<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>Ethiopian Refugee Crisis - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/6287</link>
        <description>Ethiopian Refugee Crisis</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>Ethiopian Refugee Crisis - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/6287</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2021 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Sat, 15 May 2021 12:05:50 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/ztotqmeigtqm" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>የተፈናቃዮች አቤቱታ ከመተከል ዞን ራንች መጠለያ ጣቢያ</title>
            <description>ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው በመተከል ዞን ራንች በተባለ ጊዚያዊ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የሚገኙ ተፈናቃዮች በጎርፍ አደጋ ድንኳኖቻቸው በመፍረሱ መጠለያ ማጣታቸውን ገለጹ።


የአማራ ክልል አደጋ መከላከል ምግብ ዋስትና እና ልዩ ድጋፍ የሚሹ ወገኖች ማስተባበሪያ ኮሚሽን በበኩሉ ችግሩን ለመፍታት እየጣርኩ ነው ብሏል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5889630.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5889630.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 May 2021 22:09:59 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (አስቴር ምስጋናው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5889630.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/DF5D5FB2-06A2-4C05-AA4F-C4D5C730190C_cx10_cy1_cw90_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ወደ ደቡብ ወሎ የሚገቡ ተፈናቃዮች ቁጥር መጨመሩ ተገለጸ</title>
            <description>በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተውን አለመረጋጋት ተከትሎ ወደ ደቡብ ወሎ የሚገቡት ተፈናቃዮች ብዛት እየጨመረ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ፡፡


ዞኑ አራት ሳምንታት ባለሞላ ጊዜያት ውስጥ ብቻ ከ8 ሽህ በላይ ተፈናቃዮችን ተቀብሏል፡፡ እስካሁን 18 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የምግብ፣ የአልባሳትና የገንዘብ ድጋፍ በመንግሥት፣ በውጭ አገራት በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣ በአካባቢው ኗሪዎችና በባለሃብቶች ተደርጓል፡፡


በጊዜያዊ መዋጮና የእለት ደራሽ ድጋፍ ተፈናቃዮቹን በዘላቂነት ማቋቋም አይቻልም የሚለው የዞኑ አስተዳደር የፌዴራሉም ሆነ የክልሉ መንግሥት በዚህ በኩል ትኩረት ሰጥተው እንዲንቀሳቀሱ ጥሪ አስተላልፏል፡፡


የክለልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን 878ሽህ የሚደርሱ የአማራ ተወላጆች በክልሉም ሆነ ከክልሉ ውጭ መፈናቀላቸውን ይፋ አድርጓል፡፡


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5885234.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5885234.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 May 2021 21:41:26 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (መስፍን አራጌ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5885234.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/E8A904EC-68D2-411C-9C6D-98355FC3EE8B_cx5_cy0_cw92_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የትግራይ ተፋናቃዮች በመቀሌ</title>
            <description>ሚያዚያ 27/2013 ዓ.ም</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5879179.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5879179.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 05 May 2021 18:34:00 +0300</pubDate>
            <category>ቪድዮ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5879179.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/7b1503b8-2513-4591-ad22-6037a7c14bfd_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>“ትግራይ የተላከው እርዳታ ጊዜው ያለፈበት አይደለም” - ቀይ መስቀል</title>
            <description>የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በግጭት ምክንያት ለተፈናቀሉ ግማሽ ሚሊዮን ገደማ ኢትዮጵያውያን ልዩ ልዩ ድጋፎችን እያደረገ መሆኑን አስታወቀ። ማህበሩ በመቀሌ ለሚገኙ ተፈናቃዮች የመጠቀሚያ ጊዜአቸው ያለፈ ዘይትና ስንዴ አቅርቧል የሚለውን ወቀሳም መሰረተ ቢስ ነው ብሎታል።


የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በትግራይ በአማራ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝና በደቡብ ክልሎች በልዩ ልዩ ግጭቶች ተጎጂ ለሆኑ ግማሽ ሚሊዮን ዜጎች ልዩ ልዩ ድጋፍ ማድረጉን የማህበሩ ህዝብ ግንኙነት ዶክተር ሰለሞን አሊ ለቪኦኤ አስታወቁ።


