዳናዊያን ድንበር አቋርጠው ወደቻድ እና ወደደቡብ ሱዳን እየተሰደዱ መሆኑን አመልክቷል።


በአሶሽየትድ ፕሬስ የተጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/wfp-sudan-displaced/7495331.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/wfp-sudan-displaced/7495331.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 20 Feb 2024 23:06:46 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-e49d-08dc324ea7b7_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በትግራይ “ከባድ ረኀብ አንዣቧል” ያሉት ጌታቸው ረዳ የዳያስፖራውን ድጋፍ ተማፀኑ</title>
            <description>የትግራይ ክልልን የሰላም ግንባታ እና መልሶ ማቋቋም አዳጋች የሚያደርግ፣ ከባድ የረኀብ አደጋ እያንዣበበ እንደሆነ ያመለከቱት የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ፣ ለትግራይ ዳያስፖራ ማኅበረሰብ የድጋፍ ጥሪ አቅርበዋል።


“የሰላም ግንባታ እና ፍትሕ በድኅረ ጦርነት ትግራይ” በሚል ርእስ፣ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ፣ በድረ ገጽ በተካሔደው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ አቶ ጌታቸው ሲናገሩ፣ ሕዝቡን ከረኀብ አደጋ ለመታደግና በጦርነቱ የወደመውን መንግሥታዊ መዋቅር ወደነበረበት ለመመለስ የዳያስፖራ ማኅበረሰቡ ሚና አስፈላጊ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡




ሌላው የኮንፈረንሱ ተናጋሪ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር፣ ከባድ የረኀብ አደጋ እንደሚኖር በአቶ ጌታቸው የተገለጸውን ከፍተኛ ስጋት እንደሚጋሩ ጠቅሰው፣ ከብዙ አጋሮቻችንና ለጋሾች ጋራ በትብብር መሥራታችን እንቀጥላለን፤ ብለዋል። በስርቆት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የምግብ ርዳታ ማከፋፈል፣ አሁን በአጥጋቢ ሁኔታ መግባባት ስለተደረሰበት ምግብ ማከፋፈሉ ተጀምሯል፤ ሲሉም አክለዋል፡፡




“ለሰላም፣ ፍትሕ እና ተጠያቂነት አስፈላጊ ሐሳቦችን ለማሰባሰብ” ታልሞ እንደተዘጋጀ በተገለጸው በዚኹ ዓለም አቀፍ የድረ ገጽ ኮንፈረንስ፣ በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም እስከ አሁን የታየው ፍጥነት “አላረካንም” ሲሉ መጓተቱን ማይክ ሐመር አመልክተዋል፡፡ “የኤርትራ ኀይሎች ሙሉ በሙሉ ከትግራይ


ክልል የሚወጡበትን ቀን እየጠበቅን ነው፤” ያሉት ልዩ መልዕክተኛው፣ ለተጠያቂነት መረጋገጥም “ቁርጠኞች ነን” ብለዋል፡፡


በኦሮሚያ ክልል ያለውን ግጭት ለመፍታት ጥረታቸውን እንደሚቀጥሉ ገልጸው፣ በአማራ ክልልም በፌደራል መንግሥቱ እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ድርድር እንዲካሔድ ለመገፋፋት “ፍላጎታችን ነው፤” ብለዋል። ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ ከተፈራረሙት የመግባቢያ ሰነድ ጋራ በተያያዘ፣ ከሶማሊያ ጋራ የተፈጠረውን መካረር ያነሡት ሐመር፣ ሁሉም የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ቀጣናው ሊሸከመው የማይችለውን ሌላ ግጭት እንዲያስወግዱ ጥሪ አቅርበዋል።


የሰላም ስምምነቱ ከተፈረመ 14 ወራት እንደተቆጠሩ ያወሱት ጌታቸው ረዳ ደግሞ፣ የተፈናቀለው ሕዝብ ወደ ቀዬው ሳይመለስና ሕገ መንግሥታዊ የትግራይ ክልል ግዛታዊ አንድነት ሳይረጋገጥ፣ ሰላሙ መሠረት ሊኖረው እንደማይችል አሳስበዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ አያይዘው እንዳመለከቱት፣ ሰላሙ የተሟላ ሊሆን የሚችለው ደግሞ፣ በፌደራል መንግሥቱ በተገለጸው የሽግግር ፍትሕ ሒደት፣ ዓለም አቀፍ የፍትሕ አካላት የተካተቱበትና የትግራይ ክልል የተሳተፈበት ተጠያቂነት ሲረጋገጥ ነው፡፡


