<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>Ethiopian Refugee Crisis - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/6287</link>
        <description>Ethiopian Refugee Crisis</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>Ethiopian Refugee Crisis - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/6287</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2020 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Tue, 29 Dec 2020 02:40:32 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/ztotqmeigtqm" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነሯ ስለ ትግራይ ስጋታቸውን ገለፁ</title>
            <description>የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ሚሸል ባከሌት፣ በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሰላማዊ ዜጎች በክፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደሚገኙ አስጠንቅቀዋል፡፡ በሰፊው እየተፈጸሙ መሆናቸው ከሚነገረው የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መካከልም፣ አንዳንዶቹ የጦር ወንጀሎች ሊሆኑ እንደሚችሉም ተናግረዋል፡፡</description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2020/12/24/ab486bec-55ec-4bdb-83ea-e7623f5f1a88_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/bachelet-tigray-ethiopia-12-24-2020/5712364.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 24 Dec 2020 22:35:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>አጭር ድምጽ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/6956e037-d79c-43a4-9963-2c1428fab89b_cx0_cy10_cw100_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነሯ ስለ ትግራይ ስጋታቸውን ገለፁ</title>
            <description>የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ሚሸል ባከሌት፣ በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሰላማዊ ዜጎች በከፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደሚገኙ አስጠንቅቀዋል፡፡ በሰፊው እየተፈጸሙ መሆናቸው ከሚነገረው የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መካከልም፣ አንዳንዶቹ የጦር ወንጀሎች ሊሆኑ እንደሚችሉም ተናግረዋል፡፡


በትግራይ እየተፈጸሙ ነው ፣ የተባሉትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ በብዙ አካባቢዎች፣ የመገናኛ መስመሮች የተቋረጡ በመሆናቸው፣ ለማረጋገጥና መጠናቸውንም ለመግለጽ አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ባክሌት፣ ገለልተኛ የሆኑ የሰብዓዊ መብት አጣሪ ቡድኖች፣ በክልሉ ተዘዋውረው፣ ሁኔታዎችን ለመገምገም እንዲችሉና፣ እንዲሁም፣ ሰላማዊ ዜጎችን ከጥቃት ለመከላከልና፣ ወንጀል የፈጸሙትንም ለፍርድ ለማቅረብ እንዲቻል አካባቢው፣ ያለምንም ክልከላ ክፍት እንዲደረግም ጠይቀዋል፡፡


የኮሚሽነሯ ቃል አቀባይ፣ ሊዝ ትሮሴል እንደሚሉት፣ በአካባቢው የዓለም አቀፉን የሰብአዊ መብትና ህጎችን የጣሱ ድርጊቶች፣ በሁሉም ወገኖች እየተፈጸሙ መሆኑን፣ የሰብአዊ መብት ድርጅቱ ቢሮ፣ በየጊዜው ሪፖርት እንደሚደርሰው ተናግረዋል፡፡ ስለሪፖርቶቹም ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ 


እነዚህ ሰላማዊ ዜጎች የሚዙባቸው አካባቢዎችን በከባድ መሳሪያዎች መደብደብን፣ ሰላማዊ ዜጎችን ሆን ብሎ ማጥቃትን፣ በዘፈቀደ የሚካሄዱ ግድያዎችና በስፋት የሚካሄዱ ዝርፊያዎችን ያጠቃልላሉ፡፡


የዓይን እማኞች እንደገለጹት በኤርትራ አዋሳኝ ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው የሁመራ ከተማ፣ ከኖቬምበር 9 እስከ 11 ባሉት ቀናት የከባድ መሳሪያ ድብደባ መፈጸሙን አስታውቀዋል፡፡ ከኤርትራ የተተኮሱ በርካታ የከባድ መሳሪያ ጥይቶች የመኖሪያ ቤትና ሆስፒታሎችን ስለሞታቸው በርካታ የከተማይቱን ነዋሪዎች አነጋግረናል፡፡


የኢትዮጵያ ወታደሮች እና የአማራ ታጣቂዎች ሚሊሻዎች፣ ሁመራን መቆጣጠራቸውን ትሮሴል ተናግረዋል፡፡ ሰላማዊ ዜጎችን መግደላቸውን፣ በሆስፒታል፣ ባንኮች የንግድ ድርጅቶች፣ ገበያዎችና የግል መኖሪያ ቤቶች ላይ፣ ዘረፋዎች ተፈጽመዋል የሚል ክስ መቅረቡንም ገልጸዋል፡፡