ከግጭት ጋር ባልተያያዘ መደበኛ አገልግሎቱ ከ10 ሚሊዮን ገደማ ኢትዮጵያውያንን ተጠቃሚ እንዳደረገ የገለጹት ህዝብ ግንኙነቱ የግጭት ሰለባዎችን ግን ለሌሎች ጉዳዮች ይዟቸው የነበሩ በጀቶችን ሁሉ በማጠፍ ለመደገፍ ጥረት ማድረጉን ነው ዶክተር ሰለሞን የገለጹት።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5878157.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5878157.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 04 May 2021 23:40:28 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (አዲስ ቸኮል)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5878157.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/A2A59A01-4BE4-413D-94C5-17121BDDDFC6_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተፈናቃዮች በመቀሌ ቅሳነት ትምህርት ቤት መጠለያ</title>
            <description>ሚያዚያ 25/2013 ዓ.ም</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5875960.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5875960.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 03 May 2021 14:43:00 +0300</pubDate>
            <category>ቪድዮ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (አለም ፍሰሃ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5875960.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/05950afd-f251-4ae6-846c-6f8f84355d6e_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተፈናቃዮች በመቀሌ ማይ ወይኒ መጠለያ</title>
            <description>ሚያዚያ 22/2013 ዓ.ም</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5873817.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5873817.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 01 May 2021 00:26:00 +0300</pubDate>
            <category>ቪድዮ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (አለም ፍሰሃ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5873817.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/4d72e716-77c7-4e34-9fd5-23a3ac603170_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተመድ በትግራይ ጉዳይ</title>
            <description>በትግራይ ክልል በችግር ላይ ላለው ህዝብ ሰብዓዊ ረድዔት በነጻነት ተንቀሳቅሶ ለማቅረብ የሚደረገው ጥረት በሀገሪቱ ባለው ውስብስብ እና የማያስተማምን የፀጥታ ሁኔታ ምክንያት አሁንም መስተጓጎሉ እንደቀጠለ ባልደረቦቻችን ገልጸውልናል ሲል ተመድ አስታወቀ።

 የተመድ ዋና ጸኃፊ ምክትል ቃል አቀባይ ፋርኻን ሃቅ በትናንት ዕለታዊ ጋዜጣዊ መግለጫቸው በክልሉ ግጭቱ ከተቀሰቀሰ ስድስት ወር በተጠጋው በዚህ ወቅት አብዛኛው የገጠሩ አካባቢ አሁንም የኮሙዩኒኬሽንና የኤሌክትሪክ አገልግሎቶች እንደሌለው ይህም የጤና አገልግሎቶች እና የውሃ አቅርቦት ሌላም አገልግሎት እንዳይደርስ አድርጓል ብለዋል።

የክልሉ ህዝብ ያለበት የምግብ ችግር አሁንም እጅግ የከበደ እንደሆነ የተናገሩት የመንግሥታቱ ድርጅት ምክትል ቃል አቀባይ ሃቅ በመላዋ ትግራይ በእኛ ግምት አራት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ህዝብ የምግብ እርዳታ የሚጠብቅ ነው ሲሉ አስረድተዋል። ድርጅታቸው ከሌሎች የሰብዓዊ ረድዔት አጋሮቹ ጋር ሆኖ ለዚህ ችግር የሚሰጠውን ድጋፍ ማሳደጉን እንደቀጠለ ገልጸው ይህም የጾታዊ ጥቃቶች ሰለባዎች መለየት እና አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግን ያካትታል ብለዋል።

የዓለም የምግብ ፕሮግራም ድርጅት ካለፈው እአአ መጋቢት ወር ወዲህ ባከፋፈለው ዘጠኝ ሽህ ቶን ምግብ በክልሉ በሰሜን ምዕራብ እና በደቡባዊ ዞን አምስት መቶ ሃያ ዘጠኝ ሽህ ነዋሪዎች ሊያደርስ መቻሉን በእዳጋ ሃሙስ እና አጺቢ ከተሞች ለሰላሳ አራት ሽህ ህዝብ የምግብ እርዳታ ማከፋፈሉን እና ባለፈው ሳምንት ከሰባት መቶ ሽህ በላይ ህዝብ ውሃ የማጓጓዝ አገልግሎት መሰጠቱን ዘርዝረዋል።

የረድዔት አጋሮቻችን እስካሁን ለሁለት መቶ ሰማኒያ አምስት ሽህ ተፈናቃዮች የመጠለያና ምግብ ያልሆኑ ቁሳቁስ እርዳታዎችን አድርሰዋል፤ ይህ ግን በእርዳታ ዕቅዳችን ካቀድነው የህዝብ ቁጥር አስር ከመቶው ብቻ ነው ሲሉ የመንግሥታቱ ድርጅት ቃል አቀባይ አመልክተዋል።

አስከትለውም መቀሌ ከተማ ውስጥ ከአስራ ዘጠኝ ሽህ በላይ ሰዎች ለማስጠለል የሚችል የተፈናቃዮች ካምፕ የማዘጋጀቱ ሥራ እንደቀጠለ ተናግረዋል።

