<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/6287</link>
        <description>Ethiopian Refugee Crisis</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/6287</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Wed, 08 Apr 2026 19:02:50 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/ztotqml-vomx-tpekkkqm" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>የእህል ርዳታ ወደ ቡግና ወረዳ መጓጓዝ መጀመሩን ባለሥልጣናት አስታወቁ</title>
            <description>በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ የሀገር ሽማግሌዎችና የኃይማኖት አባቶች በረኅብ ለተጎዱ ሰዎች የርዳታ እህል ወደ ወረዳው እንዲገባ ከመንግሥትና ከፋኖ ታጣቂዎች ጋራ ስምምነት ማድረጋቸውን አስታወቁ።


በስምምነቱ መሰረትም የርዳታ እህሉ እየገባ መኾኑን አንድ የኃይማኖት አባት ተናግረዋል። የሰሜን ወሎ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ይመር ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃል፣ አካባቢው በፋኖ ታጣቂዎች ስር በመኾኑ ለተከሰተው የምግብ እጥረት መንግሥት በቶሎ ምላሽ መስጠት አልቻለም ብለዋል።


የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎችና የኃይማኖት አባቶች በአደረጉት ጥረትም ከ110 ሺሕ በላይ ለሆኑ ሰዎች ከ16 ሺሕ ኩንታል በላይ የርዳታ እህል ወደ ስፍራው እየተጓጓዘ መኾኑን አስታውቀዋል።


የወረዳው ነዋሪ ያለበትን የምግብና የጤና ችግር...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/food-aid-is-being-transported-to-people/7908905.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/food-aid-is-being-transported-to-people/7908905.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 20 Dec 2024 22:50:35 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ረሃብ በአፍሪካ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (አስቴር ምስጋናው)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/BF762538-4979-41D0-95A7-E875E7FFE725_cx0_cy8_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱ የትግራይ ተወላጆች ርዳታ እንዳላገኙ ተናገሩ</title>
            <description>

በትግራይ ክልል በተጀመረውና ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ በተሰፋፋው ጦርነት ምክኒያት ወደ ሱዳን ተሰደው የነበሩ የትግራይ ተወላጆች፣ በሱዳን ጦርነት ምክኒያት ወደ አገራቸው ቢመለሱም ርዳታ ማግኘት እንዳልቻሉ ገለጹ።


የክልሉ ማኅበራዊ ጉዳይና መልሶ ማቋቋም ቢሮ በበኩሉ፣ በአቅም እጥረት ምክንያት ተመላሾቹ ርዳታ እያገኙ እንዳልሆኑ ገልጾ፣ “ጉዳዩን ለፌደራሉ መንግሥት አሳውቀናል፣ ከሚመለከታቸው ዓለምአቀፍ ተቋማት ጋራም ተነጋግረንበታል” ብሏል። ከኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/tigray-returnees/7843577.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/tigray-returnees/7843577.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 29 Oct 2024 21:23:17 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ገ/ሚካኤል ገ/መድህን)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-6835-08dca05af836_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኢትዮጵያ የርዳታ እህል ምዝበራ እስከ አሁን ባሉ መረጃዎች የሚታወቀው</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት(USAID) በዓለም የምግብ ፕሮግራም(WFP) አማካይነት በኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ ክልል የሚያሰራጨው የርዳታ እህል፣ በተገቢው መንገድ “ለተረጂው ባለመድረሱ”፣ የርዳታ ዕደላው እንዲቋረጥ ማድረጉን፣ በግንቦት ወር 2015 ዓ.ም. አስታውቆ ነበር። 


ይኸው የርዳታ እህል ምዝበራ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ &quot;ግዙፉ&quot; እንደኾነ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅቱ አመልክቷል።