ትሮሴል በከተማ ውስጥ ተፈጽመዋል ብለው ከዘረዘሯቸው አስደንጋጭ አደጋዎች መካከል፣ እጅግ የከፋውና፣ ብዙ መቶዎች፣ በዋናነትም የአማራ ተወላጆች የተገደሉበትን፣ የኖቬምበር 9ን እልቂት በማንሳት የሚከተለውን ብለዋል፡፡


“ከፍተኛ ኮሚሽነሩ ቀደም ሲል አበክረው እንደተናገሩት፣ በአንድ ወገንም ይሁን የግጭቱ ተካፋይ በሆኑት ሁሉም ወገኖች ይሁን፣ በተፈጸመው ጥቃት፣ ሰላማዊ ዜጎች ሆኖ ተብለው ተገድለዋል፡፡ እነዚህ ግድያዎች ወደ ጦር ወንጀልነት ሊያድጉ ይችላሉ፡፡ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥና ፍትህን ለማስፈን ገለልተኛ፣ ነጻ፣ ግልጽና ጥልቅ የሆነ ምርምራ ማካሄድ ያስፈልጋል፡፡”


የኮሚሽነሯ ቃል አቀባይ ትሮሴል፣ የኤርትራ ወታደሮች፣ ትግራይ ውስጥ መታየታቸው፣ ተፈጽመዋል በተባሉት፣ የጥላቻ ጥቃቶች፣ ከዚያም ጋር በተያያዘው ፣ የዓለም አቀፍ ህግ ጥሰቶች ውስጥ መሳተፋቸውን አስመልክቶ፣ ገና በሚገባ ያልተረጋገጠ ቢሆንም፣ መረጃዎች ወደ ድርጅቱ ቢሮ መድረሳቸውን ተናግረዋል፡፡


ኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ፣ የኤርትራው ወታደሮች በግጭቱ ተሳታፊ መሆናቸውን አስተባብሏል፡፡


ግጭቱ ከመጀመሩ ሰባት ሳምንታት በፊት፣ 96 ሺ የሚሆኑ ኤርትራውያን ስደተኞች፣ በትግራይ በሚገኙት የስደተኞች ካምፕ ውስጥ ተጥልለው ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ ግን ፣ ብዙዎቹ ለደህንነታቸው በመስጋት፣ መጠለያ ካምፖቹን ትተው ሸሽተዋል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር፣ ፊሊፖ ግራንዲ እንደተናገሩት፣ በትግራይ የሚገኙ በርካታዎቹ ስደተኞች፣ የተገደሉ፣ የታፈኑ እና በግዴታ ተይዘው ወደ ኤርትራ የተመለሱ መሆኑን የሚገልጽ ሪፖርት፣ ከወኪሎቻቸው የደረሳቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡


በተጠቀሰው ጊዜ አካባቢም፣ ዩናይትድ ስቴትስ ፣የኤትርትራ ወታደሮች በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ መገኘታቸውን በመግልጽ ለቀው እንዲወጡ ጥሪ ማስተላለፏም ይታወቃል፡፡ (ዘገባው የቪኦኤ ዘጋቢ ሊሳ ሽላይን ነው፡፡)


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/bachelet-tigray-ethiopia-12-24-2020/5712222.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/bachelet-tigray-ethiopia-12-24-2020/5712222.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 24 Dec 2020 20:45:48 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/bachelet-tigray-ethiopia-12-24-2020/5712222.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/6956e037-d79c-43a4-9963-2c1428fab89b_cx0_cy8_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የተባበሩት መንግሥታት ለስደተኞችና ተፈናቃዮች የ455 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ተማጽኗል</title>
            <description>የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኮሚሽን፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ፣ ስደተኞችንና ተፈናቃዮችን፣ከአስከፊው የኮቪድ- 19 ወረርሽኝ ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ የ455 ሚሊዮን ዶላር እርዳታተማጽኗል፡፡


