<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>ዜና - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/3167</link>
        <description>📜 ቪኦኤ-አማርኛ ስለ ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ አፍሪካ፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ዓለም አቀፍ በዲጂታል፣ በራዲዮና በቴሌቪዥን ዜናና ዘገባዎችን ለአድማጭና ለተመልካች ያቀርባል።  </description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>ዜና - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/3167</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Wed, 08 Apr 2026 19:11:23 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/ztbgtl-vomx-tpekvbv" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>የባለ ሥልጣናት መፈታት ለደቡብ ሱዳን ውጥረት መርገብ ቁልፍ ጉዳይ ነው ተባለ</title>
            <description>የደቡብ ሱዳን መንግሥት በሀገሪቱ የተፈጠረውን ውጥረት ተከትሎ የታሰሩ ባለሥልጣናትን እንዲፈታ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አባል ሀገራት መሪዎች ጥሪ አቅርበዋል።
የኢጋድ አባል ሀገራት ይኼንኑ የደቡብ ሱዳን ግጭት አስመልክተው ረቡዕ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም በበይነ መረብ ባደረጉት ስብሰባ የደቡብ ሱዳን መሪዎች ውጥረቱን ለማርገብ ውይይት እንዲጀምሩም ጠይቀዋል።
በደቡብ ሱዳን የጁባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር የኾኑት ፕሮፌሰር መልሃ ራውት ውጥረቱ የባለሥልጣናቱ መፈታት ውጥረቱን ለመርገብ መወሰድ ካለባቸው ቁልፍ ርምጃዎች አንዱ መኾኑን ገልጸዋል።
በአገሪቱ የቀጠለው የፀጥታ ችግር ዋነኛ ምክንያት ግን እ.አ.አ. በ2018 የተፈረመው የሰላም ስምምነት አተገባበር መጓተት መኾኑን ጠቅሰዋል።


</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/south-sudan-call-for-de-escalation/8011031.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/south-sudan-call-for-de-escalation/8011031.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 22:43:34 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/334741c0-bd9e-4b26-099c-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአፍሪካ የኅይል አቅርቦት ላይ ያተኮረውና በዋሽንግተን ዲሲ የተካሔደው ጉባኤ</title>
            <description>የአሜሪካ መንግሥት ባለሥልጣናት፣ የአፍሪካ ምኒስትሮች፣ ኢንቨስተሮች፣ የግል ገንዘብ አበዳሪዎች፣ እንዲሁም የአገልግሎትና የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች ዓመታዊ ለሆነውና በአፍሪካ የኅይል አቅርቦት ላይ በሚያተኩረው ጉባኤ ላይ ባለፈው ሳምንት በዋሽንግተን ዲሲ ተገናኝተው ነበር።
“መፃኢው የአሜሪካ እና የአፍሪካ የኅይል ትብብር” በተሰኘ መሪ ቃል በተካሄደው ጉባኤ፣ በአዲሱ የትረምፕ አስተዳደር የአሜሪካ መንግሥትም ሆነ የግል ኩባንያዎች የአፍሪካን የኤሌክትሪክ ኅይል ልማት፣ መሠረተ ልማት እንዲሁም የማዕድን ሃብትን በተመለከተ ያላቸውን ተሳትፎ እንደገና ለማዋቀር፣ የአሜሪካ ባለሥልጣናትና የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች ተወካዮች መክረዋል። 
የቪኦኤው አንተኒ ላብሩቶ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/labruto-us-africa-energy/8011019.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/labruto-us-africa-energy/8011019.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 22:40:33 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/f6e4fa2b-1590-4be5-09b6-08dd5c8b1668_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት በዶ.ር ደብረ ጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን ወቀሰ</title>
