<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>ዜና - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/3167</link>
        <description>📜 ቪኦኤ-አማርኛ ስለ ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ አፍሪካ፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ዓለም አቀፍ በዲጂታል፣ በራዲዮና በቴሌቪዥን ዜናና ዘገባዎችን ለአድማጭና ለተመልካች ያቀርባል።  </description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>ዜና - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/3167</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Sat, 25 Apr 2026 04:28:10 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zt$gteitjt" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>የባለ ሥልጣናት መፈታት ለደቡብ ሱዳን ውጥረት መርገብ ቁልፍ ጉዳይ ነው ተባለ</title>
            <description>የደቡብ ሱዳን መንግሥት በሀገሪቱ የተፈጠረውን ውጥረት ተከትሎ የታሰሩ ባለሥልጣናትን እንዲፈታ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አባል ሀገራት መሪዎች ጥሪ አቅርበዋል።
የኢጋድ አባል ሀገራት ይኼንኑ የደቡብ ሱዳን ግጭት አስመልክተው ረቡዕ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም በበይነ መረብ ባደረጉት ስብሰባ የደቡብ ሱዳን መሪዎች ውጥረቱን ለማርገብ ውይይት እንዲጀምሩም ጠይቀዋል።
በደቡብ ሱዳን የጁባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር የኾኑት ፕሮፌሰር መልሃ ራውት ውጥረቱ የባለሥልጣናቱ መፈታት ውጥረቱን ለመርገብ መወሰድ ካለባቸው ቁልፍ ርምጃዎች አንዱ መኾኑን ገልጸዋል።
በአገሪቱ የቀጠለው የፀጥታ ችግር ዋነኛ ምክንያት ግን እ.አ.አ. በ2018 የተፈረመው የሰላም ስምምነት አተገባበር መጓተት መኾኑን ጠቅሰዋል።


</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/south-sudan-call-for-de-escalation/8011031.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/south-sudan-call-for-de-escalation/8011031.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 22:43:34 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/334741c0-bd9e-4b26-099c-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአፍሪካ የኅይል አቅርቦት ላይ ያተኮረውና በዋሽንግተን ዲሲ የተካሔደው ጉባኤ</title>
            <description>የአሜሪካ መንግሥት ባለሥልጣናት፣ የአፍሪካ ምኒስትሮች፣ ኢንቨስተሮች፣ የግል ገንዘብ አበዳሪዎች፣ እንዲሁም የአገልግሎትና የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች ዓመታዊ ለሆነውና በአፍሪካ የኅይል አቅርቦት ላይ በሚያተኩረው ጉባኤ ላይ ባለፈው ሳምንት በዋሽንግተን ዲሲ ተገናኝተው ነበር።
“መፃኢው የአሜሪካ እና የአፍሪካ የኅይል ትብብር” በተሰኘ መሪ ቃል በተካሄደው ጉባኤ፣ በአዲሱ የትረምፕ አስተዳደር የአሜሪካ መንግሥትም ሆነ የግል ኩባንያዎች የአፍሪካን የኤሌክትሪክ ኅይል ልማት፣ መሠረተ ልማት እንዲሁም የማዕድን ሃብትን በተመለከተ ያላቸውን ተሳትፎ እንደገና ለማዋቀር፣ የአሜሪካ ባለሥልጣናትና የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች ተወካዮች መክረዋል። 
የቪኦኤው አንተኒ ላብሩቶ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/labruto-us-africa-energy/8011019.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/labruto-us-africa-energy/8011019.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 22:40:33 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/f6e4fa2b-1590-4be5-09b6-08dd5c8b1668_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት በዶ.ር ደብረ ጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን ወቀሰ</title>
            <description>የኢትዮጵያ መግሥት በዶ.ር ደብረ ጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን የፕሪቶሪያውን ስምምነት ጥሷል ማለቱን የሀገር ውስጥ ብዙኅን መገናኛ ዘገቡ።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት፣ በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ አዲስ አበባ ለሚገኙ ዲፕሎማቶች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በማብራሪያቸው፣ ለፕሪቶሪያው ስምምነት መተግበር የዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ድጋፍ መጠየቃቸውን የመንግሥት ብዙኅን መገናኛዎቹ ዘግበዋል፡፡
በዶ/ር ደብረ ጽዮን የሚመራው ቡድን ስምምነቱን ጥሷል መባሉን ማስተባበሉን በማስተባበል፣ በአንጻሩ ስምምነቱ የተጣሰው በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ ቡድን ነው ሲል በተደጋጋሚ ምላሽ መስጠቱ ይታወቃል፡፡ በሌላ በኩል የአፍሪካ ኅብረት፣ በክልሉ ባለው ውጥረት ተሳታፊ የሆኑ አካላት ራሳቸውን እንዲያቅቡና ችግሩ በውይይት እንዲፈታ ጠይቋል፡፡
በህወሓት የፖለቲካ አንጃዎች መካከል በተፈጠረው ሽኩቻ እጇ እንዳለበት በአቶ ጌታቸው የተከሰሰው የኤርትራ መንግሥት ክሱን አስተባብሏል።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት፣ በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ በአዲስ አበባ ለሚገኙ ዲፕሎማቶች ማብራሪያ መስጠታቸውን ጠቅሶ የዘገበው ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት፣ በውይይቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ራሱን ነጥሎ የወጣው የህወሓት አንጃ የፕሪቶሪያው ስምምነት ሙሉ ለሙሉ እንዳይተገበር እንቅፋት ኾኗል ማለታቸውን ዘግቧል።
በህወሓት አመራሮች መካከል አለመግባባቱ ከተካረረ ወዲህ በፌደራል መንግሥቱ በኩል እንዲህ ዐይነት አቋም ሲያዝ የመጀመሪያው ነው።
የትግራይ ክልል ሰሞናዊው ውጥረት ከተከሰተ በኋላ፣ በአዲስ አበባ ላሉ ዲፕሎማቶች ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ መንግሥት በተሰጠ በዚኽ ማብራሪያ ላይ፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም በክልሉ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት አስፈላጊውን እገዛ እንዲያደርግም ዶ/ር ጌዲዮን ጥሪ ማድረጋቸውን ከፎቶግራፎች እና ከቪዲዮ ጋራ የወጣው ዘገባ አመልክቷል፡፡