ሁሉም ሰው ለኮረና ቫይረስ ተጋላጭ ቢሆንም ስደተኞች፣ ተፈናቃዮችና፣ አገር አልባ ሰዎች ደግሞበከፍተኛ ደረጃ በቫይረሱ ለመያዝና ለሞት የበለጠ ተጋላጮች ናቸው፡፡  በመንግሥታቱ ድርጅት፣ወረርሽኙ ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ፣ በ13 አገሮች ላይ በተደረገ ክትትል፣ 74 ከመቶ የሚሆኑ ስደተኞችከመሰረታዊ ፍላጎቶቻቸው ግማሹን እንኳ ማሟላት የቻሉ አይደሉም፡፡ ይህ ሁኔታቸው ወረርሽኙከመከሰቱ በፊት ከነበረው 2019 ዓም በ21 ከመቶ ጨምሯል፡፡


ይህ በመሆኑም፣ ከ80 ከመቶ በላይ የሚሆኑት፣ ሕይወታቸውን ለማትረፍ ሲሉ፣ ንብረታችን ለመሸጥ፣የወሲብ አገልጋይ በመሆንና በህጻንነት ጉልበታቸው ወደ ሥራ በመሥራትና ለመበዝበዝ ተገደዋል።የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኤጀንሲ   ቃል አቀባይ፣ ባባር ባሎች እንደሚሉት፣ ከተማውስጥ ያሉ ስደተኞች፣ መሠረታዊ ፍጆታቸውን ለማሟላት የሚተማመኑት፣ የቀን ሥራ ሠርተውበሚያገኙት ገቢ ነው።ይሁን እንጂ፣ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ሳቢያ፣ ሁሉም ነገር የተዘጋጋ በመሆኑ፣ኑሯቸውና ሥራቸውም ተጎድቷል።


በወረርሽኙ የተነሳ፣ በተጣለው ገደብ፣ ብዙ ቦታዎችና መገበያያዎች በመዘጋታቸው ሁሉም ከአካባቢውጠፍተዋል፡፡ ስለዚህ፣ ተስፋ የቆረጡ ስደተኞች መሠረታዊ ፍጆታዎቻቸውን ለማሟላትና፣ ለኑሯቸውአስፈላጊ የሆኑ አገልግሎቶቹን ለመጠቀም  እንኳ እንዲችሉ በእጃቸው ጥሬ ገንዘብ ያስፈልጋቸዋል፡፡


ባሎች እንደሚሉት፣ ስደተኞቹ አክባቢያቸው የተጨናንቀ በመሆኑ፣ የአካላዊ ርቀታቸውን መጠበቅአልቻሉም፡፡ እንደ ውሃ፣ ሳሙና፣ እና ጤንነታቸውን የተጠበቀ ለማድረግ የሚረዱ ነገሮችን ሟሟላትምእጅግ አስፈላጊ ነገር መሆኑን ይናገራሉ፡፡ በዚሁ ሁኔታ ውስጥ፣ በሱዳን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንንምአንስተዋል።


“በሱዳን ያለው ገጽታ ብትመለከቱ፣ ከኢትዮጵያ በቅርቡ ወደ ሱዳን የመጡ ስደተኞች አሉ፡፡ ያ ትልቅፈተና ነው፡ በቅርብ ሳምንታት ውስጥ በቦታው የደረሱ ከ51ሺ በላይ ስደተኞች በድንበር አካባቢዎችተሰራጭተዋል፡፡ ስለዚህ እነሱም ሆኑ የሚያስተናግዳቸው ማኅበረሰብም ከኮቪድ 19 ወረርሽኝ የተጠበቁመሆናቸውን ማረጋገጥ ከባድ ፈተና ነው፡፡” ብለዋል።


የመንግሥታቱ ድጅርጅት እንደሚለው፣ በእጅ ያለው የገንዘብ እርዳታ እጅግ አስቸጋሪ በሆኑ ሁኔታዎችውስጥ ላሉ ስደተኖች እየዋለ ነው፡፡ እጅግ መሰረታዊ በሆኑ አስፈላጊ ነገሮች ላይ በማተኮር እንኳ የብዙሰዎችንም ህይወት ማሻሻል እንደሚቻል ያምናል፡፡ ከዚያም አልፎ፣ የሚገኘው ገንዘብ፣ የጾታ ጥቃቶችንለመከላከል፣ ሰዎችን ከብዝበዛ ለመታደግ፣ የአእምሮ ጤንነትና የስነልቦና ምክር አገልግሎቶችንለመስጠት እንደሚውል ዘርዝሯል፡፡