ህዝቡ ካለበት ችግር አንጻር እየተሰጠ ያለው የእርዳታ ምላሽ እጅግ አናሳ መሆኑ የሰብዓዊ ረድዔት አጋሮቻችን አስታወቀውናል በሚፈለገው መጠን እርዳታ ለማቅረብ ገንዘብ እና ባልተገደበ እና የደህንነት ጥበቃ ባልተለየው መልኩ ተረጂው ህዝብ ጋር መድረስ መቻል ይኖርብናል ብለዋል።


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5873742.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5873742.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 30 Apr 2021 23:07:04 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5873742.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/A0B34EB6-FDEB-47C1-A3EF-9BEC2160F931_cx6_cy13_cw84_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>እንባ ጠባቂው ስለተፈናቃዮች ተናገሩ</title>
            <description>በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋና ኦሮሞ ብሔረሰብ እንዲሁም በቤንሻንጉል ካማሼ አካባቢዎች በተቀሰቀሱ ግጭቶች ወደ 5መቶ ሺህ የሚጠጋ ሰው መፈናቀሉን የኢትዮጵያ የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5870931.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5870931.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 29 Apr 2021 04:46:50 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (መስፍን አራጌ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5870931.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5637C839-BC7F-49AD-9680-336D8A5CB55E_cx0_cy7_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>እንባ ጠባቂው ስለተፈናቃዮች ተናገሩ</title>
            <description>በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋና ኦሮሞ ብሔረሰብ እንዲሁም በቤንሻንጉል ካማሼ አካባቢዎች በተቀሰቀሱ ግጭቶች ወደ 5መቶ ሺህ የሚጠጋ ሰው መፈናቀሉን የኢትዮጵያ የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡</description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2021/04/28/0a592135-efe3-4a9d-a2fc-3d6ae98c820b_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5870357.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 28 Apr 2021 23:02:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (መስፍን አራጌ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5637C839-BC7F-49AD-9680-336D8A5CB55E_cx0_cy8_cw100_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የመንግሥታቱ ድርጅት ሰለሰሜን ሸዋና ኦሮምያ ልዩ ዞን</title>
            <description>በማኅበረሰቦች መካከል በተፈጠሩ ግጭቶች ምክንያት አማራ ክልል ውስጥ ያለው የፀጥታ ሁኔታ አሁንም ውጥረት የነገሠበትና ያልተረጋጋ መሆኑን ከሰብዓዊ ረድዔት ባልደረቦቻችን አገኘነው ካሉት መረጃ መገንዘባቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቃል አቀባይ ፋርሃን ሃቅ ትናንት ለጋዜጠኞች ገልፀዋል።


ቁጥሩ እጅግ የበዛ ሰው ለመፈናቀሉ ምክንያት በሆኑትና ዝርፊያ፣ የንብረትና የመሠረተ ልማት ውድመት ባስከተሉት ግጭቶች በህይወትና በአካል ላይ የደረሰው ጉዳት መጠን በውል እንደማይታወቅ አመልክተዋል።


መጋቢት 9/2013 ዓ.ም በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ አንድ ሰው መገደሉን ተከትሎ ግጭት መቀስቀሱን ቃል አቀባዩ ጠቅሰው ከሁለት ቀናት በኋላ በተፈፀሙ ጥቃቶች በሰሜን ሸዋ እና በኦሮምያ ልዩ ዞን አካባቢዎች ቢያንስ 60,000 የሚደርስ ቁጥር ያለው ሰው መፈናቀሉን፣ ተከትሎም ሚያዝያ 9/2013 ዓ.ም እንደገና በከተሞች መሃል እና በዋናዋና አውራ ጎዳናዎች ላይ በተፈጸሙ ጥቃቶች ከቀደመውም የበለጠ ህዝብ መፈናቀሉንና መጠነ ሰፊ ጉዳት መድረሱን ፋርሃን ሃቅ አስረድተዋል።


በዚህ የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት የተፈናቀለውን ሰው ቁጥር ስፋት በውል ማረጋገጥ አለመቻላቸውን የሰብዓዊ ረድዔት አጋሮቻቸው እንደገለጹላቸው የመንግሥታቱ ድርጅት ቃል አቀባይ ጠቅሰው፤ ይሁን እንጂ በሰሜን ሸዋና በኦሮምያ ልዩ ዞኖች ውስጥ የተፈናቃዩ ቁጥር በትንሹ 330,000 መሆኑን የክልሉን ባለሥልጣናት ጠቅሰው ተናግረዋል።


