<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>የፎቶ መድብሎች - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/3174</link>
        <description>የፎቶግራፎች ገጽ The best and awe-inspiring images and photos from across the world.</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>የፎቶ መድብሎች - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/3174</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Sat, 25 Apr 2026 04:21:14 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zrrj_eutjy" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሶማሊያ ጉብኝት አደረጉ </title>
            <description>እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ባለፈው ታኅሣሥ ወር መጀመሪያ በቱርክ ፕሬዝደንት ረሽፕ ታይፕ ኤርዶዋን አሸማጋይነት የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ የኹለቱ ሀገራት ግንኙነት እየተሻሻለ ባለበት ወቅት፣ ወደ ሞቃዲሾ ያቀኑት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በፕሬዝደንት ሐሰን ሼኽ መሐሙድና በሌሎች የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።


ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ረፋዱ ላይ ለይፋዊ ጉብኝት ሞቃዲሹ እንደደረሱ፣ የአል ሻባብ እንደኾነ የተገመተ በርካታ ዙር የሞርታር ተኩስ ወደ አውሮፕላን ማረፊያው አቅጣጫ መከፈቱን በደኅንነት ስጋት ምክንያት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ነዋሪዎች ተናግረዋል።


ቢያንስ አንዱ የሞርታር ተኩስ በአውሮፕላን ማረፊያው ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገኝ ጋራዥ ውስጥ ማረፉን ደግሞ ስሙ ያልተጠቀሰ የተቋሙ ባልደረባ ገልጿል። የሞርታር ጥቃቱን ተከትሎ የደረስ ጉዳት እንደሌለም ታውቋል።


በሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼኽ መሐሙድ አቀባበል የተደረገላቸው ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ወደ ፕሬዝደንታዊ ቤተ መንግሥት ተወስደው ሁለቱ ወገኖች ውይይት አድርገዋል።


ዛሬ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ሞቃዲሹ የገቡት ዐቢይ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል።


ሁለቱ ወገኖች ባወጡት የጋራ መግለጫ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ባለፉት ጥቂት ወራት ሲካሄዱ የቆዩ ተከታታይ ግንኙነቶች ቀጣይ መኾኑን ጠቅሰው፣ በኹለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደነበረበት የመመለሱን ሂደት ይበልጥ ያጠናክራል ሲሉ አክለዋል።


ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋራ የባሕር ሠፈር በሊዝ ለማግኘት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሟን ተከትሎ በኹለቱ ወገኖች መካከል የነበረው ግንኙነት ባለፈው አንድ ዓመት ሻክሮ ቆይቷል። ጉብኝቱ፣ 2ሺሕ 500 የኢትዮጵያ ወታደሮችን በአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ውስጥ ለማካተት የኹለቱ ሀገራት ከፍተኛ ወታደራዊ ባለሥልጣናት በቅርቡ መስማማታቸውን ተከትሎ የተደረገ ነው።


በኹለቱ ሀገራት መካከል ባለው ወታደራዊ ስምምነት መሠረትም፣ በአፍሪካ ኅብረት ከሚሳተፉት ውጪ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ወታደሮችንም በሶማሊያ ታሰማራለች፡፡


መሪዎቹ በከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች ስምምነት ላይ መደረሱን በመልካም መቀበላቸውን ባወጡት የጋራ መግለጫ አስታውቀዋል።


ሁለቱ መሪዎች በተጨማሪም “በተጠናከረ ዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ትብብር መተማመንን ማስፈን አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል” ሲል የጋራ መግለጫው አክሏል።


ዲፕሎማሲያዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ትብብርን በማሳደግ መተማመንን መገንባት እንደሚያስፈልግ ኹለቱ መሪዎች አጽንኦት መስጠታቸውንም የጋራ መግለጫው አመልክቷል።


የኢትዮጵያ ጠቅላይ ምኒስትር ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፣ሁለቱ መሪዎች ከዚህ ቀደም ካደረጓቸው ውይይቶች የቀጠለ ሰፋ ያለ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቋል።


ውይይታቸው &quot;በሰላም እና ፀጥታ፣ በኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲ እና በጋራ ሊሠሩ በሚችሉ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ላይ ያተኮረ ነበር &quot; ብሏል።