            <description>የኢትዮጵያ መግሥት በዶ.ር ደብረ ጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን የፕሪቶሪያውን ስምምነት ጥሷል ማለቱን የሀገር ውስጥ ብዙኅን መገናኛ ዘገቡ።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት፣ በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ አዲስ አበባ ለሚገኙ ዲፕሎማቶች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በማብራሪያቸው፣ ለፕሪቶሪያው ስምምነት መተግበር የዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ድጋፍ መጠየቃቸውን የመንግሥት ብዙኅን መገናኛዎቹ ዘግበዋል፡፡
በዶ/ር ደብረ ጽዮን የሚመራው ቡድን ስምምነቱን ጥሷል መባሉን ማስተባበሉን በማስተባበል፣ በአንጻሩ ስምምነቱ የተጣሰው በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ ቡድን ነው ሲል በተደጋጋሚ ምላሽ መስጠቱ ይታወቃል፡፡ በሌላ በኩል የአፍሪካ ኅብረት፣ በክልሉ ባለው ውጥረት ተሳታፊ የሆኑ አካላት ራሳቸውን እንዲያቅቡና ችግሩ በውይይት እንዲፈታ ጠይቋል፡፡
በህወሓት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/tigray-tension-update/8011028.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/tigray-tension-update/8011028.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 21:59:39 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0cc21c8a-e1d4-4e12-b76c-5691b2b9e8b7_cx0_cy5_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተመድ  የሶሪያ ግጭት እንዲቆም ጥሪ አቀረበ</title>
            <description>የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሶሪያ ልዩ መልዕክተኛ፣ ከፕሬዝደንት ባሽር አል አሳድ ሥልጣን መወገድ ተከትሎ  ባለፉት ሦስት ወራት ዐዲስ በተቀሰቀሰው ግጭት እየታመሰች ባለችው ሀገር ሁከቱ እንዲቆም ተማጸኑ፡፡ የሰላማዊ ዜጎች ደኅንነት እንዲጠበቅም  ጥሪ አቀረቡ፡፡
የመንግሥታቱ ድርጅት ልዩ መልዕክተኛ ጌር ፔደርሰን ጥሪያቸውን ያቀረቡት፣  የዲሞክራሲ ደጋፊዎች ሀገሪቱን ለዐስርት ዓመታት ወደ ዘለቀው የርስ በርስ ጦርነት ያመራው ጸረ  አሳድ ተቃውሞ የተጀመረበት 14ኛው ዓመት መታሰቢያ በሆነው በዛሬው ዕለት ነው፡፡
“የለውጥ ጥያቄ ጭካኔ የተሞላበት ከፍተኛ ብጥብጥ ገጥሞታል፣ በዘመናችን እጅግ አሰቃቂ ወደ ኾነ  ግጭት አምርቷል” ያሉት ፔደርሰን “ግጭቱ ጥልቅ  የሆነውን አስከፊውን የሰው ልጅ ጭካኔ አጋልጧል።” ብለዋል፡፡
“የሚወዷቸውን በሞት ያጡ ቤተሰቦች ሐዘን ላይ ናቸው፡፡...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un---syria/8010894.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un---syria/8010894.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 20:17:30 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/c5473208-e41e-4ba1-0fa7-08dd5c8d307c_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሚሳይል መስሪያ ግብአት በመጫን የተጠረጠረችው ሁለተኛ የኢራን መርከብ ከቻይና ተነሳች</title>
            <description>ከቻይና የሚሳይል ነዳጅ መስሪያ ቁልፍ ግብአቶችን ጭናለች ተብላ በምዕራባዊያን የዜና ዘገባዎች  የተጠረጠረችው ሁለተኛዋ የኢራን  መርከብ ወደ ኢራን እያመራች መሆኑን የቪኦኤ ልዩ የትንታኔ ዘገባ አመልክቷል፡፡
የመርከብ እንቅስቃሴ ክትትል ድረ-ገጾች እንደሚያሳዩት የኢራን ባንዲራ የሚያውለበልበው ጃይራን የተባለው የጭነት መርከብ፣ ከቻይና ይነሳል ተብሎ ከተጠበቀበት ጊዜ ከአንድ ወር በኋላ ዘግይቶ ባለፈው ሰኞ መነሳቱ ተጠቅሷል፡፡
በጥር እና በየካቲት  ዘ ፋይናንሺያል ታይምስ፣ ዘ ዎል ስትሪት ጆርናል እና ሲ ኤን ኤን ባቀረቧቸው ዘገባዎች፣ ቴህራን  በሚሳይል ነዳጅ ውስጥ ጥቅም ላይ የሚውለውን 1,000 ሜትሪክ ቶን ኬሚካል (ሶዲየም ፐርክሎሬት) ለመጫን ከምትጠቀምባቸው ሁለት መርከቦች መካከል ጃይራን አንዱ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡
ሦስቱ የዜና ማሰራጫዎች ስማቸው ያልተጠቀሱ የምዕራባውያን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/iran-china-missile-scheme-/8010868.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/iran-china-missile-scheme-/8010868.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 19:50:09 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/73570913-c12b-459d-b0a3-828c76588f8a_cx0_cy18_cw0_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቆዳ ላይ ቀላል እብጠት መሰል ነገሮች እና የቆዳ ቀለምን የሚለውጡ ምልክቶች ለጤና ያሳስቡ ይኾን?</title>
            <description>በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የቆዳ ቀለምን የሚለውጡ ፣በእንግሊዝኛው አጠራር ‘ሞሎች’ በአንዳንድ ባህሎች ዘንድ እንደ ውበት ምልክት ይታያሉ። በተለይ የጥቁር ዝርያ ባላቸው ሕዝቦች ውስጥ፣ በስፋት የሚታዩና የተለመዱ ናቸው።
በአንጻሩ፣ ለጤና መታወክ ይዳርጉ ይኾን? በሚል ለጭንቀት የሚጋለጡ ወገኖች የሚሰሟቸውን ስጋቶች የሚያነሣው ጁማ ማጃንጋ፣ ለእነዚኽ እና ተያያዥ ጥያቄዎች ምላሽ ፍለጋ፣ ከናይሮቢ ኬንያ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/kenya-moles-and-skin-tags-tv-headline-skin-tags-and-moles-/8010760.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/kenya-moles-and-skin-tags-tv-headline-skin-tags-and-moles-/8010760.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 18:12:12 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/6b63bcf5-b100-4ef6-0fa4-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አይኤምኤፍ እና ኢትዮጵያ በዋጋ ግሽበት ትንበያ ተለያዩ</title>
            <description>. ትንበያዎቹ &quot;የተለያዩ ብቻ ሳይኾኑ ከእውነታውም የራቁ ናቸው&quot; - ባለሞያ
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ)፣ በቅርቡ ስለ ኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ያወጣው ትንበያ፣ እ.ኤ.አ በ2025፣ 25 ከመቶ መድረሱን ይገልጻል፡፡ የዋጋ ንረቱ አኹን ካለበት ሁለት አኀዝ ወደ ነጠላ አኀዝ ለመውረድ እስከ 2028 ሊቆይ እንደሚችልም አይኤምኤፍ ተንብይዋል፡፡
በአንጻሩ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የዋጋ ግሽበቱ እየወረደ መምጣቱንና አኹን ከ15 እስከ 16 በመቶ ዝቅ ማለቱን ይናገራል፡፡
በለንደን የሚገኙት የፋይናንስ እና የምጣኔ ሀብት ባለሞያ ዶር. አብዱልመናን መሐመድ ሃምዛ ግን፣ የአይኤምኤፍም ኾነ የኢትዮጵያ መንግሥት ቁጥሮች፣ &quot;የተለያዩ ብቻ ሳይኾኑ ከእውነታው የራቁ ናቸው፤&quot; ይላሉ፡፡
ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ አጭር ቆይታ ያደረጉት ዶር. አቡዱልመናን፣ በአይኤምኤፍ እና በኢትዮጵያ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/imf-ethiopia-s-inflation/8010710.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/imf-ethiopia-s-inflation/8010710.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 18:06:32 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5ca8d0af-a26a-49ff-0900-08dd5c8b1668_cx0_cy12_cw0_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያውያት ሴቶች ጥያቄ ምንድን ነው? - የአድማጭ ተመልካቾች አስተያየት</title>