ሃቅ አስከትለውም ለተፈናቃዩ የሚያስፈልገው ረድዔትና የተደቀኑት አደጋዎች ሁኔታና መጠን ዳሰሳ የፀጥታው ሁኔታ እንደፈቀደ እንደሚከናወን ገልፀዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5868575.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5868575.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 27 Apr 2021 17:45:44 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5868575.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/BF762538-4979-41D0-95A7-E875E7FFE725_cx0_cy8_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ለሰሜን ሸዋ ተፈናቃዮች እርዳታ እየደረሰ ነው</title>
            <description>የፌዴራል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ሰሞኑን በሰሜን ሸዋ ዞን በተፈጠረው ግጭት ለተፈናቀሉት የነፍስ ደራሽ እርዳታ መስጠቱን ኮሚሽኑ አስታወቀ። 
በክልሉ 11 ዞኖች ከሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተፈናቀሉ ከ600ሺ በላይ ተፈናቃዮች ይገኛሉ ያለው ኮሚሽኑ ለሁሉም ድጋፍ እያደረግኩ ነው ብሏል።</description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2021/04/23/1df9e9ba-ea16-430d-ac3f-8d7ca8a37082_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5864859.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 24 Apr 2021 00:02:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (አዲስ ቸኮል)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/DFBB8ADD-8C12-4CF7-94B1-10E87E1BDBD0_cx0_cy5_cw100_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የጸጥታ ምክር ቤት ኢትዮጵያ ውስጥ መረጋጋት እንዲመለስ አሳሰበ</title>
            <description></description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2021/04/23/f7cd76d8-b615-43d3-aa10-12cd5374fc9d_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5864811.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 23 Apr 2021 23:05:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/BC7DD99C-5F09-470E-AE8C-8D9C3060AEC1_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የጸጥታ ምክር ቤት ኢትዮጵያ ውስጥ መረጋጋት እንዲመለስ አሳሰበ</title>
            <description>ትግራይ ክልል ውስጥ የሰብዓዊ ረድዔት በተፋጠነ ሁኔታ የሚዳረስበት ሁኔታ እንዲጠናከር እና ክልሉ ወደ ነበረበት መረጋጋት እንዲመለስ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት አሳስቧል።
በሌላ በኩል ክልሉ ውስጥ ተፈጥረዋል ለሚባሉት የመብቶች ጥሰቶችና በደሎች አጥፊዎችን በተጠያቂነት ለመያዝ መንግሥት ቁርጠኛ መሆኑን በመንግሥታቱ ድርጅት የኢትዮጵያ ልዑክ ያሳወቀ ሲሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ህግን የማስከበር ተግባር የኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ መሆኑን አመልክቷል።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5864791.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5864791.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 23 Apr 2021 22:23:25 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (አዳነች ፍሰሀየ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5864791.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/BC7DD99C-5F09-470E-AE8C-8D9C3060AEC1_cx0_cy5_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ማረት ትግራይ ውስጥ እርዳታ እያከፋፈለ ነው</title>
            <description>የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (USAID) አስቸኳይ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች እና ነዋሪዎች መርጃ እንዲውል የለገሰው 1 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ 59 ሺሕ ሜትሪክ ቶን ምግብ ለማኅበረሰቡ መከፋፈል መጀመሩን፤ ማኅበራዊ ረድኤት ትግራይ (ማረት) አስታወቀ።


በአሁኑ ጊዜ የትግራይ ሕዝብ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ስለሚገኝ በልማት ድርጅቱ አማካኝነት ለ2.8 ሚሊዮን ሕዝብ የሚደረገው ድጋፍ በየወሩ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት እንደሚሰጥ የድርጅቱ ኃላፊ ተናግረዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5860552.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5860552.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 20 Apr 2021 23:12:27 +0300</pubDate>
            <category>Ethiopian Refugee Crisis</category><category>ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5860552.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/4317DF2F-41DD-4A4B-A44B-D00772627E30_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የአሜሪካ መንግሥት ለትግራይ ቀውስ 305 ሚሊዮን ዶላር ረድቷል</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዩ ኤስ ኤድ) በትግራይ የአደጋ ጊዜ ምላሽ ሰጭ ቡድን መሪ የሆኑት፣ ኤምሊ ዴኪን፣ በትግራይ ክልል ተጎጂ ለሆኑ ተፈናቃዮች አስፈላጊውን የሰብአዊ እርዳታዎችን እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የአሜሪካ መንግሥት እስካሁን በክልሉ ባለው ግጭት ተጎጂ ለሆኑ ሰዎች እርዳታ የሚውል ወደ 305 ሚሊዮን ዶላር ማውጣቱንም አስረድተዋል፡፡ የቡድን መሪዋን ያነጋገረው የቪኦኤ ትግርኛ ክፍል ባልደረባችን በትረ ሥልጣን ከላከልን ዘገባ ተከታዩን አጠናቅረናል፡፡


ዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዩ ኤስ ኤድ)፣ በትግራይ የአደጋ ጊዜ ምላሽ ሰጭ ቡድን መሪ ፣ ኤምሊ ዴኪን በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል፣ በግጭቱ የተጎዱ ወገኖችን ብዛትም ሆነ የሁኔታውን አሳሳቢነት በመግለጽ፣ ድርጅታቸውም ሆነ አጋሮቻቸው በመስጠት ላይ የሚገኙትን ሰብአዊ እርዳታ እንደሚቀጥሉበት ተናግረዋል፡፡


 “በተለይ በሽሬ አካባቢ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ የተፈናቃይ ህዝብ ክምችት እንዳለ እናውቃለን፡፡ ስለዚህ እነዚያ ሰዎች በስፍራው እንደደረሱም የሚያስፈልጋቸው የነፍስ አድን አቅርቦት ሁሉ እንዲያገኙ ብዙ ጥረት” ይደረጋል በማለት ተከታዩን ብለዋል፡፡


“በአሁኑ ወቅት ትግራይ ውስጥ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ግምት መሠረት፣ በጠቅላላው ወደ 4.5 ሚሊዮን ሰዎች የሰብአዊ እርዳታ እንደሚሹ እናውቃለን፡፡ ያ በጣም እጅግ ከባድ የሆነ ሥራ ነው፡፡ ስለዚህ ከአጋሮቻችን ጋር ሆነን የህይወት አድን እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሁሉ በትክክል ተደራሽ መሆናችንን በማረጋገጥ መስራታችንን ቀጥለናል፡፡”




በአሁኑ ሰዓት “እርዳታ ለመስጠት በማይቻልበት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ በርካታ ሰዎች መኖራቸውን እናውቃለን” ያሉት ኤምሊ፣ ያም በጣም አሳሳቢ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


እርዳታ ወደ ሚያስፈልጋቸው ወደ እነዚህ ሰዎች ዘንድ ለመድረስና፣ አጋሮቻችንም የሚያገኟቸው መሆኑን ለማረጋገጥ፣ በኤምባሲያችን በኩል፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር እየሠራን ነው ብለዋል፡፡


አንዳንድ ችግሮች አሉ፣ ተረጅዎችን አጋሮቻችን በቀላሉ ሊያገኛዋቸው የሚችሉባቸው አካባቢዎች፣ በትላልቅ ከተሞችና ከዋና ዋና መንገዶች አቅራቢያ ባሉ አካባቢዎች ነው፡፡ ካሉ በኋላ፣ ስለሆነም “ እርዳታው አቅርቦት ሊደረስባቸው ባልተቻለባቸው አካባቢዎች በመድረስ፣ እርዳታውን ላላገኙ ሰዎች ለመድረስ እንዲቻል፣ ከተባበሩት መንግሥታት አጋሮች ድርጅቶች ጋር እየተሠራ” መሆኑንም ገልጸዋል፡፡


በኣጠቃላይ ግን ለህዝቡ በሚያስፈልገው የእርዳታ መጠንና ዓይነት የተነኩ መሆኑንም ሃልፊዋ ሲገልጹ እንዲህ ብለዋል


“በተለያዩ ዘርፎች የምግብ ዋስትና የተመጣጠነ ምግብ የጤና ንጽህንና የንጹህ ውሃ በሌሎች ዘርፎች ያሉትን ጨምሮ በሚያስፈልጉ ሰብአዊ እርዳታዎች ብዛት ዓይነትና መጠን ተነክተናል፡፡ ከአጋሮቻችን ጋር ሆነን እርዳታው በቀጥታ ከሚያስፈልጋቸው ጋር በቀጥታ በመገናኘት ውጤታማ በሆነ መንገድ በምንመድበው ገንዘብም ሆነ በምንሰጠው እርዳታ ልንረዳቸው የምንችልበትን መንገድ በማፈላለግ ጠንክረን ሠርተናል፡፡” ብለዋል፡፡