 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7991559.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7991559.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 28 Feb 2025 17:52:17 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><category>የፎቶ መድብል</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a3162224-a9e0-4efb-033f-08dd4a817621_cx0_cy9_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ ሀርሴዴ ኢሬቻ በዓል አከባበር በአዲስ አበባ እና በቢሽፍቱ </title>
            <description>ዓመታዊው የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ  በዓል ከተለያዩ የሀገርቱ ክፍሎች የመጡ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች እንደዚሁም ሌሎች ኢትዮጵያዊያን እና የውጭ አገራት ዜጎች በተገኙበት ዛሬ  መስከረም 26 ቀን 2017 ዓ/ም በደማቅ ሥነ ስርዓት ተከብሯል።


ዛሬ ማለዳ በመስቀል አደባባይ አካባቢ ባለዉ የኢሬቻ ቦታ በተከበረው በዓል ላይ የተገኙ ታዳሚዎች ወደ ከተማዋ የገቡት ከትላንት ከሰዓት አንስተዉ ነው።


ኢሬቻ አሁን የብዙ ህዝቦች መገናኛ ቦታ እየሆነ ነው ሲሉ ተሳታፊዎች ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል ።


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/addis-ababa-bishoftu--irreechaa-celebration-/7811683.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/addis-ababa-bishoftu--irreechaa-celebration-/7811683.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 06 Oct 2024 19:34:43 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a940c368-6d1f-41a5-bd71-2877fc634df6_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ባይደን በፓርቲያቸው ጉባኤ ደማቅ አቀባበል ተደረላቸው</title>
            <description></description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7750165.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7750165.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 20 Aug 2024 22:57:47 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><category>የፎቶ መድብል</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-cf92-08dcc0ce2b23_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሩሲያ በዩክሬን ዋና ከተማ ባካሄደችው የሚሳይል ጥቃት የህፃናት ሆስፒታል መታች</title>
            <description>ሩሲያ ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 1 ቀን 2016 ዓ.ም. በዩክሬን ባካሄደችው የአየር ድብደባ በዋና ከተማው የሚገኘው የህፃናት ሆስፒታል በሚሳይል መመታቱ ተገለጸ። በአየር ጥቃቱ ቢያንስ 20 ሰዎች ተገድለዋል።


የነፍስ አድን ሠራተኞች ኪቭ የሚገኘውን ኦክማትዲት የህፃናት ሆስፒታል ፍርስራሽ እየቆፈሩ መሆኑን እና የተጎጂዎች ቁጥር እስካሁን እንዳልታወቀ፣ የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ተናግረዋል።


&quot;ሩሲያ ሚሳይሎቿ የሚያርፉበትን ቦታ እንደማታውቅ ልትሆን አትችልም። ለፈጸመችው ወንጀል ሁሉ ተጠያቂ መሆን አለባት&quot; ሲሉ በኤክስ የማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው የፃፉት ዘለንስኪ፣ &quot;ዓለም በዚህ ጉዳይ ላይ ዝም ማለት የለበትም፣ ሩሲያ ምን እያደረገች እንደሆነ ማየት አለበት&quot; ብለዋል።


የኪቭ ከተማ ወታደራዊ አስተዳደር በበኩሉ በሩሲያ ጥቃት ቢያንስ ሰባት ሰዎች መገደላቸውን እና በበርካታ ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ ህንፃዎች መጎዳታቸውን ተናግረዋል።


የሩሲያ ጥቃት የዘለንስኪ የትውልድ ከተማ በሆነችው ክሪቪ ሪህ ከተማ ውስጥም ቢያንስ አስር ሰዎች መግደሉን እና ሌሎች 31 ሰዎች መቁሰላቸውን፣ የከተማዋ ወታደራዊ አስተዳደር ኃላፊ የሆኑት ኦሌክዛንደር ቪልኩል ተናግረዋል።


በምስራቃዊው የዩክሬን ክልል በምትገኘው ዶኔስክ ክልል የሚገኝ የኢንዱስትሪ ፋብሪካም በሚሳይ መመታቱን እና ቢያንስ ሦስት ሰዎች መሞታቸውን ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7689612.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7689612.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 08 Jul 2024 20:20:00 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/3a543b5d-9c5f-4586-ae86-191cfc0255bb_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በናይሮቢ ፖሊስ ለተቃውሞ የወጡ ሰልፈኞችን በአስለቃሽ ጭስ በተነ</title>
            <description>የኬንያ ፖሊስ በቅርቡ የአገሪቱ ፓርላማ ያረቀቀውን መጠነ ሰፊ የግብር ጭማሪ የሚጠይቅ ረቂቅ የፋይናንስ ሕግ ለመቃወም በወጡ ሰልፈኞች ላይ አስለቃሽ ጭስ ተኩሷል።