            <description>መጋቢት፥ የዓለም አቀፍ ሴቶች ወር ነው። ሴቶች ትምህርትንና ሥራን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች እኩል ዕድል እንዲያገኙ ለማብቃት በመላ ዓለም የሚደረጉ ጥረቶች፦ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በጦርነት እና በሌሎችም ሰው ሠራሽ ምክንያቶች መጓተታቸውን፣ በሴቶች ላይ አተኩረው የሚሠሩ ተቋማት ያወጧቸው ሪፖርቶች ያሳያሉ። 
ዘንድሮም፣ ወርኃ መጋቢት(ማርች 8)፥ “ትግበራን ማፋጠን” በሚል መሪ ቃል በመላው ዓለም እየታሰበ ይገኛል። 
በዐዲስ አበባ የአሜሪካ ድምፅ ዘጋቢ ኬኔዲ አባተ፣ በርእሰ መዲናዪቱ ጎዳናዎች ላይ ተዘዋውሮ፤ ለመኾኑ የኢትዮጵያውያት ሴቶች ጥያቄ ምንድን ነው? የሴቶች እኩልነት እንዲሰፍን ምን ቢደረግ ይበጃል? በማለት ጠይቆ ያገኘውን ምላሽ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/women-day-voxpop/8010711.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/women-day-voxpop/8010711.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 17:29:27 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/196b6129-1211-4881-3514-08dd5c897904_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>&quot;በትግራይ መፈንቅለ መንግሥት እየተፈጸመ ነው&quot; ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ተናገሩ</title>
            <description>በትግራይ ክልል፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ቢሮዎች በየደረጃው በመስበር እና ማኅተሞችን በመንጠቅ መንግሥትን የማውረድ ሥራ እየተሠራ ነው፤ ሲሉ ፕሬዘደንቱ አቶ ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል።
በዐዲስ አበባ የሚገኙት አቶ ጌታቸው፣ ዛሬ ኀሙስ፣ መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም. ረፋድ፣ በሸራተን ዐዲስ ሆቴል ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ አኹን በክልሉ ያለው ኹኔታ፣ &quot;የፕሪቶርያውን ስምምነት የሚጥስና ከፍተኛ ግጭት የሚፈጥር ስለኾነ፣ የፌደራል መንግሥቱ ይህን የሚያስቆም ርምጃ መውሰድ አለበት፤” ብለዋል።
“በምክር ቤት ወይም በካቢኔ ደረጃ ተሰብስበን የፌዴራሉ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ ያቀረብነው ጥያቄ የለም፤” ያሉት አቶ ጌታቸው፣ በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት መሠረት፣ የፌደራል መንግሥቱ ከህወሓት ጋራ ያቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር የመታደግ ሓላፊነት እንዳለበት አመልክተዋል።
ይህ ማለት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/getachew-s-presser-amanuels-reaction-/8010001.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/getachew-s-presser-amanuels-reaction-/8010001.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:53:52 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a0b29bb2-c45e-4a4e-082e-08dd5c8b1668_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር እንዲቆይ ፍርድ ቤት ፈቀደ</title>
            <description>ባለፈው ሰኞ ሌሊት፣ ከምትኖርበት ሕንፃ አምስተኛ ፎቅ ላይ ቁልቁል ወድቃ ሕይወቷ ካለፈው፣ ሞዴል እና የማስታወቂያ ባለሞያ ቀነኒ አዱኛ ሞት ጋራ በተያያዘ ተጠርጥሮ በቁጥጥር ሥር የሚገኘው እጮኛዋ አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ፣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር ቆይቶ ምርመራ እንዲቀጥል ፍርድ ቤት አዘዘ።
የዐዲስ አበባ ፖሊስ፣ ከቀነኒ ሞት ጋራ በዋና ወንጀል አድራጊነት የጠረጠረው አንዱዓለምን እንደኾነ በመግለጽ፣ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቆ የነበረ ሲኾን፣ ከጠበቃው ጋራ ፍርድ ቤት የቀረበው አንዱዓለም ደግሞ፣ የቀነኒ ሕይወት ያለፈው በአደጋ እንደኾነ በመግለጽ ከእስር እንዲፈታ አመልክቶ ነበር።