ምንም እንኳን፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቱ፣ በኢትዮጵያ ያቋረጠው የምግብ ርዳታ በድጋሚ እንዲሰጥ ቢፈቅድም፤ በአገሪቱ የርዳታ እህል ምዝበራ የረጅም ዓመታት ዕድሜ እንዳለው አውስቷል።


የዓለም የምግብ መርሐ ግብር(WFP) እና የዩናይትድ ስቴትሱ ዓለም አቀፍ የልማት ተራዶኦ (USAID)፣ ከዚኽ ምዝበራ ጀርባ ማን እንዳለ ምርመራ እያደረጉ መኾናቸውን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7838818.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7838818.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 25 Oct 2024 14:49:43 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤደን ገረመው, ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/bc7e1153-64ff-4a1b-97d7-d3c3f33121ac_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተመድ በረድኤት ሠራተኞች ላይ በሚደርስ ጥቃት ምክንያት  በአማራ ክልል ዕርዳታ ለማቋረጥ እያሰበ ነው</title>
            <description>

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በአማራ ክልል በረድኤት ሠራተኞች ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት ተከትሎ በክልሉ የምግብ እርዳታ አቅርቦትን ጨምሮ የሰብዓዊ ሥራዎችን ሊያቋርጥ እንደሚችል፣ ሮይተርስ የተመለከተው እና በሁለት ዲፕሎማቶች የተረጋገጠ ያለው ረቂቅ የውሳኔ ሀሳብ አመልክቷል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-violence-un/7815174.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-violence-un/7815174.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 08 Oct 2024 23:13:25 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/48a92bbf-0e8f-4787-bfab-cac94e89de29_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኢትዮጵያ ሲኖሩ የነበሩ 780 ሱዳናውያን ስደተኞች ወደ ሀገራቸው ተመለሱ</title>
            <description>

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን፣ ከመጠለያ ጣቢያዎች ወጥተው በአውላላ መንገድ ዳር እየኖሩ ከነበሩት የሱዳን ስደተኞች መካከል 780 የሚኾኑት ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን፣ የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር/ዩኤንኤችሲአር ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቀ፡፡ ዓለምአቀፉ የስደተኞች ተቋም፣ ለአሜሪካ ድምፅ በኢሜይል በሰጠው ማብራሪያ፣ በፀጥታ ችግርና በአገልግሎት እጥረት ምክንያት በኢትዮጵያ መኖር አንችልም ብለው፣ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የእግር ጉዞ ከጀመሩት ስደተኞች መካከል፣ 780 የሚሆኑት ሱዳን መድረሳቸውን እና እዚያም ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን ገልፆዋል፡፡ ወደ ሱዳን ሳይሻገሩ የቀሩት ደግሞ፣ በመተማ የስደተኞች መጠለያ እየኖሩ መሆናቸውን ገልፀው፣ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ግን አገልግሎት እያገኘን አይደለም ብለዋል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/sudan-refugees-arrive-safely-/7799143.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/sudan-refugees-arrive-safely-/7799143.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 25 Sep 2024 22:22:28 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ገ/ሚካኤል ገ/መድህን)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/DDBDA421-65C9-4F9C-B00E-58BDC682C041_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በመተማ በኩል ያለው የኢትዮጵያ እና የሱዳን ድንበር ተዘጋ
</title>
            <description>

በምዕራብ ጎንደር አካባቢዎች በተቀሰቀሰው ግጭት ሳቢያ፣ በመተማ በኩል ያለው የኢትዮጵያና የሱዳን ድንበር ዘመጋቱን የመተማ ዮሃንስ ከተማ ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ፡፡ ጉዳዩን አስመልክቶ ለአሜሪካ ድምፅ በኢሜይል ማብራሪያ የሰጠው የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር (ዩኤንኤችሲአር) በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች እና ባልታወቁ ታጣቂዎች መካከል ባለው ግጭት የተነሳ ኢትዮጵያን ከሱዳን የሚያገናኘው የጋላባት-መተማ ድንበር መዘጋቱን አስታውቋል፡፡