ለሰአብዊው እርዳታ፣ የዩናይትድ ስቴትስ መንግስት፣ እስካሁን ወደ 305 ሚሊዮን ዶላር ለግሷል፡፡ ያሉት ኃላፊዋ፣ ይህ እርዳታ በጣም አስፈላጊ ለሆኑ የምግብ እርዳታዎች፣ ለውሃ፣ ለመድሃኒት አቅርቦት፣ በክልሉ ውስጥ ለተፈናቀሉ ሰዎች፣ ደህንነቱ የተጠበቀ መጠለያ ማቅረብና ከግጭት አካባቢዎች የሚሸሹ ሰዎችንም ደህንነት ለመጠበቅ የሚረዱ፣ የተለያዩ ድጋፎችን ለመስጠት የዋለ ነው፡፡” በማለት ተናግረዋል፡፡


ለመጠለያ እንዲውሉ በቅርቡ ወደ አገር ውስጥ ስለገቡት እቃዎችም የተደሰቱ መሆኑን ኃላፊዋ እንደሚከተለው ገልጸዋል፡፡


“ትግራይ ክልል እየተካሄደ ባለው ግጭት ተጎጂ ለሆኑ ከ82ሺ,000 በላይ ሰዎች ለሚቀልሷቸው የአስቸኳይ ጊዜ መጠለያዎች መከለያ የሚሆን፣ 1ሺ500 ጥቅልና ጠንካራ የፕላስቲክ መሸፈኛዎችን በአውሮፕላን ከዱባይ አጓጉዘን አዲስ አበባ በማስገባታችንም ደስ ብሎናል፡፡ እነዚህን ወደ መቀሌ ሽሬ እና እርዳታው እጅግ በጣም ወደሚያስፈልጋቸው አካባቢዎች እናጓጉዛለን፡፡”


“ከምናደርጋቸው ሌሎች ነገሮች ብዙ ሰብሎች መውደማቸውንና የሰዎችና የገበያ ቦታዎች መስተጓገላቸውን ተገንዝበናል፡፡ ብዙ ሚሊዮን ሰዎች ቤቶቻቸውን ለቀው እንደተሰደዱም ይታወቃል፡፡” ያሉት የዩኤስ ኤድ ኃላፊ ኤምሊ ዴኪን፣ በምግብ አቅርቦት በኩል ለተረጅዎቹ አሁን እየተደረገ ያለውን ድጋፍ እንደሚከተለው ዘርዝረዋል፡፡


“አሁን የምንሰጠውን የምግብ እርዳታ በማጠናከር ወደ አንድ መቶ ስድስት ሺ ሜትሪክ ቶን ስንዴ፣ የምግብ ዘይት እንዲሁም ልዩ የተመጣጠነ ምግብ ከዚያ ውስጥ ወደ 4 ሚሊዮን ህዝብ በተመጣጠነ የምግብ እጥረት የተጎዱ ወደ 400ሺ የሚደርሱ ህጻናትና ሴቶችን ጨምሮ መመገብ የሚችል ነው፡፡ ከአጋሮቻችንም ጋር በመሆን ወደ 140ሺ ለሚሆኑ ሰዎች ንጽሁ የመጠጥ ውሃ ለማዳረስ እንዲሁም የንጽህና መጠበቂያ ቁሶችን እና የውሃ መቅጃና ማጠራቀሚያ እቃዎችን ለማቅረብ እየሠራን ነው፡፡”


“አጋሮቻችንን የመድሃኒት አቅርቦትን ደህንነታቸው በተጠበቀ ስፍራ እንዲያኖሩና ለሴቶችና ህጻናት የምክር አገልግሎቶችን በመስጠት እንዲሁም በግጭቱ የተነሳ፣ ከወላጆቻቸው የተነጠሉ ህጻናትን ከቤተሰቦቻቸው ጋር መልሶ በማገናኘት እንዲሁም ቀደም ሲል እንደገልጽኩት የመጠለያ ፍላጎቶችን ለማሟላት ከኢትዮጵያ መንግስትና ከሰብአዊ እርዳታ ሰጭ አጋር ድርጅቶቻችን ጋር በመሆን፣ ከክልሉ የተፈናቀሉ ዜጎችን በሽሬና አካባቢው ለማስፈር የሚረዱ መጠለያዎችን እየሠራን ነው፡፡” በማለት ዩኤስ ኤድ በትግራይ እያደረገ ያለውን ነገር ዘርዝረውዋል፡፡


በትግራይ የዩ ኤስ ኤድ፣ የአደጋ ጊዜ የእርዳታ ምላሽ ሰጭ ቡድን፣ ድርጅታቸው በሱዳን የተጠለሉትን ስደተኞችንም እንደሚረዱ ተናግረዋል፡፡