ሟች ቀነኒ አዱኛ ዋቆ፣ ሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ከሌሊቱ 10 ሰዓት ገደማ፣ አምስተኛ ወለል ላይ ከሚገኘው የቤቷ የማብሰያ ክፍል ቨረንዳ በኩል፣ ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/andualem-gosa-court-/8009809.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/andualem-gosa-court-/8009809.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:29:03 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0c9fc9b2-79e6-4c5e-0eca-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሩሲያ የተቆጣጠረቻቸውን የዩክሬን ግዛቶች እንደያዘች መቀጠል ትሻለች</title>
            <description>ሩሲያ በዩክሬን የምታካሒደውን ጦርነት ለማስቆም፣ አሜሪካ የምታደርገው ጥረት በክሬምሊን ላይ ጫናን ፈጥሯል። ይኹንና ሞስኮ አሁንም በቀጠለችው ጥቃት ተጨማሪ የዩክሬን ስፍራዎችን ተቆጣጥራለች፡፡
በሩሲያ የሚገኙ አንዳንድ ባለሥልጣናት ደግሞ፣ በድርድሩ ሩሲያ ምንም ነገር አሳልፋ መስጠትን እንደማትሻ በመናገር ላይ ናቸው።
የቪኦኤው ጄፍ ከስተር የላከውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/russia-ukraine-concessions/8009965.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/russia-ukraine-concessions/8009965.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:21:08 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/fce71d0f-fae4-482a-0ed0-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሦስት አባላቱ መታሰራቸውን አስታወቀ</title>
            <description>የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት የተደረገውን የሕገ መንግሥት ማሻሻያ የተቃወሙትን አቶ ዮሐንስ ተሰማን ጨምሮ ሦስት አባላቱ እንደታሰሩበት አስታወቀ፡፡
የፓርቲው የውጭ እና ዓለም አቀፍ ዘርፍ ሓላፊ ዶር. መብራቱ ዓለሙ፣ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፣ የሕገ መንግሥት ማሻሻያውን በመቃወማቸው ታስረዋል የተባሉት አቶ ዮሐንስ ተሰማ፣ የክልሉ ምክር ቤት አባል እንደኾኑ ጠቅሰው፣ ያለመከሰስ መብታቸው ግን እንዳልተነሳ ገልጸዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ፣ ከክልላዊ መንግሥቱ አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/opposition-member-arrest-/8009806.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/opposition-member-arrest-/8009806.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:12:15 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ገ/ሚካኤል ገ/መድህን)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/99f407d2-515a-4873-0e9e-08dd5c8d307c_cx0_cy12_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተዘግቶ የቆየው የመቐለ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት በዶር. ደብረ ጽዮን ቡድን ቁጥጥር ሥር ዋለ</title>
            <description>      &quot;የመፈንቅለ መንግሥት ሒደት ቅጥያ ነው&quot; - የጊዜያዊ አስተዳደሩ ሹም
ከህወሓት አመራሮች ውዝግብ ጋራ በተያያዘ ላለፉት መቶ ቀናት በዝግ የቆየው የመቐለ ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት፣ ዛሬ ኀሙስ፣ በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል በሚመራው ቡድን ቁጥጥር ሥር ውሏል።
በጊዜያዊ አስተዳደሩ የከተማዋ ከንቲባ እንዲኾኑ የተሾሙት አቶ ብርሃነ ገብረ ኢየሱስ፣ &quot;ጽንፈኛ&quot; ሲሉ የጠሩት ቡድን በወታደራዊ አመራሮች ድጋፍ ጽሕፈት ቤቱን እንደተቆጣጠረ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል፤ &quot;የመፈንቅለ መንግሥት ሒደት ቅጥያ ነው፤&quot; ሲሉም ድርጊቱን ኮንነዋል።