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳም፣ በክልሉ ላለው ውጥረት፣ “መፈንቅለ መንግሥት እያደረገ ነው” ያሉትን እና “አንድ የህወሓት አንጃ” ሲሉ የጠቀሱትን አካል ተጠያቂ በማድረግ በትላንትናው ዕለት ለጋዜጠኖች ከሰጡት ማብራሪያ ጋራ ተመሳሳይ ይዘት ያለው ማብራሪያ ለዲፕሎማቶች መስጠታቸው በዘገባው ተመልክቷል፡፡
በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው ህወሓት ምክትል ሊቀ መንበር የኾኑት አቶ ዐማኑኤል አሰፋ በበኩላቸው፣ ትላንት ማምሻውን ለብዙኀን መገናኛ በሰጡት መግለጫ፣ በአኹኑ ጊዜ በትግራይ ክልል እየተካሔደ ያለው፣ &quot;በወረዳዎች እና በከተሞች የሕገ መንግሥት ማስከበር እንጂ፣ መፈንቅለ መንግሥት ተብሎ እየተገለጸ ያለው ስሕተት ነው፤&quot; ሲሉ ክሱን ተከላክለዋል፡፡
“በትግራይ ክልል በአሁኑ ጊዜ አዲስ የተለየ ክስተት ሳይኖር በወሬ ግርግር እንደተፈጠረ እየተገለፀ ነው ያለው” ሲሉም ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል የአፍሪካ ኅብረት፣ በህወሓት ውስጥ የተፈጠረውን ሁኔታ በጥልቅ ስጋት በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
ኅብረቱ በመግለጫው፣ “በአሁኑ ወቅት እየታዩ ካሉት ሁኔታዎች በመነሳት ወገኖቹ በህወሀት እና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል ፕሪቶሪያ ላይ በተፈረመው ግጭቶችን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት የተካተቱትን ግዴታዎች እንዲያከብሩ እናበረታታለን ብሏል።
ስምምነቱን ማክበር በብዙ ፈተና የተገኘው ሰላም እንዲዘልቅ ብሎም ለዘላቂ ሰላም ግንባታ፥ ለዕርቅ እና ለልማት አመቺ ሁኔታ ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን አጽንዖት ሰጥተን እናሳስባለን ያለው የአፍሪካ ኅብረት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የገቧቸውን ቃሎች እንዲያከብሩ እና ሰላማዊ መፍትሄ እንዲገኝ በትብብር እንዲሰሩ እንማጸናለን ብሏል።
የአፍሪካ ኅብረት ለፕሪቶሪያ ስምምነት ተግባራዊነት የማያወላውል ድጋፉን በድጋሚ ያረጋግጣል፥ በዚህ ሂደትም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር አብሮነቱን ይቀጥላል ያለው መግለጫው ኅብረቱ በከፍተኛ ልዑክ አማካይነት በወገኖቹ መካከል ውይይት እና ትብብር የሚኖርበትን መንገድ ማመቻቸቱን ለመቀጠል ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ከፍተኛ አባል ሴናተር ጂን ሻሂን በኤክስ ገጽ ባሰፈሩት ጽሑፍ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል እየተባባሰ ያለው ውጥረት እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።
“ከግጭት እና አለመረጋጋት ይልቅ ለሰላም እና ለዲፕሎማሲ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል” ያሉት ሴናተር ሻሂን፣ “መሪዎቹ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነትን እንዲያከብሩ ጥሪ አቀርባለሁ” ብለዋል፥ አስከትለውም በአፍሪካ ቀንድ የሚፈጠር ግጭት “በቀጣናው የባሰ ስቃይ ከማስከተል ያለፈ ውጤት አይኖረውም” ብለዋል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ፣ “ከኤርትራ ጋር ግንኙነት እየፈጠሩ ያሉ አካላት አሉ” ሲሉ ወንጅለው ነበር፡፡
በሌላ በኩል የኤርትራ የማስታወቂያ አቶ የማነ ገብረ መስቀል ትላንት በኤክስ ላይ ባወጡት መግለጫ፣ “ኤርትራ በህወሓት የፖለቲካ አንጃዎች ውስጥ የተፈጠረውን የውስጥ ሽኩቻ የማባባስ ፍላጎት የላትም ፤ ይህ በትግራይ ህዝብ ላይ አላስፈላጊ ስቃይ ያስከትላል ብላ ታምናለች” ብለዋል።
በዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል በሚመራ ህወሓት ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ዐማኑኤል አሰፋም ትላንት በሰጡት መግለጫ፣ ከኤርትራ መንግስት ጋራ ሌላ አካልን ለመጉዳት ተብሎ የሚፈፀም ግንኙነት የለንም በማለት የአቶ ጌታቸውን ክስ ተከላክለዋል።
የኤርትራው ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ በትላንቱ የኤክስ መግለጫቸው “የኤርትራ ጦር በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል አለ” በሚል በተወሰኑ አካላት የሚሰነዘረው ተደጋጋሚ ክስ “ፍፁም ሀሰት እና ግጭት ለመቀስቀስ ምክንያት ለመፍጠር የሚደረግ ነው” ሲሉ ገልፀዋል፡፡
“ኤርትራ የፕሪቶሪያን የሰላም ስምምነት ለማፍረስ ምንም ፍላጎት የላትም። ይህ በመሰረቱ የኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ነው” ያሉት አቶ የማነ “በቀይ ባህር ዙሪያ በተለያዩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሃይሎች ሌት ተቀን የሚያወጧቸው ግጭት ቀስቃሽ መግለጫዎች ለአላስፈላጊ ውጥረት ምንጭ ሆነው ቀጥለዋል” በማለት ከሰዋል፡፡
በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እና የኤርትራን ክስ በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለአሁን አልተሳካም፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/tigray-tension-update/8011028.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/tigray-tension-update/8011028.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 21:59:39 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0cc21c8a-e1d4-4e12-b76c-5691b2b9e8b7_cx0_cy5_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተመድ  የሶሪያ ግጭት እንዲቆም ጥሪ አቀረበ</title>
            <description>የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሶሪያ ልዩ መልዕክተኛ፣ ከፕሬዝደንት ባሽር አል አሳድ ሥልጣን መወገድ ተከትሎ  ባለፉት ሦስት ወራት ዐዲስ በተቀሰቀሰው ግጭት እየታመሰች ባለችው ሀገር ሁከቱ እንዲቆም ተማጸኑ፡፡ የሰላማዊ ዜጎች ደኅንነት እንዲጠበቅም  ጥሪ አቀረቡ፡፡
የመንግሥታቱ ድርጅት ልዩ መልዕክተኛ ጌር ፔደርሰን ጥሪያቸውን ያቀረቡት፣  የዲሞክራሲ ደጋፊዎች ሀገሪቱን ለዐስርት ዓመታት ወደ ዘለቀው የርስ በርስ ጦርነት ያመራው ጸረ  አሳድ ተቃውሞ የተጀመረበት 14ኛው ዓመት መታሰቢያ በሆነው በዛሬው ዕለት ነው፡፡
“የለውጥ ጥያቄ ጭካኔ የተሞላበት ከፍተኛ ብጥብጥ ገጥሞታል፣ በዘመናችን እጅግ አሰቃቂ ወደ ኾነ  ግጭት አምርቷል” ያሉት ፔደርሰን “ግጭቱ ጥልቅ  የሆነውን አስከፊውን የሰው ልጅ ጭካኔ አጋልጧል።” ብለዋል፡፡