ሰልፈኞቹ ወደ ፓርላማ እንዳይገቡ ለማድረግ ቁጥሩ የበዛ ፖሊስ ተሰማርቷል።


የኬንያ መንግስት ሃገሪቱ ያለባትን ግዙፍ ዓለም አቀፍ ዕዳ ወለድ ክፍያ ለመቀጠል ያስፈልገኛል በሚል ያቀረበውን ረቂቅ ሕግ በመቃወም ከቅርብ ቀናት ወዲህ በወጣቶች የሚመራ የማኅበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴ በኬንያ እየጨመረ መምጣቱ ተመልክቷል።


በአንጻሩ የተቃውሞ ሰልፎቹ በአብዛኛው ሰላማዊ መሆናቸው ቢዘገብም፤ ባለፈው ሳምንት በተካሄዱ መሰል የተቃውሞ ሰልፎች ወቅት ሁለት ሰዎች መገደላቸውን ያመለከቱ አንዳንድ የሃገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች፣ “ፖሊስ በሕገ ወጥ መንገድ ሰልፈኞችን እያሰረ ነው” ሲሉ ከሰዋል።


ይህ በእንዲህ እንዳለ የሕግ አውጭዎች ቀደም ሲል በረቂቅ ሕጉ ተካተው የነበሩ በዳቦ፣ በተሽከርካሪዎች ባለቤትነት እና በግብይት ልውውጥ ላይ ሊጣሉ የታቀዱ አንዳንድ የቀረጥ ጭማሪዎችን ሰርዘዋል። የገንዘብ ሚኒስቴር በበኩሉ በረቂቅ ሕጉ ላይ የሚደረግ ለውጥ የ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የበጀት እጥረት ይፈጥራል ብሏል።


በዛሬው ዕለት በደቡብ ምስራቅ የወደብ ከተማይቱ ሞምባሳ እና በምዕራባዊቱ የኪሱሙ ከተማ ረቂቅ የፋይናንስ ሕጉን በመቃወም ሰልፎች መካሄዳቸው ታውቋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/kenya-protests-/7669748.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/kenya-protests-/7669748.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 25 Jun 2024 20:45:42 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-8987-08dc952fa00a_cx0_cy7_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የናይል ወንዝ በውድቅዳቂ ቆሻሻ ተሞልቷል</title>
            <description>በአህጉሪቱ ረዥሙ መሆኑ የሚነገርለት እና አሥራ አንድ አገሮችን አቋርጦ የሚፈሰው የናይል ወንዝ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ቁጥሩ ከ200 ሚሊዮን በላይ ለሚደርስ ሕዝብ ዘላቂ የሕይወት ዋስትና ይሰጣል። ይሁን እንጂ ከወንዙ የላይኛው ተፋሰስ አካባቢዎች የሚታየው እና እያደርም እየጨመረ የመጣው የሰዎች እንቅስቃሴ የወንዙን ሥነ-ምህዳር ለአደጋ ማጋለጡ ተዘግቧል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/africa-s-nile-river-suffocating-with-waste/7664810.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/africa-s-nile-river-suffocating-with-waste/7664810.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 21 Jun 2024 14:53:40 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><category>የፎቶ መድብል</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-3be8-08dc8b2e9032_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቡድን ሰባት አባል ሀገሮች መሪዎች ጉባዔ - ጣሊያን</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን ዛሬ ሐሙስ በጣሊያን አፑሊያ ከተማ ከቡድን ሰባት አባል ሀገሮች መሪዎች ጋር ጉባዔ ላይ ናቸው፡፡ በኢንዱስትሪ የበለጸጉት ሀገሮች መሪዎቹ አውሮፓ እና መካከለኛው ምስራቅ ውስጥ ጦርነቶች እየተካሄዱ ባሉበት በአሁኑ ወቅት ያለውን የዓለም ጸጥታ ጉዳይ ይወያያሉ፡፡ ዩናይትድ ስቴትስ እና የቻይና ፉክክርም የጉባዔው ትኩረት እነደሚሆን ተመልክቷል፡፡