ትምህርትንም ቀዳሚ በማድረግ፣ ደህንነታቸው የተጠበቀ ትምህርት ቤቶች፣ እንደገና የሚከፈቱበትንመንገድም ለማመቻቸት እንደሚሠራ፣ ያን ማድረግ አስቸጋሪ በሆነበት ሁኔታ ውስጥም፣ ኢንተርኔትንበመጠቀም በርቀት ትምህርት ኢንቨስት እንደሚያደርግ አስታውቋል።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5711823.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5711823.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 24 Dec 2020 14:52:30 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5711823.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/A12C9FC5-1EC9-4947-A9EB-5EEF463FB9DD_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሱዳን ካምፖች ያሉ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን የሚያግዙት ስደተኞች</title>
            <description>በሱዳን የኢትዮጵያውያን ስደተኛ ልጆች የሆኑት &apos;የኢትዮጵያውያን ወጣቶች የስደተኞች ማኅበር&apos; በሃሻባት እና ኡም ራኩባ ካምፕ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ምግብ፣ ልብስ እና እንዲሁም ቁሳቁስ በማሰባሰብ ለመርዳት እየጣሩ ይገኛሉ ኤደን ገረመው ከቡድኑ ሰብሳቢ መሃከል አንዱ የሆነውን ተሾመ ኪሮስን አነጋገራለች፡፡</description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2020/12/23/500c0294-9eb8-4c78-be98-2606d8fea28c_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5711230.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 24 Dec 2020 02:48:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>ፖለቲካ</category><category>ጋቢና ቪኦኤ</category><category>አጭር ድምጽ</category><category>ጋቢና ቪኦኤ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/4AE3EF20-C4C7-4B00-9C02-2BAA1DC69815_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አማራ ክልል ለሚገኙ ከ250 ሺሕ በላይ ተፈናቃዮች በቂ ድጋፍ አለመድረሱን ክልሉ አስታወቀ</title>
            <description>ትግራይ ክልል ውስጥ በተካሄደው ወታደራዊ ዘመቻና ቤኒሻንጉል ጉምዝ ውስጥ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ለተፈናቀሉ 250 ሺህ ዜጎች እስካሁን በቂ ድጋፍ አለመድረሱን የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት አስታውቋል።


በሌላ በኩል በጦርነቱና በሌሎችም ጥቃቶች ለተፈናቀሉና አማራ ክልል ውስጥ ለሚገኙ ተጎጂዎች የአዲስ አበባ አስተዳደር የዕለት ደራሽ ድጋፍ ሰጥቷል።


(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5711079.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5711079.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 23 Dec 2020 23:29:50 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (አስቴር ምስጋናው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5711079.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/93889E70-E218-4CC0-8D04-F65902361C46_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ቀይ መስቀል የመጀመሪያውን የሕክምና ቁሳቁስ መቀሌ አደረሰ</title>
            <description>ዓለም አቀፍ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ወደ ከግጭቱ በኋላ ለመጀመሪያ ግዜ የሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶችየጫኑ ሰባት መኪኖች መቀሌ ከተማ ማድረስ ቻለ።


የቀይ መስቀል ኮሚቴ የኮሚኒኬሽን የሥራ ክፍል ሃላፊ አቶ ዘውዱ አያሌው ቀይ መስቀል ኮሚቴ ትግራይያደረሰውን ቁሳቁስ ለክልሉ ጤና ቢሮ፣ ለአይደር ሆስፒታል እና ለኢትዮጵያ ቀይ  ማኅበር መስቀልመድሃኒት ቤቶች ማድረሱን ገልጿል።


ከአቶ ዘውዱ አያሌው ጋር ያደረግነውን ቃለ ምልልስ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5710158.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5710158.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 23 Dec 2020 15:41:19 +0300</pubDate>
            <category>Ethiopian Refugee Crisis</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ጽዮን ግርማ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5710158.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/006F3D7F-CC1C-4F75-B668-64DE107F25BC_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በዋጃ ጥሙጋ የዕለት ደራሽ ምግብ ፈላጊዎች ቁጥር ብዙ ነው</title>
            <description>በአምበጣ መንጋ ክስተትና መንግሥት ሕግ ማስከበር ባለው ወታደራዊ ርምጃ በመቶ ሺሕዎች የሚገመቱ የዋጃ ጥሙጋ አከባቢ ኗሪዎች የዕለት ደራሽ የምግብ ርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው በአካባቢው የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ገለጸ፡፡