“የሚወዷቸውን በሞት ያጡ ቤተሰቦች ሐዘን ላይ ናቸው፡፡ ማኅበረሰቦች ተበታትነዋል፡፡ ሚሊዮኖች ከቀያቸው ተነቅለዋል፣ብዙዎችም የጠፉባትን በማፈላለግ ላይ ይገኛሉ” ሲሉም ፔደርሰን አክለዋል፡፡
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት  ሶሪያ ውስጥ ግጭት ከ6 ሚሊዮን በላይ ስደተኞችን ጨምሮ ወደ 12 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን አፈናቅሏል ብሏል።
አሳድ እ.ኤ.አ. ታኅሣሥ 2024 ከሥልጣን ቢወገዱም ከመጋቢት 6 ጀምሮ በጠረፉ ክፍለ ግዛት በኩል በተጀመረ ሁከት ሀገሪቱ በርካቶችን ለሞት በዳረገ ሁከት ተንጣለች፡፡
የቀድሞ ፕሬዝደንት ታማኞች ከጸጥታ ኃይሎች ጋራ ባደረጉት አስከፊ ግጭት በርካታ ሲቪሎችን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሞተዋል፡፡


</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un---syria/8010894.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un---syria/8010894.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 20:17:30 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/c5473208-e41e-4ba1-0fa7-08dd5c8d307c_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሚሳይል መስሪያ ግብአት በመጫን የተጠረጠረችው ሁለተኛ የኢራን መርከብ ከቻይና ተነሳች</title>
            <description>ከቻይና የሚሳይል ነዳጅ መስሪያ ቁልፍ ግብአቶችን ጭናለች ተብላ በምዕራባዊያን የዜና ዘገባዎች  የተጠረጠረችው ሁለተኛዋ የኢራን  መርከብ ወደ ኢራን እያመራች መሆኑን የቪኦኤ ልዩ የትንታኔ ዘገባ አመልክቷል፡፡
የመርከብ እንቅስቃሴ ክትትል ድረ-ገጾች እንደሚያሳዩት የኢራን ባንዲራ የሚያውለበልበው ጃይራን የተባለው የጭነት መርከብ፣ ከቻይና ይነሳል ተብሎ ከተጠበቀበት ጊዜ ከአንድ ወር በኋላ ዘግይቶ ባለፈው ሰኞ መነሳቱ ተጠቅሷል፡፡
በጥር እና በየካቲት  ዘ ፋይናንሺያል ታይምስ፣ ዘ ዎል ስትሪት ጆርናል እና ሲ ኤን ኤን ባቀረቧቸው ዘገባዎች፣ ቴህራን  በሚሳይል ነዳጅ ውስጥ ጥቅም ላይ የሚውለውን 1,000 ሜትሪክ ቶን ኬሚካል (ሶዲየም ፐርክሎሬት) ለመጫን ከምትጠቀምባቸው ሁለት መርከቦች መካከል ጃይራን አንዱ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡
ሦስቱ የዜና ማሰራጫዎች ስማቸው ያልተጠቀሱ የምዕራባውያን የስለላ ምንጮችን ጠቅሰው እንደተናገሩት የተጠቀሱት ኬሚካሎች ለኢራን 260 መካከለኛ ርቀት ሚሳይሎችን ማምረት ያስችላሉ፡፡
በዘገባዎቹ ጎልቦን በሚል ስያሜ የተጠቀሰው ሌላኛው የኢራን የጭነት መርከብ፣ እ ኤ አ የካቲት 13  ከምሥራቃዊ ቻይና ብሩክ አባስ ወደተባለው የኢራን ወደብ ያደረገውን የ19 ቀናት ጉዞ አጠናቋል፡፡
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጃይራን ከቻይና መነሳት አስመልክቶ ከቪኦኤ ለቀረበለት ጥያቄ ምንም አስተያየት አልሰጠም፡፡ በኒውዮርክ የሚገኘው የኢራን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሚሽንም ባለፈው ማክሰኞ በኢሜል ለተላከከለት ተመሳሳይ የቪኦኤ ጥያቄ ምላሽ አልሰጠም።
ባለፈው ወር የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለቪኦኤ እንደተናገረው፣ ኢራን ኬሚካሎቹን ለማስመጣት፣ ጎልቦን እና ጃይራን የተባሉ መርከቦችን እንደምትጠቀም በፋይናንሺያል ታይምስ እና ዎል ስትሪት ጆርናል ከወጡ ዘገባዎች ተመልክቷል፡፡
ቃል አቀባዩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በደህንነት መረጃ ጉዳዮች ላይ ምንም ዐይነት አስተያየት ባይሰጥም &quot;ለኢራን ሚሳይል ወይም ሌሎች የጦር መሳሪያ ፕሮግራሞች ሊጠቅሙ የሚችሉ እቃዎች፣ መሣሪያዎች እና ቴክኖሎጂዎች መስፋፋትን መከላከል ላይ ማትኮሩን እና ኢራንን በማዕቀብ ተጠያቂ ማድረጉን ቀጥሏል&quot; ብለዋል ።
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ ማኦ ኒንግ፣ እ ኤ አ ጥር 23 በዜና ማሰራጫዎቹ ስለቀረቡት ዘገባዎች በሰጡት ምላሽ ፣ ቻይና፣ በራሷ የኤክስፖርት ቁጥጥር እና፣ በዓለም አቀፍ ግዴታዎች እንደምትገዛ ጠቅሰው፣  እንደ ህገ ወጥ የተናጠል ማዕቀቦች የምትቆጥራቸውን የሌሎችን ሀገሮች ተጽዕኖ እንደማትቀበል ተናግረዋል፡፡  
ባለፈው ወር የቻይና መንግሥት የመገናኛ ብዙሃን ስለ ጃይራን ጉዞ ምንም ተናግረው አያውቁም፡፡ በቻይና ማህበራዊ ሚዲያ መድረኮችም ስለ ኢራን መርከብ የተደረገ ውይይት እንዳልነበረ የቪኦኤ የማንዳሪን ቋንቋ አገልግሎት ዘገባ አመልክቷል፡፡
መሠረቱን ኒው ዮርክ ያደረገ ፣ የፖለቲካዊ ስጋቶች ጉዳይ አማካሪ ተቋም፣ ዩሬዥያ ቡድን ከፍተኛ የኢራን ተንታኝ የሆኑት፣ ግሪጎሪ ብሩው፣ &quot;ኢራን፣ ጃይራንን ከመላኳ በፊት፣ ጎልቦን የተባለው ሌላኛው መርከብ ጉዞውን ክልከላ ሳይገጥመው ለማጠናቀቅ ይችል እንደሆነ ለመፈተሽ ፈልጋ ሊሆን ይችላል&quot; ብለዋል ።
ብሩው አያይዘውም &quot;በአሜሪካ ማዕቀብ ሥር ከሆነው የኢራን ሚሳይል ኢንዱስትሪ ጋር የተያያዙ በጣም ሚስጥራዊነት ያላቸው ቁሶችን የያዙ መርከቦች የመያዝ አደጋ ተጋርጦባቸዋል፣ ኢራናውያንም ይህን አውቀውታል&quot; ብለዋል ።
በጂም ሪሽ እና በፒት ሪኬትስ የሚመሩ ስምንት ሪፐብሊካን ሴነተሮች፣ እ ኤ አ የካቲት 4 ቀን ስለ ኢራን-ቻይና የኬሚካል ትብብር ደባ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ደብዳቤ ልከዋል፡፡
 የዜና ማሰራጫዎቹ ዘገባዎች ትክክለኛ ከሆኑ ከአሜሪካ ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር “አሁን ጉዞ ላይ የሚገኘውን ጭነት ጣልቃ ገብተው እንዲያስቆሙ” አሳስበዋል ።
በቅርቡ ጎልቦን ከቻይና ወደ ኢራን ባደረገው ጉዞ መንገድ ላይ መያዙን የሚያሳይ ምንም ምልክት አልታየም።
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ስለ ደብዳቤው ከቪኦኤ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፡- “ከምክር ቤት ጋር በሚደረጉ መልእክቶች ላይ አስተያየት አንሰጥም” ብለዋል። 
የሪኬትስ ቢሮም ሩቢዮ ከሴነተሮቹ ለተላከላቸው ደብዳቤ ምላሽ ሰጥተው እንደሆነ ከቪኦኤ ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ አልሰጠም።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/iran-china-missile-scheme-/8010868.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/iran-china-missile-scheme-/8010868.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 19:50:09 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/73570913-c12b-459d-b0a3-828c76588f8a_cx0_cy18_cw0_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቆዳ ላይ ቀላል እብጠት መሰል ነገሮች እና የቆዳ ቀለምን የሚለውጡ ምልክቶች ለጤና ያሳስቡ ይኾን?</title>