መሪዎቹ ቅንጡው ጉባዔው የሚካሄድበት ቅንጡው ቦርጎ ኢኛትዚያ (Borgo Egnatzia) መዝናኛ ሲደርሱ የጣሊያን ጠቅላይ ሚንስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ተቀብለዋቸዋል፡፡ አክራሪ ቀኝ ክንፉ የሜሎኒ ፓርቲ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በተካሄደው የአውሮፓ ፓርላማ ምርጫ 29 ከመቶ ድምጽ ያገኘ ሲሆን ጠንከር ያለ ድጋፍ አግኝተው የወጡ ብቸኛዋ የዋና የምዕራብ አውሮፓ ሀገር መሪ አድርጓቸዋል፡፡


ባይደን በሌላ በኩል በድጋሚ ለመመረጥ የሪፐብሊካን ፓርቲው ዕጩ እንደሚሆኑ ከሚጠበቁት ከቀድሞው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕ ጋር ብርቱ ፉክክር ላይ ሲሆን በግልም አስቸጋሪ ጉዳይ ገጥሟቸዋል፡፡ በጣሊያኑ ጉባዔ ላይ ለመገኘት ከመነሳታቸው በአንድ ቀን ቀደም ብሎ ማክሰኞ ዕለት ልጃቸው ሀንተር ባይደን የሱስ አስያዥ ቁስ ሱሰኛ ሆነው ሳለ መሣሪያ በመግዛት ወንጀል ክስ ጥፋተኛ ተብለዋል፡፡


ያም ሆኖ ባይደን መሪዎቹን ለዩክሬይን 50 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጣት ለማግባባት ተስፋ በማድረግ ወደጉባዔው ተጉዘዋል፡፡ የቻይናን የኤሌክትሪክ መኪናዎች ጨምሮ በስትራተጂያዊ የአረንጓዴ ቴክኖሎጂ አቅም ጉዳዮች ስምምነት እንደሚደርግ ተስፋ አድርገው ተጉዘዋል፡፡ የአውሮፓ ህብረት ባይደን ጣሊያን ከመግባታቸው በአንድ ቀን ቀደም ብሎ በቻይና የኤሌክትሪክ መኪናዎች ላይ ቀረጥ በመጣል እንደሚደግፋቸው ፍንጭ ሰጥቷል፡፡


ባይደን በተጨማሪም አፍሪካ ላይ መዋዕለ ነዋይ መመደብ፡ ዓለም አቀፍ ልማት እና የአየር ንብረት ጉዳዮችን ቁልፍ አጀንዳዎቹ ላደረገው የጂዮርጂያ መሎኒ አስተዳደር ፖሊሲ ድጋፋቸውን ገልጠዋል፡፡ በጉዳዮቹ ላይ በዛሬው የጉባዔው መክፈቻ ላይ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በማስከተል የጋዛ እና የዩክሬይን ጦርነቶች ላይም ተወያይተዋል፡፡


ቀን አክራሪዋ የጣሊያን ፖለቲከኛ መሎኒ አፍሪካዊያን ፍልሰተኞች በሜዲቴራኒያን ባሕር በኩል ወደ አውሮፓ እንዳይገቡ ለመከላከል በባሕር ኅይል መርከቦች ይታጠር የሚል ጥሪ ማቅረባቸው ሲታወስ በአሁኑ ወቅት ደግሞ አፍሪካ ላይ ዓለም አቀፍ ኢንቬስትመንት በማጠናከር ያንን ግብ ለማሳካት ይፈልጋሉ፡፡