ዘገባውን ያጠናቀረው የትግርኛ ክፍል ባልደረባ ገብረ ገብረ መድኅን ነው፤ ሀብታሙ ሥዩም በድምጽ አቅርቦታል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7465281.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7465281.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 31 Jan 2024 22:07:18 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ክምችት </category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-8795-08dc228f7644_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>“የሰሜን ጎንደር ነዋሪዎች በድርቁ ምክንያት ወደ ከተሞች እየተሰደዱ ነው”- ዩኤንኦቻ</title>
            <description>

በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን፣ ጃናሞራና ጠለምት ወረዳዎች በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ከአራት ሺ በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ከቀያቸውን ለቀው ወደ ከተሞች መሰደዳቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (UN-OCHA) ትናንት ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።


በሁለቱ ወረዳዎች በተከሰተው ድርቅ ከ86 ሺ በላይ የቤት እንስሳት መሞታቸውን እና ከ173 ሺህ በላይ መሰደዳቸውን ሪፖርቱ አመልክቷል።


የጃን አሞራ ወረዳ ግብርና ፅ/ ቤት በበኩሉ፣ በሶስት ወራት ውስጥ ብቻ 1ሺ 4 መቶ ሰዎች ቤታቸውን ለቀው ወደ ከተሞች መሰደዳቸውን ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ አረጋግጠዋል።




ድርቁ ባስከተለው ረኀብ ምክንያት ጠለምት ወረዳን ለቀው አራት ቀን በእግር  ተጉዘው በአጎራባቹ አድርቃይ ከተማ እንደሚገኙ የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል።


የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበርያ ቢሮ(UN-OCHA)፣ ከአንድ ወር  በፊት ባወጣው ሪፖርቱ፣ በአማራ ክልል፣ 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሕዝብ የምግብ ዋስትና ችግር እንዳለበት ጠቅሶ፣ የመንግሥት ምላሽ ያገኙት 25 በመቶ ያህሉ ብቻ እንደሆኑና በስምንት ዞኖች ውስጥ የሚገኙ 713 ሺህ ሰዎች ለአደጋ እንደተጋለጡ ማመልከቱ የሚታወስ ነው፡፡


በዐማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን፣ ሦስት ወረዳዎች፣ ማለትም በጃን አሞራ፣ በየዳ እና ጠለምት ወረዳዎች፣ በ2015/16 መኸር ምርት የተከሠተው ድርቅ ባስከተለው ረኀብ፣ 36 ሰዎች መሞታቸውን እና ከ72 ሺ በላይ እንስሳትም መሞታቸውን በአካባቢው የሚገኘው የደባርቅ ዩኒቨርስቲ “ከአንድ ወር በፊት አደረግኩት” ባለው ጥናት ይፋ አድርጎ ነበር።


የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (UN-OCHA) ትናንት ባወጣው ሪፖርቱ ከድርቁ ጋር በተያያዘ በአማራ ክልል፣ ጠለምትና ጃን አሞራን ጨምሮ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ህፃናት ትምህርት ማቋረጣቸውንም ገልፆል።




የፌደራል አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ እርዳታ አስተባባሪ በሀገሪቱ ያለውን ወቅታዊ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት  በተመለከተ በጋራ ባወጡት  መግለጫ በኢትዮጵያ በአምስት ክልሎች 4 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/amhara-migration-/7436341.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/amhara-migration-/7436341.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 12 Jan 2024 00:30:35 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (አስቴር ምስጋናው)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a0b34eb6-fdeb-47c1-a3ef-9bec2160f931_cx0_cy8_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሱዳን የሚካሄደው ጦርነት የረሃብ አደጋን ደቅኗል </title>
            <description>በሱዳን በመካሄድ ላይ ያለው የሁለት ጀኔራሎች ጦርነት ከካርቱም በስተ ደቡብ ወደምትገኘውና አል-ጃዚራ ወደተሰኘችው ለም አካባቢ ከተዛመተ ወዲህ፣ በአንድ ወቅት ትርፍ ያመርቱ የነበሩ ገበሬዎች ምጽዋት ጠባቂ ሆነዋል።