            <description>በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የቆዳ ቀለምን የሚለውጡ ፣በእንግሊዝኛው አጠራር ‘ሞሎች’ በአንዳንድ ባህሎች ዘንድ እንደ ውበት ምልክት ይታያሉ። በተለይ የጥቁር ዝርያ ባላቸው ሕዝቦች ውስጥ፣ በስፋት የሚታዩና የተለመዱ ናቸው።
በአንጻሩ፣ ለጤና መታወክ ይዳርጉ ይኾን? በሚል ለጭንቀት የሚጋለጡ ወገኖች የሚሰሟቸውን ስጋቶች የሚያነሣው ጁማ ማጃንጋ፣ ለእነዚኽ እና ተያያዥ ጥያቄዎች ምላሽ ፍለጋ፣ ከናይሮቢ ኬንያ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/kenya-moles-and-skin-tags-tv-headline-skin-tags-and-moles-/8010760.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/kenya-moles-and-skin-tags-tv-headline-skin-tags-and-moles-/8010760.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 18:12:12 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/6b63bcf5-b100-4ef6-0fa4-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አይኤምኤፍ እና ኢትዮጵያ በዋጋ ግሽበት ትንበያ ተለያዩ</title>
            <description>. ትንበያዎቹ &quot;የተለያዩ ብቻ ሳይኾኑ ከእውነታውም የራቁ ናቸው&quot; - ባለሞያ
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ)፣ በቅርቡ ስለ ኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ያወጣው ትንበያ፣ እ.ኤ.አ በ2025፣ 25 ከመቶ መድረሱን ይገልጻል፡፡ የዋጋ ንረቱ አኹን ካለበት ሁለት አኀዝ ወደ ነጠላ አኀዝ ለመውረድ እስከ 2028 ሊቆይ እንደሚችልም አይኤምኤፍ ተንብይዋል፡፡
በአንጻሩ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የዋጋ ግሽበቱ እየወረደ መምጣቱንና አኹን ከ15 እስከ 16 በመቶ ዝቅ ማለቱን ይናገራል፡፡
በለንደን የሚገኙት የፋይናንስ እና የምጣኔ ሀብት ባለሞያ ዶር. አብዱልመናን መሐመድ ሃምዛ ግን፣ የአይኤምኤፍም ኾነ የኢትዮጵያ መንግሥት ቁጥሮች፣ &quot;የተለያዩ ብቻ ሳይኾኑ ከእውነታው የራቁ ናቸው፤&quot; ይላሉ፡፡
ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ አጭር ቆይታ ያደረጉት ዶር. አቡዱልመናን፣ በአይኤምኤፍ እና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል ያለውን የትንበያ ልዩነት አብራርተዋል፡፡ ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይይ ይከታተሉ።
   የቪኦኤ ዋትስአፕ ቻናል ይከተሉ
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/imf-ethiopia-s-inflation/8010710.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/imf-ethiopia-s-inflation/8010710.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 18:06:32 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5ca8d0af-a26a-49ff-0900-08dd5c8b1668_cx0_cy12_cw0_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያውያት ሴቶች ጥያቄ ምንድን ነው? - የአድማጭ ተመልካቾች አስተያየት</title>
            <description>መጋቢት፥ የዓለም አቀፍ ሴቶች ወር ነው። ሴቶች ትምህርትንና ሥራን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች እኩል ዕድል እንዲያገኙ ለማብቃት በመላ ዓለም የሚደረጉ ጥረቶች፦ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በጦርነት እና በሌሎችም ሰው ሠራሽ ምክንያቶች መጓተታቸውን፣ በሴቶች ላይ አተኩረው የሚሠሩ ተቋማት ያወጧቸው ሪፖርቶች ያሳያሉ። 
ዘንድሮም፣ ወርኃ መጋቢት(ማርች 8)፥ “ትግበራን ማፋጠን” በሚል መሪ ቃል በመላው ዓለም እየታሰበ ይገኛል። 
በዐዲስ አበባ የአሜሪካ ድምፅ ዘጋቢ ኬኔዲ አባተ፣ በርእሰ መዲናዪቱ ጎዳናዎች ላይ ተዘዋውሮ፤ ለመኾኑ የኢትዮጵያውያት ሴቶች ጥያቄ ምንድን ነው? የሴቶች እኩልነት እንዲሰፍን ምን ቢደረግ ይበጃል? በማለት ጠይቆ ያገኘውን ምላሽ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/women-day-voxpop/8010711.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/women-day-voxpop/8010711.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 17:29:27 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/196b6129-1211-4881-3514-08dd5c897904_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>&quot;በትግራይ መፈንቅለ መንግሥት እየተፈጸመ ነው&quot; ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ተናገሩ</title>
            <description>በትግራይ ክልል፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ቢሮዎች በየደረጃው በመስበር እና ማኅተሞችን በመንጠቅ መንግሥትን የማውረድ ሥራ እየተሠራ ነው፤ ሲሉ ፕሬዘደንቱ አቶ ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል።
በዐዲስ አበባ የሚገኙት አቶ ጌታቸው፣ ዛሬ ኀሙስ፣ መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም. ረፋድ፣ በሸራተን ዐዲስ ሆቴል ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ አኹን በክልሉ ያለው ኹኔታ፣ &quot;የፕሪቶርያውን ስምምነት የሚጥስና ከፍተኛ ግጭት የሚፈጥር ስለኾነ፣ የፌደራል መንግሥቱ ይህን የሚያስቆም ርምጃ መውሰድ አለበት፤” ብለዋል።
“በምክር ቤት ወይም በካቢኔ ደረጃ ተሰብስበን የፌዴራሉ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ ያቀረብነው ጥያቄ የለም፤” ያሉት አቶ ጌታቸው፣ በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት መሠረት፣ የፌደራል መንግሥቱ ከህወሓት ጋራ ያቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር የመታደግ ሓላፊነት እንዳለበት አመልክተዋል።
ይህ ማለት “ጦር አዝምቶ ጦርነት ይቀስቅስ ማለት አይደለም፤” ያሉት አቶ ጌታቸው፣ ነገር ግን፣ ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጋራ በመኾን፣ አኹን በክልሉ ባለው ኹኔታ ምክንያት ጦርነት እንዳይፈጠር የሚያስችሉ ርምጃዎችን መውሰድ የፌዴራል መንግሥት ኃላፊነት ነው፤” ሲሉ አስረድተዋል።
ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ፣ በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫቸው ከኤርትራ መንግሥት ጋራ ግንኙነት ያላቸው አመራሮች ይኖሩ እንደኾነ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ &quot;ግንኙነት ያላቸው የተወሰኑ ግን አደጋ መፍጠር የሚችሉ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ አመራሮች አሉ፤&quot; ሲሉ ወንጅለዋል፡፡
በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው ህወሓት ምክትል ሊቀ መንበር የኾኑት አቶ ዐማኑኤል አሰፋ በበኩላቸው፣ ዛሬ ማምሻውን ለብዙኀን መገናኛ በሰጡት መግለጫ፣ በአኹኑ ጊዜ በትግራይ ክልል እየተካሔደ ያለው፣ &quot;በወረዳዎች እና በከተሞች የሕገ መንግሥት ማስከበር እንጂ፣ መፈንቅለ መንግሥት ተብሎ እየተገለጸ ያለው ስሕተት ነው፤&quot; ሲሉ ክሱን ተከላክለዋል፡፡
ከኤርትራ መንግሥት ጋራ &quot;ግንኙነት አለ፤&quot; በሚል በአቶ ጌታቸው የቀረበውን ውንጀላ በተመለከተም፣ የኤርትራ መንግሥትን ጨምሮ ከማንኛውም የውጭ አካል ጋራ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ይኹን የፌደራል መንግሥቱን ለመጉዳት የተደረገ ግንኙነት የለም፤ ሲሉ አቶ ዐማኑኤል ምላሽ ሰጥተዋል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/getachew-s-presser-amanuels-reaction-/8010001.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/getachew-s-presser-amanuels-reaction-/8010001.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:53:52 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a0b29bb2-c45e-4a4e-082e-08dd5c8b1668_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር እንዲቆይ ፍርድ ቤት ፈቀደ</title>
            <description>ባለፈው ሰኞ ሌሊት፣ ከምትኖርበት ሕንፃ አምስተኛ ፎቅ ላይ ቁልቁል ወድቃ ሕይወቷ ካለፈው፣ ሞዴል እና የማስታወቂያ ባለሞያ ቀነኒ አዱኛ ሞት ጋራ በተያያዘ ተጠርጥሮ በቁጥጥር ሥር የሚገኘው እጮኛዋ አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ፣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር ቆይቶ ምርመራ እንዲቀጥል ፍርድ ቤት አዘዘ።
የዐዲስ አበባ ፖሊስ፣ ከቀነኒ ሞት ጋራ በዋና ወንጀል አድራጊነት የጠረጠረው አንዱዓለምን እንደኾነ በመግለጽ፣ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቆ የነበረ ሲኾን፣ ከጠበቃው ጋራ ፍርድ ቤት የቀረበው አንዱዓለም ደግሞ፣ የቀነኒ ሕይወት ያለፈው በአደጋ እንደኾነ በመግለጽ ከእስር እንዲፈታ አመልክቶ ነበር።
ሟች ቀነኒ አዱኛ ዋቆ፣ ሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ከሌሊቱ 10 ሰዓት ገደማ፣ አምስተኛ ወለል ላይ ከሚገኘው የቤቷ የማብሰያ ክፍል ቨረንዳ በኩል፣ ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ ኹኔታ ቁልቁል ወደ ምድር ወድቃ ለሕክምና ርዳታ ወደ ያኔት ሆስፒታል እየተወሰደች ባለችበት ወቅት ሕይወቷ ማለፉን፣ የዐዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ትላንት አስታውቆ ነበር።
የምርመራ መዝገቡን ለፍርድ ቤቱ ያቀረበው ፖሊስ፣ ሞዴል ቀነኒ፥ ሕይወቷ ባለፈበት ወቅት፣ ፍቅረኛዋ አርቲስት አንዱዓለም በቤት ውስጥ እንደነበር ጠቅሶ፣ የአስከሬን ምርመራ ውጤትን ጨምሮ የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎችን መርምሮ ለማቅረብ 14 ቀን የምርመራ ጊዜ ጠይቆ ነበር።
&quot;ለምርመራ የሚያበቃ በቂ ምክንያት የለም፤&quot; በሚል ተቃውሞ ማቅረባቸውን ለአሜሪካ ድምፅ የገለጹት፣ የአርቲስት አንዱዓለም ጎሣ ጠበቃ አቶ ሊባን አብዲ ሑሴን፣ የቀነኒ ሕይወት ያለፈው &quot;በአደጋ ነው&quot; የሚል ምላሽ መስጠታቸውን አስረድተዋል።
የግራ ቀኙን ክርክር ያደመጠው ፍርድ ቤቱ፣ የአስከሬን ምርመራ ውጤትን ጨምሮ የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎችን አጠናቅሮ እንዲያቀርብ፣ ለፖሊስ ተጨማሪ የ13 ቀናትን የጊዜ ቀጠሮ በመፍቀድ፣ ለመጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም. ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/andualem-gosa-court-/8009809.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/andualem-gosa-court-/8009809.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:29:03 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0c9fc9b2-79e6-4c5e-0eca-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሩሲያ የተቆጣጠረቻቸውን የዩክሬን ግዛቶች እንደያዘች መቀጠል ትሻለች</title>
            <description>ሩሲያ በዩክሬን የምታካሒደውን ጦርነት ለማስቆም፣ አሜሪካ የምታደርገው ጥረት በክሬምሊን ላይ ጫናን ፈጥሯል። ይኹንና ሞስኮ አሁንም በቀጠለችው ጥቃት ተጨማሪ የዩክሬን ስፍራዎችን ተቆጣጥራለች፡፡
በሩሲያ የሚገኙ አንዳንድ ባለሥልጣናት ደግሞ፣ በድርድሩ ሩሲያ ምንም ነገር አሳልፋ መስጠትን እንደማትሻ በመናገር ላይ ናቸው።
የቪኦኤው ጄፍ ከስተር የላከውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/russia-ukraine-concessions/8009965.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/russia-ukraine-concessions/8009965.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:21:08 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/fce71d0f-fae4-482a-0ed0-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሦስት አባላቱ መታሰራቸውን አስታወቀ</title>
            <description>የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት የተደረገውን የሕገ መንግሥት ማሻሻያ የተቃወሙትን አቶ ዮሐንስ ተሰማን ጨምሮ ሦስት አባላቱ እንደታሰሩበት አስታወቀ፡፡