መሎኒ በርካታ የአእፍሪካ መሪዎችን በጉባዔው ላይ በታዛቢነት እንዲገኙ ጋብዘዋል፡፡ ከተጋበዙት መካከል የአልጄሪያ ፕሬዚደንት አብደልመጂድ ቴቡኒ፣ የቱኒዥያው ካይስ ሳኢድ፣ የኬኒያው ዊሊያም ሩቶ እና የሞሪታኒያው መሐመድ ኡልድ ጋዙዋኒ ይገኙባቸዋል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/biden-g-7-leaders-focus-on-ukraine-gaza-global-infrastructure-africa/7654909.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/biden-g-7-leaders-focus-on-ukraine-gaza-global-infrastructure-africa/7654909.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Jun 2024 21:14:53 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-638c-08dc8bd46eff_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ደቡብ አፍሪካ እየመረጠች ነው</title>
            <description></description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7636210.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7636210.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 28 May 2024 19:43:51 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-9379-08dc8006652b_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በፓፕዋ ኒው ጊኒ የተራራ ናዳ ከሁለት ሺሕ በላይ ሰዎችን ከነሕይወታቸው ቀበረ</title>
            <description>በፓፕዋ ኒው ጊኒ አንድ መንደር ውስጥ፣ ከሁለት ሺሕ በላይ ሰዎች ከነሕይወታቸው በተራራ ናዳ እንደተቀበሩ፣ አገሪቱ ለተባበሩት መንግሥታት ቢሮ አስታውቃለች፡፡


መንጋሎ የተሰኘው ተራራ፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ ሲናድ፣ ከሥሩ የሚገኘውን ኢንጋ መንደር ሙሉ ለሙሉ አውድሞ ነዋሪዎቿን ከነሕይወታቸው እንደቀበረ፣ ብሔራዊ የአደጋ መከላከያ ቢሮው በመዲናዋ ፖርት ሞርዝቢ ለሚገኘው የተመድ ቢሮ አስታውቋል።


ናዳው፣ በሕንጻዎች እና በሰብል ላይ ከፍተኛ ውድመት በማድረሱና ዋናው አውራ ጎዳና ሙሉ ለሙሉ በመዘጋቱ፣ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል።


ናዳው አሁንም ቀስ በቀስ መንከባለሉን በመቀጠሉ፣ በአደጋ ሠራተኞች እና ከአደጋው መውጣት በሚችሉት ላይ ስጋትን መደቀኑ ተመልክቷል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/papua-new-guinea-landslide/7629620.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/papua-new-guinea-landslide/7629620.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 28 May 2024 13:43:06 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><category>የፎቶ መድብል</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/27057755-1167-466c-a1cc-161349630e66_cx0_cy1_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢራኑ ፕሬዚዳንት በሄሊኮፕተር አደጋ ሞቱ</title>
            <description>የኢራኑ ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ ትላንት እሁድ ኢራን ውስጥ በደረሰ የኤሊኮፕተር አደጋ ሕይወታቸው አልፏል።


በአደጋው የሃገሪቱን የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሁሴን አሚራብዶላሂያንን ጨምሮ ሌሎችም ባለሥልጣናት መሞታቸው ታውቋል። ሄሊኮፕተሩ ምስራቅ ኢራን ውስጥ አዘርባይጃን በተባለ አውራጃ እንደተከሰከሰ ሲታወቅ፣ የአደጋውን ምክንያት የሃገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን አልገለፀም።


የኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ ደቀመዝሙር እንደሆኑ የሚነገርላቸው ራይሲ፣ በእ.አ.አ 1988 ዓ.ም. በኢራን በሺሕዎች በሚቆጠሩ የፖለቲካ እስረኞች፣ ተቃዋሚዎች እና አማፂያን ላይ የሞት ፍርድ ያስተላለፈው ኮሚሽን ቁልፍ ሰው እንደነበሩ ተነግሯል። በኋላም የሃገሪቱን ዩራኒየም የማበልጸግ ፕሮግራም መርተዋል።


የ63 ዓመቱ ራይሲ በእስራኤል ላይ የተፈጸሙትን ከፍተኛ ጥቃቶችን እንደመሩም ይነገርላቸዋል።


መንፈሳዊው መሪ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ ዛሬ ሰኞ ምክትል ፕሬዝደንት የነበሩትን ሞሃመድ ሞክበር ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት አድርገው ሾመዋል። አምስት የሃዘን ቀናትንም አውጀዋል።


የራይሲ ሞት የመጣው በመካከለኛው ምሥራቅ የእስራኤል እና ሐማስ ጦርነት መላ ባላገኘበት ወቅት ነው። ባለፈው ወር በእስራኤል ላይ የደረሰው የድሮን እና የሚሳዬል ጥቃት፣ በኻሚኒ መሪነት እና በራይሲ አስፈጻሚነት እንደተከናወነ ተነግሯል።


በሄሊክፕተሩ አደጋ የተረፈ ሰው እንደሌለ ኢራን በይፋ ማስታወቋን ተከትሎ፣ ጎረቤት ሃገራትና ሌሎችም የኢራን ወዳጆች የሃዘን መግለጫ መልዕክት አስተላልፈዋል።