በአካባቢው በተካሄደው ግጭት በስደተኞች ላይ የደረሰ ጉዳት ግን አለመኖሩን ገልጸዋል፡፡ በመተማ ወረዳ የተለያዩ አካባቢዎች፣ በመንግስት የፀጥታ ሐይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ግጭቶች መቀጠላቸውንም የአሜሪካ ድምፅ ምንጮች አመልክተዋል።


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/metema-conflict/7774666.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/metema-conflict/7774666.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 07 Sep 2024 00:23:19 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/DDBDA421-65C9-4F9C-B00E-58BDC682C041_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሰሜን ሸዋ ዞን ታግተው ከነበሩት 52 መንገደኞች ስምንቱ አሁንም አልተለቀቁም</title>
            <description>

ትላንት ኀሙስ፣ ከዐዲስ አበባ ወደ ደብረ ማርቆስ ከተማ በሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ሲጓዙ የነበሩ 52 ሰዎች፣ በታጣቂዎች ታግተው እንደነበር የገለጸው በኦሮሚያ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር፣ ኾኖም አብዛኛዎቹ ወዲያውኑ አምልጠው ስምንት ተሳፋሪዎች ብቻ መቅረታቸውን አስታውቋል።።


በኦሮሚያ ክልል፣ በገብረ ጉራቻ እና ቱሉ ሚልኪ ከተሞች መካከል ባለ ቦታ ላይ፣ ከማሽላ ማሳ ውስጥ የወጡ ታጣቂዎች አውቶብሱን አስቁመው፣ አሽከርካሪውን ጨምሮ 52 ተሳፋሪዎችን ወደ ጫካ ወስደው እንደነበር ከእገታ ያመለጡ እማኞች ገልጸዋል።


በኦሮሚያ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደሪ አቶ ከፍያለው አደሬ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃል፣ 52ቱ ተሳፋሪዎች፣ እርሳቸው “ሸኔ” ሲሉ በገለጹት ታጣቂ ቡድን ታግተው የነበሩ ቢኾንም፣ “የጸጥታ ኀይሎች ብዙዎቹን ማስለቀቅ ችለዋል፤” ብለዋል።


የቀሩትን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/north-shoa-abduction/7765791.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/north-shoa-abduction/7765791.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 30 Aug 2024 22:23:42 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (አስቴር ምስጋናው)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-b513-08dcc927c561_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኢትዮጵያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ስደተኞችን ከእስር ማስፈታቱን ተመድ አስታወቀ</title>
            <description>የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር በምኅጻሩ ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር፣ ባለፈው ሐምሌ ወር፣ ከአጋሮች ጋራ በመተባበር፣ “በዘፈቀደ የታሰሩ” ያላቸውን በመቶዎች የሚቆጠሩ የከተማ ውስጥ ስደተኞችን ማስፈታቱን አስታውቋል፡፡


ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር፣ ከትላንት በስቲያ ሰኞ ባወጣው ሪፖርት፣ በዐዲስ አበባ 879 ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ያቀረቧቸውን አስተያየቶች እና ቅሬታዎች መሠረት በማድረግ እና ከኢትዮጵያ የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት ጋራ በመተባበር ችግሮቻቸውን ለመፍታት ባደረገው ጥረት ነው እስረኞችን ማስፈታቱን የገለጸው፡፡