የፓርቲው የውጭ እና ዓለም አቀፍ ዘርፍ ሓላፊ ዶር. መብራቱ ዓለሙ፣ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፣ የሕገ መንግሥት ማሻሻያውን በመቃወማቸው ታስረዋል የተባሉት አቶ ዮሐንስ ተሰማ፣ የክልሉ ምክር ቤት አባል እንደኾኑ ጠቅሰው፣ ያለመከሰስ መብታቸው ግን እንዳልተነሳ ገልጸዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ፣ ከክልላዊ መንግሥቱ አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/opposition-member-arrest-/8009806.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/opposition-member-arrest-/8009806.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:12:15 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ገ/ሚካኤል ገ/መድህን)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/99f407d2-515a-4873-0e9e-08dd5c8d307c_cx0_cy12_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተዘግቶ የቆየው የመቐለ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት በዶር. ደብረ ጽዮን ቡድን ቁጥጥር ሥር ዋለ</title>
            <description>      &quot;የመፈንቅለ መንግሥት ሒደት ቅጥያ ነው&quot; - የጊዜያዊ አስተዳደሩ ሹም
ከህወሓት አመራሮች ውዝግብ ጋራ በተያያዘ ላለፉት መቶ ቀናት በዝግ የቆየው የመቐለ ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት፣ ዛሬ ኀሙስ፣ በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል በሚመራው ቡድን ቁጥጥር ሥር ውሏል።
በጊዜያዊ አስተዳደሩ የከተማዋ ከንቲባ እንዲኾኑ የተሾሙት አቶ ብርሃነ ገብረ ኢየሱስ፣ &quot;ጽንፈኛ&quot; ሲሉ የጠሩት ቡድን በወታደራዊ አመራሮች ድጋፍ ጽሕፈት ቤቱን እንደተቆጣጠረ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል፤ &quot;የመፈንቅለ መንግሥት ሒደት ቅጥያ ነው፤&quot; ሲሉም ድርጊቱን ኮንነዋል።
በዶር. ደብረ ጽዮን ሊቀ መንበርነት በሚመራው የህወሓት ቡድን የመቐለ ከተማ ከንቲባ እንዲኾኑ ታጭተው በከተማዋ ምክር ቤት የተሾሙት ዶክተር ረዳኢ በርሀ በበኩላቸው፣ &quot;ወደ ጽሕፈት ቤቱ የገባነው በሰላማዊ መንገድ ነው፤&quot; ሲሉ ተናግረዋል።
ተቀማጭነታቸው በዐዲስ አበባ ከተማ የኾኑ የዩናይትድ ስቴትን ጨምሮ የ25 አገሮች ኤምባሲዎች፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እያገረሸ ያለውን ውጥረት በቅርበት እየተከታተሉት እንደሚገኙ ገልጸው፣ ችግሩ በውይይት እንዲፈታ ጠይቀዋል። 
ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ። 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/mekelle-mayor-take-over-/8009904.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/mekelle-mayor-take-over-/8009904.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 22:25:45 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/846c6708-ef34-447d-345c-08dd5c897904_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኤኮዋስ የፀረ-ሽብር ጦሩ በተጠንቀቅ እንዲቆም አደረገ</title>
            <description>የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ &quot;ኤኮዋስ&quot; የቀጠናው የጦር ኃይል በተጠንቀቅ እንዲጠባበቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል። የጸጥታ ተንታኞች ርምጃውን ያደነቁ ቢሆንም፣ የተቋሙ ሦስት አባል ሀገራት በቅርቡ መውጣታቸው ውጤታማነቱን አጠራጣሪ እንደሚያደርገው ተገልጿል።
የናይጄሪያ መከላከያ ሚኒስትር ሞሃመድ ባዳሩ አቡባካር የኤኮዋስ የጦር ኃይል በተጠንቀቅ ላይ እንደሚሆን ያስታወቁት፣ ትላንት ማክሰኞ በተካሄደው የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት ጥምረት የሆነው ኤኮዋስ 43ኛ መደበኛ የፀጥታ ስብሰባ ወቅት ነው።
5 ሺሕ ወታደሮች እንደሚኖሩት የሚጠበቀው የጦር ኃይል፣ በቀጠናው የሚካሄዱትን ሽብርተኝነት እና ድንበር ዘለል ወንጀሎች ለመከላከል የሚደረግ ቀጠናዊ የፀጥታ እንቅስቃሴ አካል ነው።
አቡበከር በንግግራቸው &quot;ይህ  ኃይል በተጠንቀቅ እንዲቆም ሆኖ ሥራ መጀመሩ፣ የሽብርተኝነትን መስፋፋት ለመጋፈጥ እና የዜጎቻችንን ደኅንነት ለማረጋገጥ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት ያሳያል&quot; ብለዋል።
በተጨማሪ የኤኮዋስ የፀጥታ ኃላፊዎች በጊኒ ባህረ ሰላጤ የባህር ላይ ደኅንነት እና የሰላም ድጋፍ ለማድረግ በሚቻልበት መንገድ ላይም ተወያይተዋል።
የምዕራብ አፍሪካው ተቋም አካል የነበሩት ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር ከኤኮዋስ ተገንጥለው  &quot;የሳህል አገሮች ጥምረት&quot; የተባለ ኮንፌዴሬሽን አቋቁመዋል። ወታደራዊ አመራር ያላቸው ሦስቱም ሀገራት፣ ኤኮዋስን &quot; የአባል ሀገራቱን ጥቅም ከማስጠበቅ ይልቅ የውጭ ሀገራት ጥቅም ማስፈፀሚያ ሆኗል&quot; ሲሉ ይከሳሉ። 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ecowas-regional-bloc-activates-counterterror-force/8009724.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ecowas-regional-bloc-activates-counterterror-force/8009724.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 20:42:16 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9a78e2c0-aa66-46a3-95bd-53dfc7c9bc06_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ትረምፕ ከአውሮፓ በሚገቡ የአልኮል መጠጦች ላይ ከበድ ያለ ታሪፍ እንደሚጥሉ አስታወቁ</title>
            <description>የአውሮፓ ኅብረት ከአሜሪካ በሚገባው ዊስኪ ላይ የ50 በመቶ ታሪፍ መጣሉን ተከትሎ፣ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ከአውሮፓ በሚገባው የወይን ጠጅ፣ ሻምፓኝና ሌሎች የአልኮል መጠጦች ላይ የ200 በመቶ ታሪፍ እንደሚጭኑ አስጠንቅቀዋል።
የ27 ሃገራት ስብስብ የሆነውን የአውሮፓ ኅብረት &quot;በዓለም የከፋው ታክስና ታሪፍ ጣይ&quot; ሲሉ የገለጹት ትረምፕ፣ &quot;እ.አ.አ በ1993 ሲመሠረት ዓላማው &quot;ከአሜሪካ የኢኮኖሚ ጥቅም ለማግኘት ነው&quot; ብለዋል። 
ባለፈው አንድ ወር ከአሜሪካ ከፍተኛ የንግድ ሸሪኮች፣ ማለትም ከሜክሲኮ፣ ካናዳ፣ ቻይናና የአውሮፓ ኅብረት ጋራ የታሪፍ ውዝገብ ውስጥ የገቡት ትረምፕ፣ ታሪፉን መጣሉ አስፈላጊ የሆነው ሃገራቱ ወደ አሜሪካ የሚገባውን አደገኛ  ዕጽ እና መድሃኒት እንዲያስቆሙና እንዲሁም የሸቀጥ አምራቾች በውጪ ያላቸውን ፋብሪካ ዘግተው ወደ አሜሪካ እንዲመጡ ለማስገደድ መሆኑን ይገልጻሉ።
ትረምፕ ትላንት ረቡዕ የአውሮፓ ኅብረትን ጨምሮ ብረታብረት ወደ አሜሪካ በሚልኩ 35 ሃገራት ላይ የ25 በመቶ ታሪፍ ጥለዋል። አውርፓውያኑ በአጸፋው ከአሜሪካ በሚላከው የ28 ቢሊዮን ዶላር ሸቀጥ ላይ ታሪፍ ጥለዋል። ካናዳ በበኩሏ 20.7 ቢሊዮን ዶላር በሚጠጋ የአሜሪካ ሸቀጥ ላይ ታሪፍ ጥላለች፡፡