የቻይናው ፕሬዝደንት ሺ ጂንፒንግ ሃገራቸው “ጥሩ ወዳጅ” እንዳጣች ባስተላለፉት የሃዘን መግለጫ አስታውቀዋል።


ራይሲ በሥልጣን ዘመናቸው “የኢራንን ፀጥታና መረጋጋት በመጠበቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል” ብለዋል ሺ ጂንፒንግ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7619680.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7619680.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 20 May 2024 20:43:38 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-7016-08dc78d49b98_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title> በ“ዘንባባው እሑድ” የተገለጸው የኢትዮጵያውያን የሰላም ምኞት</title>
            <description>በታላቁ ጾመ ኢየሱስ ሱባኤ ላይ የሚገኙት፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን፣ የሱባኤው ስምንተኛ ሰንበት የኾነውን የሆሳዕናን በዓል  እሑድ ዕለት አክብረዋል፡፡ የሆሳዕና በዓል በሌላ አጠራር የዘንባባው እሑድ፣ ጌታ ኢየሱስ በአህያ ጀርባ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ፣ ሕፃናት እና አዕሩግ በዘንባባ ዝንጣፊ እያመሰገኑ የተቀበሉበት ቀን ነው፡፡


የአሶሽየትድ ፕሬስ ዘጋቢ በተገኘበት የእንጦጦ ርእሰ አድባራት መንበረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓሉ ሲከበር የተገኙ ምእመናን፣ በአገራቸው ሰላም እንዲሰፍን ምኞታቸውን ገልጸዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7591684.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7591684.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 30 Apr 2024 15:43:19 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-451f-08dc690f1db5_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የፀሐይ ግርዶሽ </title>
            <description>ሜክሲኮ፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ካናዳ የፀሐይ ግርዶሽ ዛሬ ሰኞ መጋቢት 30፣ 2016 ዓ/ም ተከስቷል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7561669.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7561669.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 08 Apr 2024 22:43:03 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><category>የፎቶ መድብል</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-f89c-08dc580260cd_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በታይዋን ርዕደ መሬት 7 ሰዎች ሞቱ ከ700 በላይ ቆሰሉ</title>
            <description>ታይዋን ምስራቃዊ  ግዛት ዛሬ ረቡዕ ማለዳ ከባድ ርዕደ መሬት ደርሶ  ቢያንስ ሰባት ሰዎች ሲሞቱ ከ700 በላይ ቆስለዋል፡፡ በርዕደት መለኪያው ሪክተር ስኬል 7 ነጥብ 2 ባስመዘገበው የመሬት መናወጥ   ከባድ የኤሌክትሪክ  ኃይል መቋረጥም የደረሰ ሲሆን በርካታ ህንጻዎችም ወድቀዋል፡፡ ከታይዋን ምስራቃዊ የባህር ዳርቻ 25 ኪሎ ሜትር ርቀት ድረስ ዘልቆ ተሰምቷል የተባለው ርዕደ መሬት በሀገሪቱ በ25 ዓመታት ከደረሱት ሁሉ ከባዱ ርዕደ መሬት ነው፡፡ በርዕደ መሬቱ በማዕከላዊ ታይዋን አንድ ሕንፃ ሙሉ በሙሉ ሲወድም 15 ህንጻዎች በከፊል ወድመዋል፡፡ ሌሎች 67 የሚሆኑ ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል። በተለይ ሁዋልያን በተባለቸው የምስራቅ ታይዋን  ከተማ ብቻ  ቢያንስ 26 ህንጻዎች  ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል ሲወድቁ  ያዘመሙ ህንጻዎችም አሉ፡፡ በማሕበራዊ መገናኛዎች የወጡ ምስሎች  ሊወድቅ የደረሰ ህንጻ እንዲሁም በዋና ከተማዪቱ ታይፔይ የተነቃነቁ ህንጻዎች ጨምሮ  ከፍተኛ መዋቅራዊ ጉዳት መድረሱን አሳይተዋል፡፡ የነፍስ አድን ሠራተኞች ከህንጻዎች ፍርስራሽ ስር ተቀብረው መውጫ ያጡ ሰዎች ለማትረፍ ሲረባረቡም ታይተዋል፡፡ ተራራማ በሆኑ አውራ ጎዳናዎች ላይ ቁልቁል የተንከባለሉ ቋጥኞች  መንገድ በመዝጋታቸው በተፈጠረው የትራፊክ እክል በርካታ ሰዎች መውጫ አጥተዋል፡፡ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት በመሬት ርዕደቱ  የተበላሹ አውራ ጎዳናዎችና የባቡር ሀዲድ መስመሮችን በመጥረግ እስከ ነገ ሀሙስ ሥራ ለማስመጀር ተስፋ አድርገዋል፡፡ ብዙዎቹ ነዋሪዎች  ስለ አደጋው የደረሳቸው ማስጠንቀቂያ ባለመኖሩ በሀገሪቱ  የአደጋ ጊዜ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓት ላይ ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡ በሚቀጥሉት አራት ቀናት  ከ6.5 እስከ 7 የሚደርስ  ተከታይ ርዕደ መሬት እንደሚኖር ማዕከላዊ የአየር ሁኔታ አስተዳደር አስጠንቅቋል፡፡ በደሴቲቱ  የደረሰው ርዕደ መሬት አጎራባቾቹ ጃፓን፣ ፊሊፒንስ እና አንዳንድ የቻይና ክፍሎች ድረስ ዘልቆ የነዘራቸው መሆኑ ተሰምቷል፡፡ ታይዋንን እ.ኤ.አ. በ 1999  ዓመተ ምሕረት የመታት በሬክተር 7.6  ያስመዘገበ ርዕደ መሬት  2,400 የሚጠጉ ሰዎችን መግደሉ ይታወሳል።