ጊዜያዊ አስተዳደሩ ካለው የተረጅ ቁጥር አንጻር ተደራሽ ማድረግ የተቻለው ከ45 ሺሕ የማይበልጡትን ነው ብሏል፡፡


የሰጡትን የሚቀበለው፤ የተቀበለውን አብዝቶ የሚሰጠው የራያ አላማጣ መሬት ዘንድሮ ምርታማነት ርቆታል ሲሉ የአካባቢው ኗሪዎች ይናገራሉ፡፡


(ከአላማጣ ከተማ የተጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)






 


 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5710009.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5710009.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 23 Dec 2020 10:09:40 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (መስፍን አራጌ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5710009.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/709D840E-C4E7-4947-817B-9D2460A862E0_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የትግራይ ክልል ተፈናቃዮችን ለመርዳት የ160 ሚሊዮን ተማፅኖ ቀርቧል</title>
            <description>ከሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል በግጭቱ ሳቢያ ከቀያቸው ለሸሹ ስደተኞች የሚያስፈልገውን አጣዳፊርዳታ ለማቅረብ የ.ተ.መ.ድ የስድተኞች ኮሚሽነር እና 30 የሰብዓዊ ረድዔት አጋሮቹ የ160 ሚሊዮን ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ተማጽነዋል።  


ገንዘቡ ለስደተኞቹ እስከመጪው የአውሮፓውያን 2021 ዓመተ ምህረት አጋማሽ የሚዘልቅ ርዳታ ለማቅረብየሚውል መሆኑን ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር አመልክቷል


“የተጠየቀው አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ ቀያቸውን እየለቀቁ ወደሌላ ሃገር የሚሰደዱ ሰዎች እንቅስቃሴከቀጠለ መደረግ ያለበትን ዝግጅት ለማጠናከርም ይውላል” ብሏል።


ባለፉት ስድስት ሳምንታት ድንበር አቋርጠው ሱዳን የገቡት ኢትዮጵያውያን ከ56 ሺሕ በላይ መሆናቸውንያመለከተው ድርጅቱ፤ በቅርብ ቀናት የሚገቡት ቁጥር ቀንሶ በቀን 500 የሚጠጉ ሰዎች ይገባሉ ብሏል።“በዚህ ደረጃ የገዘፈ የስደተኛ እንቅስቃሴ  ባልታየበት እጅግ የራቀ አካባቢ ለረድዒት ድርጅቶች ሥራ እጅግፈታኝ ሆኗል” ሲል የተ. መ.ድ የስደተኞች ኮሚሽነር አስረድቷል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5709997.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5709997.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 23 Dec 2020 09:06:02 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5709997.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/19E9E402-19DE-49E3-AD67-83263A620F06_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በማይካድራ በጅምላ ለተገደሉ መታሰቢያ መሰረት ድንጋይ ተቀመጠ</title>
            <description>በማይካድራ ከተማ ቁጥራቸው ከ600 እስከ 1000 ሺሕ እንደሚደርስ የተነገሩ በጅምላ የተገደሉ ነዋሪዎችንእየዘከረች መሆኗን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አስታወቀች:: 


በማይካድራ በጅምላ የተቀበሩ ሰዎች ፀሎተ ፍትሃት ተደርጎላቸው አስክሬናቸው ቤተክርስቲያ ውስጥበተዘጋጀ የመቃብር ሥፍራ እንዲያርፍ ተደርጓል። በከተማው መሃልም የመታሰብያ ሃውልት መሰረተ ድንጋይተቀምጦላቸዋል:: 


(ከስፍራው የተጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)