ከእስር ተፈተዋል ያላቸው ስደተኞች፣ ከየትኛው ሀገር የመጡ እና ለምን ያኽል ጊዜ የታሰሩ እንደኾኑ ግን ሪፖርቱ አልጠቀሰም፡፡


በዚህ እና ተያያዥ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ ለማግኘት በኢሜይል ለላክንለት ጥያቄ ዩኤንኤችሲአር...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/unhcr-operational-report-/7762940.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/unhcr-operational-report-/7762940.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 28 Aug 2024 23:04:54 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-f8f3-08dcc79bc25f_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተፈናቃዮች ወደ ጠለምት ወረዳ መመለሳቸውን ወታደራዊ እዙ አስታወቀ</title>
            <description>የሰሜኑ ኢትዮጵያን ጦርነት ተከትሎ ከጠለምት አካባቢዎች ተፈናቅለው ነበር የተባሉ ከዐሥር ሺሕ በላይ ሰዎች፣ በአራት ዙሮች ወደ ቀዬአቸው መመለሳቸውን፣ በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የሰሜን ምዕራብ እዝ አስታወቀ፡፡


የዕዙ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄነራል መሰለ በለጠ፣ ለመንግሥታዊው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሰጡት መግለጫ፣ &quot;ከትግራይ እና ከዐማራ ክልሎች ተወካዮች ጋራ በመተባበር ተፈናቃዮቹን የመመለስ ሥራ ተሠርቷል፤&quot; ብለዋል፡፡




የጠለምት ወሰንና ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ግን፣ &quot;በተፈናቃይ ስም የህወሓት ታጣቂዎች ገብተዋል፤ ቀድሞ መግባባት ከተደረሰበት ውጭም፣ ቁጥሩ የበዛ ተፈናቃይ እንዲገባ ተደርጓል፤&quot; ሲሉ ይከሳሉ፡፡


የሰሜናዊ ምዕራብ ትግራይ ምክትል አስተዳዳሪ ከላሊ ሃጋዚ በተፈናቃዮች አመለላስ ሒደት እና በተሰነዘሩት ቅሬታዎች ላይ ምላሻቸውን ሊሰጡን ከተስማሙ በኋላ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-army-idps-rxn/7709785.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-army-idps-rxn/7709785.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 23 Jul 2024 22:03:17 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (መስፍን አራጌ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/7853907F-0D6C-4277-81F6-9364698A799A_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአውላላ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ጥቃት ሁለት ሱዳናውያን ተገደሉ</title>
            <description>
	ስደተኞቹ ወደ ዐዲሱ መጠለያ በመዛወር እንዲተባበሩ የስደተኞች ተቋሙ ጠየቀ


በምዕራብ ጎንደር ዞን በሚገኘው የአውላላ የስደተኞች መጠለያ፣ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ፣ ታጣቂዎች ፈጸሙት በተባለ ጥቃት ሁለት ሰዎች መገደላቸውን፣ የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቀ፡፡


በመጠለያው የሚኖሩ ስደተኞችም፣ በጥቃቱ የተገደሉት ሰዎች ባል እና ሚስት መኾናቸውን ጠቅሰው፣ “የአምስት ልጆች ወላጆች ነበሩ፤” ብለዋል፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመው የመጠለያ ጣቢያው ጥበቃ ከተነሣ በኋላ መኾኑንም ስደተኞቹ አመልክተዋል።




ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር በበኩሉ፣ የጸጥታ ችግር አለባቸው የሚባሉትን የአውላላ እና የኩመር መጠለያዎችን በሒደት ለመዝጋት፣ ስደተኞቹን በዚያው ዞን ወደሚገኝ አፍጥጥ ወደሚባል ዐዲስ የመጠለያ ጣቢያ ማዛወር መጀመሩን ገልጿል።


የቅዳሜው...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7708553.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7708553.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 22 Jul 2024 23:07:21 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ገ/ሚካኤል ገ/መድህን)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-cc94-08dca73ce103_cx0_cy3_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአውላላ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ጥቃት ሁለት ሱዳናውያን ተገደሉ</title>
            <description></description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7708550.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7708550.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 22 Jul 2024 23:06:47 +0300</pubDate>
            <category>ክምችት </category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><category>ድምጽ</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-cc94-08dca73ce103_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኩመር የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ጥቃት 10 የፖሊስ አባላት መገደላቸው ተገለጸ</title>
            <description>