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7554946.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7554946.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 03 Apr 2024 20:07:27 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><category>የፎቶ መድብል</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a83b1afd-da07-4dbc-a7d2-9f5156dd9b71_cx0_cy4_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የጥምቀት ከተራ በዓል በአዲስ አበባ</title>
            <description>የጥምቀት ከተራ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ በኃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች ተከብሯል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7456919.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7456919.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 19 Jan 2024 18:49:00 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><category>የፎቶ መድብል</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-9549-08dc1dbc4dc8_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የእስራኤል ጦር በሀገሪቱ ግዛት ውስጥ የቀሩትን የሀማስ ተዋጊዎች ጠራርጎ ለማስወጣት እየሠራ እንደኾነ አስታወቀ </title>
            <description></description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7301866.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7301866.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 08 Oct 2023 19:51:00 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብል</category><category>የፎቶ መድብሎች</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-c0a8-0242-1915-08dbc80ae9f0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>78ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ድባብ </title>
            <description> 


ከ190 በላይ ሀገራት መሪዎች የሚሳተፉበት ዓመታዊ ጉባዔ የምታስተናግደው ኒው ዮርክ ከተማ ከጥብቅ የጸጥታ ሥምሪት ጋር መሪዎቹን እያስተናገደች ትገኛለች።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7281223.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7281223.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 23 Sep 2023 23:09:21 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><category>የፎቶ መድብል</category><category>የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-2c3c-08dbbc6e9c33_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሞሮኮ የደረሰው የመሬት መንቀጥቅጥ አደጋ </title>
            <description></description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7266752.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7266752.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 13 Sep 2023 21:31:06 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><category>የፎቶ መድብል</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5751ddff-ecd1-4a39-81c7-80aac7ae41e9_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የማንዴላ ዋሺንግተን የወጣት አፍሪካዊያን መሪዎች የትስስር መርሐ-ግብር</title>
            <description>
በዋሺንግተን ዲሲ በመከናወን ላይ ይገኛል። ከሰሃራ በታች ከሚገኙ የአፍሪካ ሀገራት ማህበረሰብ አጋዥ ፈጠራዎች እና የላቁ ሀሳቦችን ይዘው ብቅ ያሉ ከ700 በላይ ወጣት መሪዎች በዘንድሮው መርሐ-ግብር ተሳታፊ ናቸው።



መርሀ-ግብሩ በአውሮፓዊያኑ 2014 የተጀመረ ሲሆን ፣ ከብዙ ሺ አመልካቾች መካከል የተመረጡ ወጣቶች በዩናይትድ ስቴትስ ለስድስት ሳምንታት የቀለም ትምህርት እና አመራር ክህሎት ስልጠና እንዲያገኙ ከማስቻሉ በተጨማሪ የርስ በርስ ትስስር አፍታዎችን ያመቻቻል።