አውሮፓውያኑ የሚጥሉት ታሪፍ ያተኮረው እንደ ትረምፕ ባሉ ሪፐብሊካኖች ቁጥጥር ሥር ካሉ ግዛቶች በሚላኩ ሸቀጦች ላይ ነው። ከካንሳስ እና ኔብራስካ በሚላከው ሥጋና ዶሮ፣ ከአላባማ እና ጆርጂያ በሚላከው የእንጨት ውጤት፣ እንዲሁም ከኬንተኪ እና ቴነሲ በሚላከው የአልኮል መጠጥ ላይ ነው። በብረት እና አሉምነም ላይ አንዱ በሌላው ላይ በሚጥለው ታሪፍና ውዝግብ መሃል የአልኮል አምራቾችም ሰለባ ሆነዋል።
የአውሮፓ ኅብረት ለአሜሪካ ዊስኪ ትልቁ ገበያዋ ሲሆን፣ ከዚህ በፊት የነበረው ታሪፍ መነሳቱን ተከትሎ ባለፉት ሦስት ዓመታት ወደ አውሮፓ የሚላከው የአሜሪካ ዊስኪ በ60 በመቶ ጨምሮ ነበር። 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/trump-tariffs/8009704.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/trump-tariffs/8009704.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 20:34:24 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a1531c9d-c3db-422b-0e43-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት በዩክሬይን ለ30 ቀናት ተኩስ እንዲቆም የቀረበውን ሐሳብ ደገፉ</title>
            <description>ዩክሬይን ለ30 ቀናት ተኩስ እንዲቆም በቀረበው ሐሳብ እንደምትስማማ ትላንት ይፋ ማድረጓን የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት በደስታ ተቀበሉት፡፡ ቀድሞ የተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ሊቀ መንበር የነበሩት ሪፐብሊካኑ ማይክል መኮል &quot;ስምምነት ላይ መደረሱ በጣም አበረታቶኛል፡፡ አሁን ፕሬዚደንቱ የተያዘውን የስለላ መረጃ እና የጦር መሣሪያ ለመልቀቅ የወሰኑ ይመስለኛል፡፡ በጣም ትልቅ ክንዋኔ ነው&quot; ማለታቸው ተጠቅሷል፡፡
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ እና የዩክሬይን ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ በኋይት ሐውስ ኦቫል ኦፊስ የተካረረ ንግግር ማድረጋቸውን ተከትሎ ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬይን የምትሰጠውን የጦር መሣሪያ ርዳታ እና የስለላ መረጃዎች ማጋራቷን እንደምታቋርጥ ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቀች ይታወሳል። ኾኖም በቀናት የተገደበው የተኩስ ማቆም ስምምነት ይፋ ከተደረገ በኋላ፣ ከዩክሬይን ጋራ መተባበሯን እንደምትቀጥል ትላንት አስታውቃለች፡፡
ዲሞክራቱ የተወካዮች ምክር ቤት አባል ጄሰን ክሮው በበኩላቸው &quot;መጀመሪያም ቢሆን ለነጻነት፣ ለዲሞክራሲ እና ለብሔራዊ ጸጥታቸው የሚዋጉ ዩክሬይናውያንን ሕይወት አደጋ ላይ የሚጥለው ድጋፍ የማቋረጥ ርምጃ መወሰድ አልነበረበትም፡፡ ስለዚህ አሁን አስተዳደሩ እገዳውን ማንሳቱ አዎንታዊ ርምጃ ነው&quot; ብለዋል፡፡
ዩናይትድ ስቴትስ እና ዩክሪይን ሊፈራረሙ የነበረው የዩክሬይን ውድ ማዕድናት ውል ሁለቱ መሪዎች በይፋ እሰጥ አገባ ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ ሳይፈረም መቅረቱ ይታወሳል፡፡ የተወካዮች ምክር ቤት አባል ማይክል መኮል &quot; ከዚህ በኋላ እንግዲህ ፕሬዝደንት ዜሌንስኪ ወደ ኦቫል ኦፊስ ተመልሰው ይመጡና የኢኮኖሚ ትብብር ስምምነቱ ይፈረማል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ከዚያ ደግሞ ጉዳዩ በሙሉ ወደሚስተር ፑቲን ይዞራል&quot; ብለዋል፡፡
ሩሲያ በተኩስ አቁም ዕቅዱ አልተስማማችም፡፡ ፕሬዝደንት ትረምፕ በጉዳዩ ላይ የሚወያዩ ተወካዮች ወደሞስኮ መላካቸውን ትላንት አስታውቀዋል፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-congress-ukraine/8009685.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-congress-ukraine/8009685.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 20:24:40 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/3471c82e-4c7f-46c9-89af-c96f71d45c8b_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከታቀደው በላይ የቆዩትን ጠፈርተኞች ለመተካት ሊላክ የነበረው የስፔስ ኤክስ ተልእኮ ዘገየ</title>
            <description>ጠፈር ላይ ከጊዜያቸው በላይ የቆዩ የ ዩናይትድ ስቴትስ የኤሮኖቲክስ እና ጠፈር ምርምር (ናሳ) ጠፈር ተመራማሪዎችን ለመተካት ወደ  ሊላክ የነበረው የስፔስ ኤክስ መንኮራኩር የሮኬት ማስወንጨፊያ እክል ስለገጠመው ወደ ጠፈር ጣቢያው የሚያደርገው በረራ ዘግይቷል፡፡
ቡች ዊልሞር እና ሱኒ ዊሊያምስ የተባሉት ጠፈርተኞች ከዘጠኝ  ወራት  ቆይታ በኋላ ወደ ምድር ከመመለሳቸው በፊት እነሱን የሚተካ የጠፈርተኞች ቡድን ከዓለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ መድረስ ይኖርበታል፡፡
ይሁን እንጂ ከኬኔዲ የጠፈር ማእከል ሊወነጨፍ ተዘጋጅቶ የነበረውን ፋልከን ሮኬት እክል ገጥሞታል፡፡
አሶስየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ሮኬቶቹን ደግፈው ከያዙት መሳሪያዎች መካከል አንዱን የሚቆጣጠረው የማስወንጨፊያ ክፍል (የማስነሻ ፓድ)  ችግር የገጠመው መኾኑን መሀንዲሶች በመናገራቸው ስፔስ ኤክስ (SpaceX) ተልዕኮውን እንዲያዘገይ ተደርጓል፡፡
ችግሩ የታወቀው ሮኬቱ ከመወንጨፉ ከአራት ሰዐታት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ሲሆን ተልእኮ ሙሉ ለሙሉ እንዲሰረዝ የተደረገው ከመወንጨፊያ አንድ ሰዓት ያነሰ ጊዜ ሲቀረው መሆኑ ተመልክቷል፡፡
ስፔስ ኤክስ ተልእኮው እንደገና የሚጀመርበትን ቀን መቸ እንደሚኾን ባይረጋገጥም ቀጣዩ ሙከራ ኅሙስ ምሽት ሊደረግ እንደሚችል ተገልጿል ((ኤፒ)፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/https-www-voanews-com-a-launch-pad-problem-delays-spacex-flight-to-replace-nasa-s-stuck-astronauts-8009048-html/8009493.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/https-www-voanews-com-a-launch-pad-problem-delays-spacex-flight-to-replace-nasa-s-stuck-astronauts-8009048-html/8009493.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 18:18:13 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5ee089cb-5149-4b45-0757-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኩዌት ከአደገኛ ዕጽ ጋራ በተያያዘ የታሰሩ የቀድሞ ሠራዊት አባላት ጨምሮ አሜሪካዊ እስረኞችን ለቃለች</title>