ገበሬዎቹ ወደ ማሳቸው መሄድ እንዳልቻሉ እና የዘሩትን መንከባከብም ሆነ መሰብሰብ እንዳልቻሉ ለኤ.ኤፍ.ፒ ዜና ወኪል ተናግረዋል።


በሱዳን መደበኛ ሰራዊት እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ መካከል ባለፈው ሚያዚያ ጦርነቱ ከጀመረ ወዲህ፣ አል-ጃዚራ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ሰዎች መጠለያ እንደሆነበረች የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታውቋል።


ጦርነቱ ወደ ደቡብ አቅጣጫ እየተስፋፋ በመምጣቱ ግን፣ ባሳለፍነው ታህሳስ ወር በአል-ጃዚራ የነበረው ሰላም ደፍርሷል። ዋድ ማዳኒ የተሰኘችውን ከተማ ለመቆጣጠር ውጊያው በመፋፋሙ፣ በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎች ለመሸሽ ተገደዋል።




የሱዳን ሠራዊት ዋድ ማዳኒን ጥሎ ሲወጣ፣ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ሰፊ የእርሻ መሬቶችን በመቆጣጠሩ፣ ሰዎች መንደራቸውን ለቆ ለመውጣትም ሆነ በመስኖ እና ማዳበሪያ የሚለሙ ሰፋፊ እርሻዎቻቸውን ለመንከባከብ እንዳይቹሉ አድርጓል።


የተመድ የዓለም የምግብ ፕሮግራም እንደሚለው፣ በአሁኑ ወቅት 18 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች ከረሃብ ጋር ተፋጠዋል። አምስት ሚሊዮን የሚሆኑቱ ደግሞ አስቸኳይ መልስ የሚያሻው ሁኔታ ውስጥ ናቸው።


ረሃብ በይፋ ባይታወጅም፣ መከሰቱ አይቀሬ መሆኑን ‘የኖርዌ ፍልሰተኞች ም/ቤት’ የተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲያስታውቅ፣ የአሜሪካው ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዩኤስኤይድ) በበኩሉ፣ ጦርነቱ ሰብል አምራች በሆኑ አካባቢዎች መስፋፋቱ፣ የአገሪቱን የምግብ ዋስትና አደጋ ላይ እንደጣለ አመልክቷል።


በሱዳን ዘጠኝ ወራት ያስቆጠርውን ጦርነት ለማስቆም እና የሰብዓዊ ሥራ ለማከናወን እንዲቻል፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ “አስቸኳይ እና ወሳኝ” እርምጃ መውሰድ እንዳለበት የተመድ የአስቸኳይ ግዜ አስተባባሪ ማርቲን ግሪፊትስ ባለፈው ሐሙስ አሳስበዋል። 




በዚህ ዓመት ሃያ አምስት ሚሊዮን የሚሆኑ ሱዳናውያን ርዳታ እንደሚያሻቸው የጠቀሱት ኃላፊው፣ ውጊያው የሚቀጥል ከሆነ ግን ርዳታ የማድረስ ሥራው እንደሚስተጓጎል ሥጋታቸውን ገልጸዋል። 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/sudan-famine/7432497.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/sudan-famine/7432497.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 09 Jan 2024 17:47:44 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/11e21467-897f-43e1-a1a2-00b39e592cb2_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በረሃብ “138 ሰው ሞቷል” - አፅቢ ወረዳ</title>
            <description>“በረሃብ ምክንያት የሚሞተው ሰው ቁጥር እየጨመረ ነው” ሲል በትግራይ ክልል የአፅቢ ወረዳ አስተዳደር አስታውቋል።


&quot;አስቸኳይ ምላሽ ለትግራይ&quot; በሚል የተቋቋመው ኮሚቴ 282 ሚልዮን ብር አሰባስቦ 64 ሺሕ ኵንታል እህል በድርቅ ወደ ተጎዱ አካባቢዎች ማድረስ መጀመሩን ገልጿል።


የአፅቢ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ መዝገበ ግርማይ በወረዳው በረሃብ ምክንያት 138 ሰው መሞቱን ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ማብራሪያ ተናግረዋል።