በምዕራብ ጎንደር ዞን በሚገኘው የኩመር የስደተኞች መጠለያ አቅራቢያ በሚገኝ አንድ የፌደራል ፖሊስ ጣቢያ ላይ፣ ታጣቂዎች ፈጸሙት በተባለ ጥቃት፣ 10 የፖሊስ አባላት ሳይገደሉ እንዳልቀሩ መረዳቱን፣ የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር በምኅጻሩ ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቀ፡፡


በመጠለያው የሚኖሩ ስደተኞችም፣ ትላንት ረቡዕ ንጋት ላይ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ፣ መጠለያውን ሲጠብቁ የነበሩ የጸጥታ ኀይሎች መገደላቸውን ተናግረዋል፡፡


 ስለ ጉዳዩ፣ ከዐማራ ክልላዊ መንግሥት ኃላፊዎች እንዲሁም ከኢትዮጵያ የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለዛሬ አልተሳካም፡፡         


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/west-gondar-atrack/7703689.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/west-gondar-atrack/7703689.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 18 Jul 2024 21:37:55 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ገ/ሚካኤል ገ/መድህን)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-c441-08dca758171f_cx0_cy9_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተፈናቃዮችን ወደ ወልቃይት የመመለሱ ሒደት እንደሚጀመር የትግራይ ክልል አስታወቀ </title>
            <description>የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር “ምዕራብ ትግራይ ዞን” እያለ የሚጠራውና ከጦርነቱ ፍጻሜ በኋላ በዐማራ ክልል “የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን” ተብሎ ወደተቋቋመው አካባቢ፣ ተፈናቃዮችን መመለስ እንደሚጀመር፣ የትግራይ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት ተናግረዋል።


ምክትል ፕሬዚዳንቱ ሌተናንት ጀነራል ታደሰ ወረደ፣ ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ በሰጡት መግለጫ፣ በክልሉ ተባብሰዋል በተባሉ ወንጀሎች ተጠያቂነትን ለማስፈን ጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደሚሠራም ገልጸዋል።




 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/tigray-idps-return-plan/7699192.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/tigray-idps-return-plan/7699192.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 16 Jul 2024 00:57:23 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-1d59-08dca4dfc5ca_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በዓለምዋጭ የስደተኞች መጠለያ በታጣቂዎች ጥቃት ሞት እና የአካል ጉዳት ደረሰ</title>
            <description>በሰሜን ጎንደር ዞን በሚገኘው የዓለምዋጭ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ፣ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ እና ትላንት ሰኞ፣ ለዘረፋ የተደራጁ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት፣ አንድ ሰው መገደሉንና 10 ሰዎች መቁሰላቸውን ስደተኞች ተናገሩ፡፡


ስደተኞቹ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃል፣ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ምሽት ታጣቂዎች ወደ መጠለያው ገብተው፣ ስምንት ሰዎችን በስለት ወግተው ማቁሰላቸውን ተናግረዋል፡፡ ትላንት ሰኞ በተፈጸመ ጥቃት ደግሞ፣ የሰው ሕይወት ማለፉንና የቆሰሉም መኖራቸውን ገልጸዋል፡፡




መጠለያ ጣቢያው የሚገኝበት የዳባት ወረዳ የጭላ ቀበሌ አስተዳደር በበኩሉ፣ በሁለቱም ቀናት በተፈጸሙት ጥቃቶች፣ አንድ ሰው መገደሉንና የተጎዱም እንዳሉ አረጋግጦ፣ የመጠለያ ጣቢያውን ጸጥታ ለማስከበር እየሠራ መኾኑን ገልጿል፡፡