በዶር. ደብረ ጽዮን ሊቀ መንበርነት በሚመራው የህወሓት ቡድን የመቐለ ከተማ ከንቲባ እንዲኾኑ ታጭተው በከተማዋ ምክር ቤት የተሾሙት ዶክተር ረዳኢ በርሀ በበኩላቸው፣ &quot;ወደ ጽሕፈት ቤቱ የገባነው በሰላማዊ መንገድ ነው፤&quot; ሲሉ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/mekelle-mayor-take-over-/8009904.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/mekelle-mayor-take-over-/8009904.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 22:25:45 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/846c6708-ef34-447d-345c-08dd5c897904_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኤኮዋስ የፀረ-ሽብር ጦሩ በተጠንቀቅ እንዲቆም አደረገ</title>
            <description>የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ &quot;ኤኮዋስ&quot; የቀጠናው የጦር ኃይል በተጠንቀቅ እንዲጠባበቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል። የጸጥታ ተንታኞች ርምጃውን ያደነቁ ቢሆንም፣ የተቋሙ ሦስት አባል ሀገራት በቅርቡ መውጣታቸው ውጤታማነቱን አጠራጣሪ እንደሚያደርገው ተገልጿል።
የናይጄሪያ መከላከያ ሚኒስትር ሞሃመድ ባዳሩ አቡባካር የኤኮዋስ የጦር ኃይል በተጠንቀቅ ላይ እንደሚሆን ያስታወቁት፣ ትላንት ማክሰኞ በተካሄደው የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት ጥምረት የሆነው ኤኮዋስ 43ኛ መደበኛ የፀጥታ ስብሰባ ወቅት ነው።
5 ሺሕ ወታደሮች እንደሚኖሩት የሚጠበቀው የጦር ኃይል፣ በቀጠናው የሚካሄዱትን ሽብርተኝነት እና ድንበር ዘለል ወንጀሎች ለመከላከል የሚደረግ ቀጠናዊ የፀጥታ እንቅስቃሴ አካል ነው።
አቡበከር በንግግራቸው &quot;ይህ  ኃይል በተጠንቀቅ እንዲቆም ሆኖ ሥራ መጀመሩ፣ የሽብርተኝነትን መስፋፋት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ecowas-regional-bloc-activates-counterterror-force/8009724.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ecowas-regional-bloc-activates-counterterror-force/8009724.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 20:42:16 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9a78e2c0-aa66-46a3-95bd-53dfc7c9bc06_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ትረምፕ ከአውሮፓ በሚገቡ የአልኮል መጠጦች ላይ ከበድ ያለ ታሪፍ እንደሚጥሉ አስታወቁ</title>
            <description>የአውሮፓ ኅብረት ከአሜሪካ በሚገባው ዊስኪ ላይ የ50 በመቶ ታሪፍ መጣሉን ተከትሎ፣ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ከአውሮፓ በሚገባው የወይን ጠጅ፣ ሻምፓኝና ሌሎች የአልኮል መጠጦች ላይ የ200 በመቶ ታሪፍ እንደሚጭኑ አስጠንቅቀዋል።
የ27 ሃገራት ስብስብ የሆነውን የአውሮፓ ኅብረት &quot;በዓለም የከፋው ታክስና ታሪፍ ጣይ&quot; ሲሉ የገለጹት ትረምፕ፣ &quot;እ.አ.አ በ1993 ሲመሠረት ዓላማው &quot;ከአሜሪካ የኢኮኖሚ ጥቅም ለማግኘት ነው&quot; ብለዋል። 
ባለፈው አንድ ወር ከአሜሪካ ከፍተኛ የንግድ ሸሪኮች፣ ማለትም ከሜክሲኮ፣ ካናዳ፣ ቻይናና የአውሮፓ ኅብረት ጋራ የታሪፍ ውዝገብ ውስጥ የገቡት ትረምፕ፣ ታሪፉን መጣሉ አስፈላጊ የሆነው ሃገራቱ ወደ አሜሪካ የሚገባውን አደገኛ  ዕጽ እና መድሃኒት እንዲያስቆሙና እንዲሁም የሸቀጥ አምራቾች በውጪ ያላቸውን ፋብሪካ ዘግተው ወደ አሜሪካ እንዲመጡ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/trump-tariffs/8009704.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/trump-tariffs/8009704.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 20:34:24 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a1531c9d-c3db-422b-0e43-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት በዩክሬይን ለ30 ቀናት ተኩስ እንዲቆም የቀረበውን ሐሳብ ደገፉ</title>