በወረዳው ደራ የሚባል ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አቶ ብርሃን ክፍለ የዘንድሮን የመሰለ ድርቅ አይተው እንደማያውቁ ጠቁመው አምስት ልጆች ይዘው ለረኃብ መጋለጣቸውን ገልፀዋል።


“ብዙ አረጋዊያን እናቶች ቤታቸውን ዘግተው ተኝተዋል። ከባድ ረሃብ ስላለ ወጣቱም አካባቢውን ጥሎ እየተሰደደ ነው። ወላጆቻችን፣ እህት ወንድሞቻችን እያየን ከሚሞቱብን በማለት ወደ አረብ አገሮች እየተሰደዱ ነው። ለመኖ የሚሆን ነገርም ባለመኖሩ እንስሣት እየሞቱ ነው&quot; ብለው ሦስት ልጆቻቸው በረሃቡ ምክንያት ትምህርት እንዳቋረጡም አቶ ብርሃን ገልፀዋል።


ከወረዳው 33 ትምህርት ቤቶች ስምንቱ በረሃቡ ምክንያት ትምህርት ለማቆም መቃረባቸውን አስተዳደሪው አቶ መዝገበ ግርማይ አመልክተዋል።


“ጠፍተው ነበር” ያሏቸው እንደ ጆሮ ደግፍ፣ እከክ፣ የዐይን መታወክ፣ ተቅማጥ ያሉ የጤና ችግሮች በስፋት እየታዩ መሆናቸውንም አስተዳዳሪው ገልፀዋል። ከ5070 እናቶች 4078 በምግብ እጥረት የተጎዱ መሆኑን በጤና ባለሞያዎች ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።


የፌደራሉ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር ዶ/ር ሺፈራው ተክለማርያም በአሁኑ ጊዜ በረሃብ ምክንያት ህይወት ማለፉን አላረጋገጥንም ብለው ነበር።


በትግራይ ክልል &quot;አስቸኳይ ምላሽ ለትግራይ&quot; በሚል የተቋቋመው ኮሚቴ በበኩሉ በዚህ ዓመት በክልሉ ለተፈጠረው ድርቅ እና ረሃብ 10 ሚልዮን ኩንታል ምግብ እንደሚያስፈል አስታውቋል።


የኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋይ ገብረእግዚአብሔር እህል በድርቅ ወደ ተጎዱ ወረዳዎች ከከትናንት በስተያ ቅዳሜ፣ ታህሳስ 27 / 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ማድረስ መጀመሩን ተናግረዋል።


“በዚህ ድርቅ ምክንያት በሰላሣ ስድስት ወረዳዎች 215 ቀበሌዎች ውስጥ 4 ሚልዮን ተኩል ሰው አስቸኳይ እርዳታ ይጠብቃል። ይህ መንግሥትና ለጋሾች ያካሄዱት ጥናት ነው። እነዚህን ምግብ በአስቸኳይ የሚያስፈልጋቸውን ለማገዝም በዚህ አንድ ዓመት አሥር ሚልዮን ኵንታል ወይም 40 ቢልዮን ብር ያስፈልጋል። አሁን በአንደኛው ዙር 32 ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ 425 ሺሕ ተጠቃሚዎች የሚታደል 64 ሺሕ ኩንታል እህል መላክ ጀምረናል” ብለዋል።


ይህ ከግለሰቦችና ከተቋማት በማሰባሰብ በቆሎ በመግዛት ወደ ተጎዱ አካባቢዎች መላክ የተጀመረው እህል ወደ ህዝቡ በቀጥታ እንዲደርስም ክትትል ይደረጋል ተብሏል።


በትግራይ ክልል የተከሰተው ድርቅ “ለፖለቲካ ዓላማ እየዋለ ነው” ሲሉ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሠ ቱሉ ወቅሰው ድርቁ “የ77ቱን ዓይነት አደጋ ደቅኗል መባሉ ፍፁም የተሳሳተ ነው” ብለው ነበር።


የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ በሰጡት ምላሽ “ለረኃብ የተጋለጡ ሚልዮኖችን ለመታደግ የቀረበው ጥሪ ፖለቲካዊ መባል የለበትም ማለታቸው” አይዘነጋም።


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/tigray-atsbi-hunger/7431178.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/tigray-atsbi-hunger/7431178.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 08 Jan 2024 22:30:13 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-c0a8-0242-1ae7-08dc107fe964_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>