 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5709989.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5709989.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 23 Dec 2020 08:57:24 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ዮናታን ዘብዴዎስ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5709989.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/DD5870FF-3AB3-4C8E-8C58-92CC44FD9899_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አላማጣ ከስጋት አገግማ የወትሮ ገጽታዋን እየያየዘች ነው</title>
            <description>አላማጣ ከተማ ተቋርጠው የነበሩ መንግሥታዊና ሕዝባዊ አገልግሎቶች እንዲቀጥሉ መደረጋቸውን የከተማዋ ጊዜያዊ አስተዳደር ገለጸ፡፡</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5705264.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5705264.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 19 Dec 2020 00:51:16 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (መስፍን አራጌ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5705264.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/7635FCA2-167E-49C7-994D-5FBAE8163B32_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በማይካድራ በጅምላ የተቀበሩ ሰዎች ፀሎተ ፍትሃት ተደረገላቸው</title>
            <description>በማይካድራ በጅምላ የተቀበሩ ሰዎች ፀሎተ ፍትሃት ተደርጎላቸው አስክሬናቸው ቤተክርስቲያ ውስጥ እንዲያርፍ ተደረገ። ሰሞኑን ሰሜን ኢትዮጵያ የሚገኘው የሃዋሳው ዘጋቢያችን ዮናታን ዘብዲዮስ ዛሬ ውሎውን ማይካድራ አድርጎ ነበር። የሟቾች ፀሎተ ፍትሃት ሲደረግም ተከታትሏል።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5705243.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5705243.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 19 Dec 2020 00:23:27 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ዮናታን ዘብዴዎስ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5705243.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/22F01425-7248-4E15-995A-AF3FE4BF2521_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ሁኔታ በሱዳን</title>
            <description> 


 


በትግራይ ክልል ሃይል እና በመከላከያ ሰራዊት መካከል ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኃላ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች መጠጊያ ያደረጓት ሱዳንን ነው። ለመሆኑ ስደተኞቹ  በሱዳን ያሉበት ሁኔታ ምን ይመስላል?


ሀብታሙ ስዩም ሱዳን ውስጥ የምትገኘውን  የቪኦኤ የስደተኞች ጉዳይ ዘጋቢ ሄይዘር መርዶክን በስልክ አግኝቶ ጠይቋታል። በመቀጠል ይሰማል።


 


 




 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5705098.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5705098.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 18 Dec 2020 22:27:34 +0300</pubDate>
            <category>ኢትዮጵያ</category><category>ጋቢና ቪኦኤ</category><category>የዩናይትድ ስቴትስ ምርጫ - 2020</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ሀብታሙ ስዩም)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5705098.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/6B010082-1FBF-414B-837B-60C74793BC3D_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ደራሽ እርዳታ እየተሰጠ ካለበት የሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል የተጠናቀረ ዘገባ</title>
            <description>ደራሽ እርዳታ እየተሰጠ ያለበትን ጨምሮ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የተጓዘው አካባቢዎቹ ዘጋቢያችን የተመለከተው ከተከታዩ ዘገባ ያዳምጡ።</description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2020/12/17/62d1191f-9264-4656-bd6e-61643b9223bb_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5703797.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 18 Dec 2020 00:35:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>ሳምንታዊ  ዝግጅቶች</category><category>ፖለቲካ</category><category>አጭር ድምጽ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (መስፍን አራጌ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/6083F046-8651-46AB-BED5-707D231D4C7E_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በጎንደር ሕክምና እየተከታተሉ ከሚገኙ የኢትዮጵያ መከላከያ አባላት ጋር የተደረገ ቆይታ</title>
            <description>“የሕግ ማስከበር ዘመቻው ያስገኘው ውጤት በቶሎ እንድናገግም ከሠራዊቱ ጋር እንድንቀላቀል የሚያነቃቃ” ነው ሲሉ በትግራዩ ጦርነት የቆሰሉና በጎንደር ዩኒቨርስቲ ሆስፒታል ሕክምና እየተከታተሉ የሚገኙ የኢትዮጵያ መከላከያ አባላት ተናግረዋል::</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5703746.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5703746.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 17 Dec 2020 23:43:53 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ዮናታን ዘብዴዎስ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5703746.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/D874ABF2-4948-4A5E-BC51-8C71D080D786_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ትናንሾቹ የጦርነት ሰለባዎች</title>
            <description>በትግራይ ክልል በተነሳው ጦርነት ምክንያት ወደ ሱዳን ከተሰደዱ መሃከል ነፍሰጡሮች እና አራሶች ሲኖሩ ባዛው በሱዳን ካምፕ ውስጥም ልጆቻቸውን የተገላገሉ እናቶች አሉ፡፡ የካምፑ አስተዳዳሪዎች ስደተኞቹን ወደ ሌላ ጣቢያ የማዘዋወር ዕቅድ ቢኖራቸውም እናቶቹ ግን፤ ገና ከተወለዱ የቀናት እድሜ ያላቸውን ሕጻናት ይዞ ወደሌላ ካምፕ መሄዱ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ከቷቸዋል፡፡ የአሜሪካ ድምጿ ሄዘር ሙርዶክ ከሱዳን ሃምዳይት የላከችውን ዘገባ ኤደን ገረመው እንደሚከተለው አጠናቅራዋለች፡፡</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5702421.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5702421.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 17 Dec 2020 02:05:00 +0300</pubDate>
            <category>የቪዲዮ ዘገባ</category><category>ቪድዮ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ኤደን ገረመው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5702421.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9663375c-fba8-4d3d-a92e-84fb758c08eb_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዩናይትድ ስቴትስ እንደራሴዎች ም/ቤት የውጭ ግንኙነቶች ንኡስ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ጉዳይ</title>
            <description>ሁለት የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ኮሚቴ አመራር አባላት በኢትዮጵያ በትግራይ ክልል ያለው ወታደራዊ ግጭት በሰላም እንዲበቃ ያበረታቱበትን አቋም ያንጽባረቁበትን ረቂቅ ይፋ አደረጉ።


በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የሲቪሎችን ደህንነት፤ ዲሞክራሲና የሰብዓዊ ጉዳዮች የሚመለከተው የውጭ ግንኙነቶች ንዑስ ኮሚቴ ሊቀ መንበር የአይዳሆ ክፍለ ግዛቱ የሪብሊካን እንደራሴ ጂም ሪሽ እና የሜሪላንዱ የዲሞክራት ፓርቲ እንደራሴ የኮሚቴው ምክትል ሊቀመንበር ቤን ካርዲን በትላንትናው ዕለት በጋራ ባወጡት በዚህ አቅቋማቸው ሁሉም ዓይነት ግጭቶች እንዲቆሙ፤ ለኢትዮጵያውያን የሰብዓዊ መብት ጥበቃ እንዲያደርጉ እና ሰላማዊ መፍትሄ እንዲያፈላልጉ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።


በትግራይ ያለው ግጭት የከፋ ሰብዓዊ ሁኔታ እና በታሪካዊው የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ሽግግር ላይ ቀጠኛ አደጋ ይደቅናል” ያሉት ሪች “የሁለቱ ፓርቲዎች በጋራ ያወጡት ይህ አቋም በፕሬዝዳንት አብይ አህመድ የሚመራው የኢትዮጵያ መንግስት እና የትግራይ ሕዝብ ነታ አውጭ ግንባር በልዩነቶቻቸው ዙሪያ እንዲነጋገሩ ለግጭቶቹ ሰላማዊ እና ዘለቂ መቋጫዎችን እንዲያበጁ ያበረታታል ብለዋል። የተረጋጋችና ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ለሠፊው የአህጉሩ አካባቢዎች ወሳኝ መሆኗን ዩናይትድ ስቴትስ ኢትዮጵያ የያዘችውን የዲሞክራሲ ኝባታ ጥረት በመተማመን መንፈስ መርዳቷን ትቀጥላለች።” ሲሉ አጽንዖት ሰጥተው ተናገረዋል.።


“በትግራይ እየተካሄደ ያለው ግጭት በሺዎች የተቆጠሩ ሰዎችን ህይወት አጥፍቷል። እጅግ የገነነ መጠን ያለው ሰብዓዊ ቀውስ በመፍጠር የኢትዮጵያን መረጋጋት ዘለቄታ ብቻ ሳይሆን የመላውን የአህጉሩን አካባቢም ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው።” ያሉት ደግሞ ካርዲን ናቸው።