            <description>ዩክሬይን ለ30 ቀናት ተኩስ እንዲቆም በቀረበው ሐሳብ እንደምትስማማ ትላንት ይፋ ማድረጓን የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት በደስታ ተቀበሉት፡፡ ቀድሞ የተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ሊቀ መንበር የነበሩት ሪፐብሊካኑ ማይክል መኮል &quot;ስምምነት ላይ መደረሱ በጣም አበረታቶኛል፡፡ አሁን ፕሬዚደንቱ የተያዘውን የስለላ መረጃ እና የጦር መሣሪያ ለመልቀቅ የወሰኑ ይመስለኛል፡፡ በጣም ትልቅ ክንዋኔ ነው&quot; ማለታቸው ተጠቅሷል፡፡
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ እና የዩክሬይን ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ በኋይት ሐውስ ኦቫል ኦፊስ የተካረረ ንግግር ማድረጋቸውን ተከትሎ ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬይን የምትሰጠውን የጦር መሣሪያ ርዳታ እና የስለላ መረጃዎች ማጋራቷን እንደምታቋርጥ ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቀች ይታወሳል። ኾኖም በቀናት የተገደበው የተኩስ ማቆም ስምምነት ይፋ ከተደረገ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-congress-ukraine/8009685.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-congress-ukraine/8009685.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 20:24:40 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/3471c82e-4c7f-46c9-89af-c96f71d45c8b_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከታቀደው በላይ የቆዩትን ጠፈርተኞች ለመተካት ሊላክ የነበረው የስፔስ ኤክስ ተልእኮ ዘገየ</title>
            <description>ጠፈር ላይ ከጊዜያቸው በላይ የቆዩ የ ዩናይትድ ስቴትስ የኤሮኖቲክስ እና ጠፈር ምርምር (ናሳ) ጠፈር ተመራማሪዎችን ለመተካት ወደ  ሊላክ የነበረው የስፔስ ኤክስ መንኮራኩር የሮኬት ማስወንጨፊያ እክል ስለገጠመው ወደ ጠፈር ጣቢያው የሚያደርገው በረራ ዘግይቷል፡፡
ቡች ዊልሞር እና ሱኒ ዊሊያምስ የተባሉት ጠፈርተኞች ከዘጠኝ  ወራት  ቆይታ በኋላ ወደ ምድር ከመመለሳቸው በፊት እነሱን የሚተካ የጠፈርተኞች ቡድን ከዓለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ መድረስ ይኖርበታል፡፡
ይሁን እንጂ ከኬኔዲ የጠፈር ማእከል ሊወነጨፍ ተዘጋጅቶ የነበረውን ፋልከን ሮኬት እክል ገጥሞታል፡፡
አሶስየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ሮኬቶቹን ደግፈው ከያዙት መሳሪያዎች መካከል አንዱን የሚቆጣጠረው የማስወንጨፊያ ክፍል (የማስነሻ ፓድ)  ችግር የገጠመው መኾኑን መሀንዲሶች በመናገራቸው ስፔስ ኤክስ (SpaceX) ተልዕኮውን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/https-www-voanews-com-a-launch-pad-problem-delays-spacex-flight-to-replace-nasa-s-stuck-astronauts-8009048-html/8009493.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/https-www-voanews-com-a-launch-pad-problem-delays-spacex-flight-to-replace-nasa-s-stuck-astronauts-8009048-html/8009493.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 18:18:13 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5ee089cb-5149-4b45-0757-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኩዌት ከአደገኛ ዕጽ ጋራ በተያያዘ የታሰሩ የቀድሞ ሠራዊት አባላት ጨምሮ አሜሪካዊ እስረኞችን ለቃለች</title>
            <description>ኩዌት ከአደገኛ ዕፅ ጋራ በተያያዘ ክስ ተመስርቶባቸው ለዓመታት በእስር ላይ የነበሩ የቀድሞ ሠራዊት አባላትና እና የወታደራዊ ተቋራጭ ሠራተኞችን ጨምሮ አሜሪካውያን እስረኞችን ለቃለች።