“ዋነኛው ትኩረታችንን ያደረግነው ኢትዮጵያ ውስጥ በትግራይ ክልል ለቀሩት ይሁን እንጂ፣ በሱዳን ያሉትን ስደተኞችን ከዓለም ምግብ ድርጅት አማካይነት አጣዳፊ የምግብ እርዳታዎችን እንሰጣለን” ብለዋል፡፡


እስካሁን በትግራይ ውስጥ በሚሰጡት ሰብአዊ አገልግሎት ሊጠቅሱት የሚችሉት ምንም ዓይነት ችግር ያልደረሰባቸው መሆኑን የገለጹት፣ የዩኤስ ኤድ ሓላፊዋ ኤምሊ ዴኪን፣ “በዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት በኩል፣ ለትግራይ ህዝብ ትልቅ ድጋፍ ያለ ይመስለኛል፡፡ እርዳታችንንም የምቀጥልበት ሲሆን ከአጋሮቻችን ጋር በመስራት የሚሰጠው ሰብአዊ እርዳታ በሚያስፈልገው መጠን መሟላቱን ለማረጋገጥ፣ ሌሎች ለጋሽ ድርጅቶችም፣ በክልሉ ላለው ችግር እርዳታቸውን እንዲለግሱ እናበረታታለን፡፡” ማለታቸውን፣ ከቪኦኤ ትግርኛው ክፍል የተላከልን የበትረ ስልጣን ዘገባ ያስረዳል፡፡ 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/tigray-usaid-emily-4-20-2021/5860520.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/tigray-usaid-emily-4-20-2021/5860520.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 20 Apr 2021 22:29:28 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/tigray-usaid-emily-4-20-2021/5860520.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/EC7BC574-6AB1-49CA-B3E2-76E9EC3C90CE_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኅዳሴ ጉዳይ ኢትዮጵያውያን ምሁራን ሚዲያውን ወቀሱ</title>
            <description></description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2021/04/19/5b5976e2-6595-4950-8944-01b199a54731_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5859101.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 19 Apr 2021 23:27:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/e311b069-62d9-40ac-a8a5-40b6ea0b0a9b_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የተፈናቀሉ ነዋሪዎች ቁጥር ከ250 ሺሕ በልጧል ተባለ</title>
            <description>በአማራ ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን መፈናቀል ያወገዘ ሰልፍ በደሴ ከተማ ተካሄደ</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5859072.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5859072.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 19 Apr 2021 22:58:38 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (መስፍን አራጌ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5859072.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/7853907F-0D6C-4277-81F6-9364698A799A_cx0_cy8_cw72_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የምዕራብ ወለጋ ተፈናቃዮች በአማራ ክልል</title>
            <description></description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2021/04/16/79bbbaf2-fddb-4b84-91d1-fd04739aa82d_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5856144.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 16 Apr 2021 22:25:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/021543F9-BC7A-4862-A3BE-1289A7863BAA_cx0_cy17_cw100_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከአስቸጋሪው የየመን ስደት 160 ኢትዮጵያውያን ቢመለሱም በሺዎች የሚቆጠሩ ይቀራሉ</title>
            <description>የመን ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 160 ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ማክሰኞ ከኤደን ወደ አዲስ አበባ መውሰዱን ዓለም አቀፉ የፍልሰትድርጅት (IOM) አስታወቀ። ይሁን እንጂ አሁንም ኢትዮጵያውያን የሚበዙበት 32 ሺሕ ስደተኞች የመን ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይገኛሉ።


ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት አይ ኦኤም ስደተኞቹን ወደ ሃገራቸው በሰላም እንዲመለሱ ያደረገው ሕገወጥ አዘዋዋሪዎች ስደተኞቹን ወደ ጅቡቲለማሻገር የተጠቀሙበት ጀልባ የኤደን ባህረ ሰላጤ ላይ ተገልብጦ ቢያንስ 42 ሰዎች ህይወታቸው ካለፈ ከአንድ ቀን በኋላ ነው። ጀልባው ወደ 60 የሚጠጉ ሰዎችን አሳፍሮ የነበረ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ በየመን ያለውን ግጭት የሸሹ ከደርዘን በላይ ሕፃናት ይገኙበታል።


ድርጅቱ አያይዞ እደተናገረው በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች እንደ ሶማሊያ እናኢትዮጵያ ካሉ ሀገራት እየተሰደዱ ወደ ሳዑዲ አረቢያ እና በሌሎችየባህረ ሰላጤው አገራት ሥራ ለማግኘት በየዓመቱ አደገኛውን መንገድ ያቋርጣሉ ብሏል።