            <description>ኩዌት ከአደገኛ ዕፅ ጋራ በተያያዘ ክስ ተመስርቶባቸው ለዓመታት በእስር ላይ የነበሩ የቀድሞ ሠራዊት አባላትና እና የወታደራዊ ተቋራጭ ሠራተኞችን ጨምሮ አሜሪካውያን እስረኞችን ለቃለች።
የአሜሪካ መንግሥት በውጭ ሀገር የታሰሩ አሜሪካውያንን አስለቅቆ ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ ባደረገው ጥረት የተፈቱት እስረኞች ወደ ኒውዮርክ ተወስደዋል፡፡
እስረኞቹ የተለቀቁት በቅርቡ ዋናው የትረምፕ አስተዳደር የታጋቾች ጉዳይ መጓዛቸውን ተከትሎ መኾኑም ተመልክቷል፡፡
በአሜሪካዊያን ታጋቾች እና እስረኞች ጉዳይ የሚሰሩት አማካሪው ጆናታን ፍራንክ እስር ላይ ከነበሩ ስድስት እስረኞች ጋራ በመኾን ለኩዌት መንግሥት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን “ደንበኞቼና ቤተሰቦቻቸው የኩዌት መንግሥት ላሳየው ሰብአዊነት ምስጋናቸውን ያቀርባሉ”ሲሉም በመግለጫቸው ተናግረዋል፡፡ ደንበኞቻቸው ጥፋት የሌለባቸው ንጹሐን መኾናቸውንም ፍራንክ አያይዘው ገልጸዋል።
ምንም እንኳን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስለ ሁኔታው ምንም ዐይነት አስተያየት ባይሰጥም፣ ከኩዌት እስር ቤት ተጨማሪ አሜሪካውያን እስረኞች ይፈታሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በነዳጅ የበለጸገችው እና በመካከለኛው ምስራቅ የአሜሪካ ቁልፍ አጋር የሆነችው ኩዌት፣ ጉልህ የሆነ የአሜሪካ ጦር ኅይል የሠፈረባት እና ብዙ የአሜሪካ ሥራ ተቋራጮች የሚገኙባት ሀገር ናት፡፡
ኩዌት በርካቶችን ለእስር የዳረጋቸውን ጠንካራ የአደገኛ እፅ ሕግጋትን የምታስፈጽም ሲሆን እስረኞች ላይ የተለያዩ የሰብአዊ አያያዝ በደሎች እንደሚፈጸሙ ቤተሰቦች ይናገራሉ፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኩዌት የአደገኛ እፅ ሕጎች፣ የሞት ቅጣትን ጨምሮ ረጅም እስራት እና ከባድ ቅጣት እንደሚያስከትሉ ያስጠነቅቃል፡፡
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ወደ ሥልጣን ከተመለሱ በኋላ አስተዳደራቸው ከሩሲያዊው ማርክ ፎጌል እና ከቤላሩስ የመጣውን ሌላ አሜሪካዊ ዜጋን ጨምሮ በእስር ላይ የሚገኙ በርካታ አሜሪካውያን እንዲፈቱ አድርጓል።


   የቪኦኤ ዋትስአፕ ቻናል ይከተሉ
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/kuwait-frees-a-group-of-jailed-americans-including-contractors-held-on-drug-charges/8009398.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/kuwait-frees-a-group-of-jailed-americans-including-contractors-held-on-drug-charges/8009398.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 17:03:57 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/2b3bac0b-d475-42e6-0758-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቀረጡ ጉዳይ በዩናይትድ ስቴትስ ኢኮኖሚ ላይ ያስከተለው አለመረጋጋት</title>
            <description>የቀረጡ ጉዳይ ከዋጋ ንረት ስጋት ጋራ ተዳምሮ በፈጠረው አለመረጋጋት የተነሳ ሰኞ እና ማክሰኞ የዩናይትድ ስቴትስ የአክሲዮን ገበያ አሽቆልቁሏል፡፡
በአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ እና በሕዝብ ብዛት ትልቋ የካናዳ ጠቅላይ ግዛት ኦንታሪዮ ጠቅላይ ሚንስትር ደግ ፎርድ መካከል የሁለቱን ሀገሮች የንግድ ውዝግብ በሚመለከት የተደረገውን ልውውጥ ጠቅሳ የቪኦኤ የኋይት ሐውስ ዘጋቢ ካሮላይን ፕሬሱቲ የላከችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
የቪኦኤ ዋትስአፕ ቻናል ይከተሉ 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8009199.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8009199.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 13:56:26 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0c7bb9ac-79cd-4505-0e03-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በግሪንላንድ ምርጫ ያሸነፈው ፓርቲ የትረምፕን ዕቅድ ተቃወመ</title>
            <description>በግሪንላንድ በተካሄደው የምክር ቤት ምርጫ፣ ሀገሪቱ በሂደት ከዴንማርክ ነጻ እንድትወጣ የሚደግፈው ዴሞክራቲት ፓርቲ ያልተጠበቀ ድል ተቀዳጅቷል፡፡
የትላንት ማክሰኞው ምርጫ የተካሄደው፣ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ደሴቲቱን ለመጠቅለል ያላቸውን እቅድ ይፋ ባደረጉበት ድባብ ውስጥ ነው፡፡
ዲሞክራቲት ፓርቲ “የግዛቲቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወስኑት የግሪላንድ ነዋሪዎች ናቸው” በማለት የትረምፕን ንግግር ሲቃወም ቆይቷል፡፡
“የምርጫው ውጤት ግሪንላንድ አትሸጥም የሚለውን ግልፅ መልዕክት ለትረምፕ ማስተላለፍ አለበት” ሲሉ የፓርቲው መሪ ጄንስ ፍሪደሪክ ኒልሰን ለስካይ ኒውስ ተናግረዋል።
&quot;እኛ አሜሪካዊ መሆን አንፈልግም። ፣ ዴኒሽ መኾንም አንፈልግም። የምንፈልገው ግሪንላንድነታችንን  ነው። ወደፊትም  ነፃነታችንን እንፈልጋለን። የራሳችንን ሀገር እርሳቸው በሚሰጡት ተስፋ ሳይሆን በራሳችን መገንባት እንፈልጋለን&quot; ብለዋል።
ግሪንላንድ ሞባይል ሞባይል ስልክ  እና የታዳሽ ኅይል ቴክኖሎጂን ጨምሮ   ለመሥራት  አስፈላጊ ግብዓት የኾኑ  ውድ የምድር ማዕድናት ክምችት የያዘች ናት፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ አየር ኃይል የጦር ሰፈር የሚገኝባት  ስትኾን ለሰሜን አትላንቲክ የአየር እና የባህል መስመሮች ቁልፍ የስትራቴጂ ስፍራ ናት፡፡
ትረምፕ ግሪንላንድን የመቆጣጠር ፍላጎታቸውን በግልጽ ተናግረዋል፡፡ ባለፈው ሳምንት ለዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤቶች የጋራ ጉባኤ ባሰሙት ንግግር  &quot;ዩናይትድ ስቴትስ “በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ታገኛዋለች&quot; ሲሉ ሐሳባቸውን ገልጸዋል።
56 ሺሕ የሕዝብ ብዛት ያላት ግሪንላንድ ከ300 ዓመታት በፊት የዴንማርክ ቅኝ ግዛት የነበረች ሲኾን  አሁንም የውጭ እና የመከላከያ ፖሊሲዋን የምትቆጣጠረው ዴንማርክ ነች፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8008519.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8008519.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 22:30:23 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/8231741b-316a-4e22-0b45-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>