ከስር የተያያዙት ምስሎች የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ከፍተኛ ኃላፊዎች እና ስኬታማ ወጣት አፍሪካዊ አሜሪካዊያን ከተሳተፉበት የመክፈቻው ቀን ሥነ-ሥርዓት ላይ የተወሰዱ ናቸው።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7206928.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7206928.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 01 Aug 2023 18:43:51 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><category>የፎቶ መድብል</category><category>ያሊ 2023</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-51af-08db92a4a60b_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ለአፍሪካ ሩሲያ ጉባኤ የአህጉሪቱ መሪዎች ፒተርስበርግ መግባት ጀመሩ</title>
            <description>የአፍሪካ መሪዎች፣ ከሁለተኛው የሩሲያ - አፍሪካ ጉባኤ እና የኢኮኖሚ ፎረም አስቀድመው፣ ዛሬ ረቡዕ፣ ቅዱስ ፒተርስበርግ መግባት እንደ ጀመሩ ተነገረ፡፡


የምግብ ደኅንነት እና የቫግነር ወታደራዊ ቡድን የወደፊት ዕጣ፣ የጉባኤው ከፍተኛ አጀንዳ ይኾናል፤ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነግሯል፡፡


የፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን መንግሥት፣ በዓለም አቀፉ መድረክ ተሰሚነቱ እየጨመረ ለመጣውና 1ነጥብ3 ቢሊዮን ለሚደርሰው፣ የአፍሪካ አህጉር ሕዝብ ወዳጅነት ያለውን ቁርጠኝነት ማሳየት ይኖርበታል፤ ተብሏል፡፡


ለሩሲያ ጥሩ አቀባባል ከሚያሳየው የዓለም ክፍልም፣ አገሪቱ ተጨማሪ አጋሮችን እንደምትሻ ተገልጿል፡፡


የአፍሪካ መሪዎች ልኡካን ቡድን፣ በሩሲያ - ዩክሬኑ ጦርነት ሰላም እንዲመጣ፣ ባለፈው የተጓዙበትን የማደራደር ውጥን፣ በድጋሚ ሊሞክሩት ይችላሉ፤ የሚል ግምት መኖሩም ተመልክቷል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7202450.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7202450.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 27 Jul 2023 21:48:00 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብሎች</category><category>የፎቶ መድብል</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0a00-0242-5ae3-08db8f9ab691_cx1_cy1_cw98_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሕንድ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ16 ሰዎች ሕይወት ጠፋ፤ ፍለጋው ቀጥሏል</title>
            <description>በሕንድ፣ በሳምንቱ ውስጥ ከባድ ዝናም መጣሉን ተከትሎ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ፣ 16 ሰዎች መሞታቸውን ተከትሎ፣ የአደጋ ሠራተኞች፣ አሁንም ከነሕይወታቸው በናዳ የተቀበሩ ሰዎችንና አስከሬኖችን ለማውጣት በፍለጋ ላይ ናቸው።


ናዳው፣ ራይጋድ በተሰኘው አውራጃ ከደረሰ በኋላ፣ 75 ሰዎችን በሕይወት ማውጣት እንደተቻለ፣ ባለሥልጣናት ተናግረዋል። ሌሎች በሕይወት ያሉ ሰዎች እና አስከሬኖች፣ አሁንም በፍርስራሹ ውስጥ ሳይኖሩ አይቀሩም፤ በሚል ፍለጋው ቀጥሏል።


በትላንትናው ዕለት በጣለው ከባድ ዝናም ምክንያት፣ ሌላ አደጋ እንዳይከሠት በመስጋት፣ ፍለጋው ተቋርጦ ነበር። በአደጋው አካባቢ ከሚገኙ 50 ቤቶች ውስጥ 17 የሚኾኑት፣ በመሬት መንሸራተቱ ተቀብረዋል፤ ሲሉ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።


በሕንድ፣ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ብቻ፣ ከ100 በላይ ሰዎች፣ ከባድ ዝናም በአስከተለው አደጋ ሕይወታቸው አልፏል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7190811.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7190811.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 21 Jul 2023 20:30:18 +0300</pubDate>
            <category>የፎቶ መድብል</category><category>የፎቶ መድብሎች</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-c0a8-0242-eddf-08db89b49628_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>