የኢትዮጵያ የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎትም፣ የመጠለያ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/alemwach-killing/7691453.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/alemwach-killing/7691453.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 09 Jul 2024 23:51:54 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ገ/ሚካኤል ገ/መድህን)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-50de-08dca03e6c65_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያ መንግሥት “ከሱዳኑ ጦርነት ይታደገን” ያሉ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እንዲመለሱ እየሠራ መኾኑን ገለጸ</title>
            <description>የሱዳኑ ጦርነት፣ የትግራይ ተወላጆች ወደተጠለሉባቸው መጠለያ ጣቢያዎች እየተቃረበ መኾኑን በመጥቀስ፣ በዚያ ያሉትን ስደተኞች እንዲታደግ የተጠየቀው የኢትዮጵያ መንግሥት፣ ኮሚቴ አቋቁሞ እየሠራ መኾኑን ለአሜሪካ ድምፅ ገልጿል፡፡


የኢትዮጵያ መንግሥት የስደተኞቹን ሕይወት እንዲታደግ፣ ትላንት ረቡዕ፣ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሑፍ ጥሪ ያቀረቡት፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የፌደራሉ መንግሥት የስደተኞቹ ሥቃይ እንዲያበቃ የሚችለውን ኹሉ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡




በሱዳኑ ጦርነት መስፋፋት ችግር ላይ መውደቃቸውን የገለጹት ስደተኞቹም፣ የሚመለከታቸው አካላት እንዲደርሱላቸው ተማፅነዋል፡፡


ስለ ጉዳዩ የአሜሪካ ድምፅ የጠየቃቸው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢዩ ተድላ፣ የሱዳኑ ጦርነት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/refugees-in-sudan/7685471.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/refugees-in-sudan/7685471.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 04 Jul 2024 22:38:21 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ገ/ሚካኤል ገ/መድህን)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-3415-08dc9c6016fc_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የትግራይ ተፈናቃዮች ከሰኔ 30 ቀን በፊት ወደቀዬአቸው ለመመለስ በድጋሚ ጠየቁ</title>
            <description>በትግራይ ክልል የተለያዩ ስፍራዎች የሚገኙ ተፈናቃዮች፣ ወደ ቀዬአቸው ለመመለስ የጠየቁበትን ሰላማዊ ሰልፍ፣ ትላንት እሑድ አካሒደዋል፡፡


በመቐለ ከተማ ሰልፍ የወጡ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች፣ መንግሥት ቃል በገባው መሠረት፣ ከሰኔ 30 ቀን በፊት ወደ ቀዬአችን ይመልሰን፤ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡




በሰልፉ ላይ፣ ተፈናቃዮች በተደጋጋሚ ሰልፍ መውጣታቸውን ያወሱት፣ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ፣ “የአሁኑ ሰልፍ የመጨረሻ ይኾናል፤” ብለዋል፡፡


የተፈናቃዮቹን አመላለስ ያለጸጥታዊ ችግር ለመፈጸም እንደሚሠራ ፕሬዚዳንቱ አመልክተዋል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/mekelle-demo/7668145.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/mekelle-demo/7668145.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 24 Jun 2024 22:23:05 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-bd1b-08dbb877cd62_cx0_cy8_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዓለም የስደተኞች ቀን - ቸልታው አዲስ ልምድ ሆኖ ይሆን?</title>
            <description>የረድዔት ቡድኖች ቀውስ በገጠማቸው በሱዳን፣ ሶማሊያ፣ በሳህል እና በሌሎች አካባቢዎች፤ ተግዳሮቶችን ለመቋቋም እጅግ አነስተኛ የሆነ የገንዘብ ድጋፍ ብቻ እንደሚደረግ ይናገራሉ። በዚህ ወር መግቢያ ላይ የኖርዌይ የስደተኞች ምክር ቤት (NRC) ኃላፊ “ሙሉ ለሙሉ ተፈናቃዮችን መዘንጋት አዲሱ ልምድ ሆኗል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡




ሄኔሪ ዊልኪንስ ስደተኞች እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት በገንዘብ ድጋፍ ዙሪያ ያላቸው አስተያየት ላይ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/africa-world-refugee-day/7663916.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/africa-world-refugee-day/7663916.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 21 Jun 2024 04:33:57 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/06a70000-0aff-0242-5493-08da197d7ee5_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የተመድ የስደተኞች ኮሚሽነር የሱዳኑ ጦርነት እንዲቆም ጠየቁ</title>
            <description>የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲ፣ “እብደት” ብለው የገለጹትና በሱዳን እንዲሁም በደቡብ ሱዳን የሚካሄደው ጦርነት እንዲቆም ጠይቀዋል።




ኮሚሽነሩ ዛሬ ታስቦ የዋለውን የዓለም የስደተንኞችን ቀን በማስመልከት በሁለቱ ሃገራት በጉብኝት ላይ ናቸው።


የቪኦኤ የተመድ ዘጋቢ ማርግሬት ባሺር ከኒው ዮርክ አነጋግራቸዋለች። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un-world-refugee-day/7663912.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un-world-refugee-day/7663912.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 21 Jun 2024 04:19:10 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/77149b13-b2c5-4f66-a2c5-8be1e1e63332_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኢትዮጵያ የሚኖሩ ስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች አገልግሎቶች እንዲሻሻሉ ጠየቁ</title>
            <description>በኢትዮጵያ ያሉ ስደተኞች፣ ከአገልግሎት አቅርቦት እና ከጸጥታ ጋራ የተያያዙ ችግሮች እንዲፈቱላቸው ጥሪ አቀረቡ።


በሰሜን ጎንደር ዞን በዓለምዋጭ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞች ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት አስተያየት፣ ባለፈው ማክሰኞ፣ በአካባቢያቸው፣ በመንግሥት የጸጥታ ኀይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተኩስ ልውጥ ተደርጎ፣ አንድ ስደተኛ በበራሪ ጥይት መቁሰሉን ገልጸው፣ በኹኔታው ስጋት እንዳደረባቸው ተናግረዋል፡፡




በምዕራብ ጎንደር ዞን ያሉት የሱዳን ስደተኞች ደግሞ፣ የጸጥታ እና የአገልግሎት አቅርቦት ችግሮች እንዳሉባቸው ጠቅሰው፣ የሚመለከታቸው አካላት ፍላጎቶቻቸውን እንዲያሟሉ ጠይቀዋል፡፡


ዛሬ እየተከበረ ያለውን “የዓለም ስደተኞች ቀን”ን በማስመልከት መግለጫ ያወጣው፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በበኩሉ፣ በስደተኞች አገልግሎት ላይ የሚታዩት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-refugees-/7663909.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-refugees-/7663909.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 20 Jun 2024 23:22:11 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ገ/ሚካኤል ገ/መድህን)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5828365f-4681-4aed-b61d-fda42f02f84f_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በመተማ ወረዳ አንዲት ሱዳናዊትን ጨምሮ ሦስት ሰዎች በታጣቂዎች ተገደሉ</title>
            <description>በምዕራብ ጎንደር ዞን፣ ባለፈው ሳምንት እሑድ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ፣ አንዲት ሱዳናዊት ስደተኛን ጨምሮ ሁለት ኢትዮጵያውያን መገደላቸውን፣ የመተማ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ፡፡




የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ደሳለኝ ሞገስ ግድያው የተፈጸመው፣ ከምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና ከተማ ገንደ ውኃ ወደ ነጋዴ ባሕር ሲጓዝ በነበረ አነስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ መኪና ላይ በተከፈተ ተኩስ እንደኾነ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡


የግድያ ድርጊቱን፣ የኢትዮጵያ የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎትም አረጋግጧል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/west-gonder-killings/7662337.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/west-gonder-killings/7662337.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 19 Jun 2024 22:22:50 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><author> voadigital@voanews.com (ገ/ሚካኤል ገ/መድህን)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9869053e-5648-4980-bcfe-4a5b73e72792_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>