“ለኢትዮጵያውያን እና በዩናይትድ ስቴትስ የእንደራሴዎች ምክር ውስት በታላቅ ኩራት የምወክላቸው የሜሪላንድ ክፍለ ግዛት ነዋሪ የሆኑ ቤተሰቦቻቸው ብዙዎች ሲባል ግጭቱ መቆም አለበት። በግጭቱ ያሉ ሁሉም ወገኖች በመተባበር እርቅ ለመፍጠር - ፍትህ እና ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥ በሚያስችሉ ሥራዎች ላይ ትኩረት ማድረግ አለባቸው።” ብለዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/senate-resolution-12-10-2020/5694889.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/senate-resolution-12-10-2020/5694889.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 10 Dec 2020 23:50:10 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/senate-resolution-12-10-2020/5694889.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/189F468E-5016-40FA-A3B8-33BD1DDF3B9C_cx0_cy8_cw83_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ግጭቱን ሸሽተው ወደ ሱዳን የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ሁኔታ</title>
            <description>ከትግራይ ክልል በህወሓት እና በፌዴራል መንግሥት መካከል የተፈጠረውን ግጭት ሸሽተው ወደ ሱዳን የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን አብዛኞቹ አሁንም ድረስ ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንደተለያዩ እና ያሉበትን ሁኔታ እንደማያውቁ እየተናገሩ ይገኛሉ፡፡  የአሜሪካ ድምጿ ሄዘር ሙርዶክ በምስራቃዊ ሱዳን ኡም ራኩባ ካምፕ በመግኘት የስደተኞችን ሁኔታ ቃኝታለች፡፡</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/who-killed-those-pople-ethiopian-children-ask-freeing-brutual-conflict-12-10-2020/5694844.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/who-killed-those-pople-ethiopian-children-ask-freeing-brutual-conflict-12-10-2020/5694844.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 10 Dec 2020 23:21:00 +0300</pubDate>
            <category>ቪድዮ</category><category>የቪዲዮ ዘገባ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/who-killed-those-pople-ethiopian-children-ask-freeing-brutual-conflict-12-10-2020/5694844.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/4c859a42-dbaa-43e4-baf6-3391610538a0_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ትግራይ ክልል ሰብዓዊ እርዳታ ለማድረስ እንዲቻል ተመድ በድጋሚ ጠየቀ</title>
            <description>ትግራይ ክልል ውስጥ ለሲቪሎች ሰብዓዊ እርዳታ ማድረስ እንዲቻል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በድጋሚ መጠየቁ ተዘግቧል። 

ከአንድ ወር በላይ በዘለቀው ውጊያ ምክንያት በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ በግጭት አካባቢዎች የሚኖሩ ሰዎች የለት ደራሽ እርዳታ ፈላጊ መሆናቸውም ተገልጿል።</description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2020/12/08/03b90cda-2a3c-4ad4-8399-af8e96011a46_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/unhcr-ethiopia-12-8-2020/5692023.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 08 Dec 2020 23:33:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>አጭር ድምጽ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9a6e108a-0b5e-4fc1-b34f-84aa27d1e9f0_cx0_cy2_cw100_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ትግራይ ክልል ሰብዓዊ እርዳታ ለማድረስ እንዲቻል ተመድ በድጋሚ ጠየቀ</title>
            <description>ትግራይ ክልል ውስጥ ለሲቪሎች ሰብዓዊ እርዳታ ማድረስ እንዲቻል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በድጋሚ መጠየቁ ተዘግቧል። 


ከአንድ ወር በላይ በዘለቀው ውጊያ ምክንያት በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ በግጭት አካባቢዎች የሚኖሩ ሰዎች የለት ደራሽ እርዳታ ፈላጊ መሆናቸውም ተገልጿል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/umhcr-ethiopia-12-8-2020/5692024.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/umhcr-ethiopia-12-8-2020/5692024.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 08 Dec 2020 23:22:47 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ቆንጂት ታየ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/umhcr-ethiopia-12-8-2020/5692024.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9a6e108a-0b5e-4fc1-b34f-84aa27d1e9f0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አፍሪካ ነክ ርዕሶች</title>
            <description>የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አገልግሎቶች ትግራይ ውስጥ በሚካሄደው ውጊያ ምክንያት እየተሰቃዩ ያሉትን በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመርዳት እንዳልቻሉ ገልፀዋል።</description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2020/12/07/fc070834-0462-4a1e-bebd-dec65c529f64_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/unhcr-ready-to-provide-aid-in-tigray-as-soon-as-access-restored-12-7-2020/5690608.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 07 Dec 2020 23:23:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>አጭር ድምጽ</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/d3118c9b-9e86-47a5-95fa-94aceefd1a3d_cx0_cy6_cw100_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>