የአሜሪካ መንግሥት በውጭ ሀገር የታሰሩ አሜሪካውያንን አስለቅቆ ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ ባደረገው ጥረት የተፈቱት እስረኞች ወደ ኒውዮርክ ተወስደዋል፡፡
እስረኞቹ የተለቀቁት በቅርቡ ዋናው የትረምፕ አስተዳደር የታጋቾች ጉዳይ መጓዛቸውን ተከትሎ መኾኑም ተመልክቷል፡፡
በአሜሪካዊያን ታጋቾች እና እስረኞች ጉዳይ የሚሰሩት አማካሪው ጆናታን ፍራንክ እስር ላይ ከነበሩ ስድስት እስረኞች ጋራ በመኾን ለኩዌት መንግሥት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን “ደንበኞቼና ቤተሰቦቻቸው የኩዌት መንግሥት ላሳየው ሰብአዊነት ምስጋናቸውን ያቀርባሉ”ሲሉም በመግለጫቸው ተናግረዋል፡፡ ደንበኞቻቸው ጥፋት የሌለባቸው ንጹሐን መኾናቸውንም...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/kuwait-frees-a-group-of-jailed-americans-including-contractors-held-on-drug-charges/8009398.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/kuwait-frees-a-group-of-jailed-americans-including-contractors-held-on-drug-charges/8009398.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 17:03:57 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/2b3bac0b-d475-42e6-0758-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቀረጡ ጉዳይ በዩናይትድ ስቴትስ ኢኮኖሚ ላይ ያስከተለው አለመረጋጋት</title>
            <description>የቀረጡ ጉዳይ ከዋጋ ንረት ስጋት ጋራ ተዳምሮ በፈጠረው አለመረጋጋት የተነሳ ሰኞ እና ማክሰኞ የዩናይትድ ስቴትስ የአክሲዮን ገበያ አሽቆልቁሏል፡፡
በአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ እና በሕዝብ ብዛት ትልቋ የካናዳ ጠቅላይ ግዛት ኦንታሪዮ ጠቅላይ ሚንስትር ደግ ፎርድ መካከል የሁለቱን ሀገሮች የንግድ ውዝግብ በሚመለከት የተደረገውን ልውውጥ ጠቅሳ የቪኦኤ የኋይት ሐውስ ዘጋቢ ካሮላይን ፕሬሱቲ የላከችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
የቪኦኤ ዋትስአፕ ቻናል ይከተሉ 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8009199.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8009199.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 13:56:26 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0c7bb9ac-79cd-4505-0e03-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በግሪንላንድ ምርጫ ያሸነፈው ፓርቲ የትረምፕን ዕቅድ ተቃወመ</title>
            <description>በግሪንላንድ በተካሄደው የምክር ቤት ምርጫ፣ ሀገሪቱ በሂደት ከዴንማርክ ነጻ እንድትወጣ የሚደግፈው ዴሞክራቲት ፓርቲ ያልተጠበቀ ድል ተቀዳጅቷል፡፡
የትላንት ማክሰኞው ምርጫ የተካሄደው፣ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ደሴቲቱን ለመጠቅለል ያላቸውን እቅድ ይፋ ባደረጉበት ድባብ ውስጥ ነው፡፡
ዲሞክራቲት ፓርቲ “የግዛቲቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወስኑት የግሪላንድ ነዋሪዎች ናቸው” በማለት የትረምፕን ንግግር ሲቃወም ቆይቷል፡፡
“የምርጫው ውጤት ግሪንላንድ አትሸጥም የሚለውን ግልፅ መልዕክት ለትረምፕ ማስተላለፍ አለበት” ሲሉ የፓርቲው መሪ ጄንስ ፍሪደሪክ ኒልሰን ለስካይ ኒውስ ተናግረዋል።
&quot;እኛ አሜሪካዊ መሆን አንፈልግም። ፣ ዴኒሽ መኾንም አንፈልግም። የምንፈልገው ግሪንላንድነታችንን  ነው። ወደፊትም  ነፃነታችንን እንፈልጋለን። የራሳችንን ሀገር እርሳቸው በሚሰጡት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8008519.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8008519.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 22:30:23 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/8231741b-316a-4e22-0b45-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>