የድርጅቱ ቃል አቀባይ አንጌላ ዊልስ ብዙዎቹ ድንበሩን አቋርጠው በጭራሽ ያሰቡበት አይደርሱም አብዛኞቹ በየመን እጅግ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥይገኛሉ ብለዋል። በአሁኑ ሰዓትም አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን የሚበዙበት 32 ሺሕ ስደተኞች የመን ውስጥ እንደሚገኙ አያይዘው ተናግረዋል።


“ብዙዎቹ አደገኛ በሆኑ ሁኔታዎች ውስጥ ነው ያሉት፣ መጠለያ ስለሌላቸው መንግድ ላይ ያድራሉ ምንም አይነትአገልግሎትችም አያገኙም። ሌሎችደግሞ በእስር ላይ ናቸው ወይም በህገወጥ አዘዋዋሪዎች ተይዘዋል። በየመን ያሉስደተኞች ጉዳይ እጅግ አሳዛኝ ከመሆኑ የተነሳ ወደ ሀገራቸውለመመለስ ያላቸው አማራጭ ህገ ወጥ አዘዋዋሪዎቹ ብቻእንደሆነ ይሰማቸዋል።” ብለዋል።


እነዚህ ስደተኞች ለዚህ አሰቃቂ እና አብዛኛውን ግዜ በአሳዛኝ ሁኔታ ለሚደመደመው ጉዞ ከፍተኛ ገንዘብ ለአሻጋሪዎች ለመክፈል ይገደዳሉ።አደጋዎች ቢኖሩም ደግሞ ስደተኞቹ ወደ ሃገራቸው ለመመለስ በጣም ይፈልጋሉ። ዌልስ ባለፈው ወር ብቻ ወደ ጅቡቲ በሚወስደው የባህር ጉዞ ላይላይ ቢያንስ 20 ሰዎች መስጠማቸውን ጠቁመዋል።


“እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከ ግንቦት 2020 ጀምሮ ከ 11 ሺህ በላይ ስደተኞች በህገ ወጥ አዘዋዋሪዎች አማካኝነትአደገኛ የሆነ የጀልባ ጉዞበማድረግ ወደ አፍሪካ ቀንድ ሀገራት ተመልሰዋል። ለመመለስ ፈቃደኛ የሆኑትን ሰዎችየሚያግዘው የዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት ፕሮግራምከየመን መውጣት ላቃታቸው መውጫ መንገድ ያዘጋጃል።ስለዚህ በነዚህ መንገዶች ላይ የሚግኙ ሀገራት መንግስታቶች ይህን ጥረታችንንእንዲደግፉና ስደተኞቹ ደህንነታቸውተጠብቆ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱበትን ሁነታ ለመፍጠር እንዲተባበሩ ጥሪያችንን እናቀርባለን።”


አይ.ኦ.ኤም ከጥቅምት ወር ጀምሮ በየመን የሚገኙና ወደ ሃገራቸው ለመመለስ የሚፈልጉ ከ6000 በላይ ስደተኞችን መመዝገቡን አስታውቋል።በተጨማሪም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰነድ አልባ ስደተኞች ዜግነታቸው እስኪረጋገጥ እና ለጉዞ የሚያስፈልጋቸውን ሰነድ እየተጠባበቁ የሚገኙስደተኞች ይገኛሉ። እነርሱም ሰነድ ያገኙና አንድ ቀን ወደ ሃገራቸው ይጓዛሉ።


(በሊሳሽ ላይን ከጄኔቫ ለተጠናቀረው ዘገባ ጽዮን ግርማ ወደ አማርኛ መልሳዋለች)






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-migrants-yemen-4-16-2021/5856044.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-migrants-yemen-4-16-2021/5856044.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 16 Apr 2021 21:20:54 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ጽዮን ግርማ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-migrants-yemen-4-16-2021/5856044.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/36fdba22-c3e7-4328-b98e-258ca2255e08_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ትግራይ - ኢትዮጵያ፤ ከግጭት ወደ ሰብዓዊ ቀውስ</title>
            <description>ሚያዚያ 7/2013 ዓ.ም</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/tigray-Ethiopia-from-conflict-to-humanitarian-crisis-4-16-2021/5855415.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/tigray-Ethiopia-from-conflict-to-humanitarian-crisis-4-16-2021/5855415.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 16 Apr 2021 07:11:00 +0300</pubDate>
            <category>ቪድዮ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><comments>https://amharic.voanews.com/a/tigray-Ethiopia-from-conflict-to-humanitarian-crisis-4-16-2021/5855415.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/c2c7832d-029d-447e-b412-a40c1efa9391_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>