<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>የዓለም የስደተኞች ቀን - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/7510</link>
        <description>world refugee day 2023</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>የዓለም የስደተኞች ቀን - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/7510</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Wed, 08 Apr 2026 19:11:22 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zrbjqil-vomx-tpeovrom" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>በስደተኛ ካምፕ ያደገው ሶማልያዊው ጋዜጠኛ በኬንያ</title>
            <description>ሕይወት በኬኒያ ካምፖች፣ በሶማልያዊው ስደተኛ ጋዜጠኛ ሲቃኝ።


አደን አብዱላሂ፣ በኬኒያ ዳዳብ ስደተኛ ካምፕ ሲያድግ፣ ብዙ ፈተናዎችን አሳልፏል። ከሀገሩ ከሶማሊያ ወደ ኬንያ ለመሰደድ ያደረሰው፣ ጽንፈኛው እስላማዊ ታጣቂ ቡድን አልሻባብ ሊመለምለው ሲያግባባው፣ አሻፈረኝ ብሎ ነው።


ዛሬ፣ አደን ጋዜጠኛ ነው። “ራዲዮ ጋርጋር” በሚባል፣ ትኩረቱን በስደተኛው ማኅበረሰብ ላይ ያደረገ፣ በተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር የሚደገፍ የራዲዮ ጣቢያ ውስጥ ይሠራል።


የዛሬውን፣ የዓለም የስደተኛ ቀን ምክንያት በማድረግ፣ ጁማ ማጃንጋ፣ አደን አብዱላሂን፥ ስለ ሥራው እና ምን ሕልም እንዳለው በመጠየቅ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፍይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/kenya-refugee-journalist-pkg-mp4/7147112.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/kenya-refugee-journalist-pkg-mp4/7147112.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 21 Jun 2023 22:02:20 +0300</pubDate>
            <category>ቪድዮ</category><category>የቪዲዮ ዘገባ</category><category>የዓለም የስደተኞች ቀን</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-59a1-08db7289c626_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አሜሪካ የስደተኞች ቅበላ ፕሮግራሟን በማዘመን ድጋፏን እንደምትቀጥል ብሊንከን ገለጹ</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ፣ ላለፉት አምስት ዐሥርት ዓመታት ያህል የዘለቀውንና ከሦስት ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ስደተኞችን በመቀበል ሕይወታቸውን የታደገችበትን የደግነት ባህሏን በማዘመን፣ አሜሪካኖች፥ በግል ስደተኞችን የሚቀበሉበት ዐዲስ ፕሮግራም፣ በዚህ ዓመት ተግባራዊ ማድረጓን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን አስታወቁ፡፡


ትላንት የተከበረውን፣ “የዓለም ስደተኞች ቀን” በማስመልከት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ባወጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ “በሚደረግባቸው ጫና እና ግፊት ምክንያት፣ አገራቸውን ጥለው በሌሎች አገሮች የሚገኙ፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ስደተኞች ለሚያሳዩት፣ ፈተናን የመቋቋም ጽናት እና ከችግር መልሶ የመውጣት ብቃት፣ እንዲሁም ተቀባይ ማኅበረሰቦች ለሚያሳዩት ደግነት እና ዓለም ለሰጣቸው ምላሽ፣ እንዲሁም ሰብአዊ አጋሮቻቸው ለሰጧቸው ድጋፍ፣ እውቅና እንሰጣለን፤”...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7146981.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7146981.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 21 Jun 2023 20:57:11 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>የዓለም የስደተኞች ቀን</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/19e53ca2-7fb6-4208-af15-1e6b479a8af1_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በዓለም ትልቋ የፍልሰተኞች መጠጊያ ቱርክ ጫናው እየተሰማት ነው</title>
            <description>ቱርክ፣ ከሶሪያው የእርስ በርስ ጦርነት የሸሹ፣ ሦስት ሚሊዮን ሶሪያውያንን ጨምሮ፣ ከየትኛውም አገር የበለጠ ቁጥር ያላቸውን ፍልሰተኞች ቁጥር አስጠግታ እያኖረች ትገኛለች፡፡


ሥሉስ የተመረጡት የቱርክዬ ፕሬዚዳንት ረሲፕ ታዪፕ ኤርዶዋን፣ ሕዝባዊ ተቃውሞ እየበረታባቸው ቢኾንም፣ በዋናነት ከሶሪያ የሚመጡ አእላፋት ፍልሰተኞችን ተቀብለው በማሳደር ፖሊሲያቸው ጸንተዋል።


ወደ ቱርክ የተሰደዱት ዐያሌ ሶሪያውያን ፍልሰተኞች፣ ከቤት እና ከአገራቸው በላይ የኾነን ነገር አጥተዋል፡፡ በመጀመሪያው ስሙ ብቻ መጠራት የመረጠውን የ18 ዓመቱ ሰሚርን፣ የእርስ በርስ ጦርነቱ እግሩን ብቻ አይደለም ያሳጣው፤ ወላጆቹን ከአራት ወንድሞቹ እና እህቶቹ ጋራ ነጥቆታል፡፡


ይኹን እንጂ፣ “ለእግዚአብሔር ምስጋና ይድረሰውና በሁሉም ነገር ረድተውኛል፤” የሚለው ሰሚር፣ “ሁሉም ነገር ጥሩ ነው፤ እግዜር...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/turkey-world-s-biggest-refugee-host-feels-the-pressure/7146583.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/turkey-world-s-biggest-refugee-host-feels-the-pressure/7146583.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 21 Jun 2023 17:07:48 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><category>የዓለም የስደተኞች ቀን</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-8bdd-08db726014b5_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የስደት ሁኔታዎች እና የጥበቃ መብቶች</title>
            <description>በየዓመቱ እ.አ.አ ሰኔ 20 ቀን ታስቦ የሚውለው “የዓለም የስደተኞች ቀን”፣ በዓለም ዙሪያ ስደተኞች ስላሉበት ሁኔታ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ የሚሠራበት ነው፡፡ የመጀመሪያው የዓለም የስደተኞች ቀን እ.አ.አ በ2001 ሲታሰብ፣ የ1951ዱን፣ “ከስደተኞች ጋራ የተያያዙ ጉዳዮች ኮንቬንሽን” 50ኛ ዓመት መታሰቢያ በማክበር ነበር፡፡


የ1951ዱ የስደተኞች ጉዳይ ስምምነት፣ “ስደተኛ” ማለት ምን ማለት እንደኾን በይኗል፡፡ ጥገኝነት የሚሰጣቸው ግለሰቦች፣ የሚገቧቸውን መብቶች እና ጥገኝነት ሰጪዎቹ ሀገራት ያሉባቸውን ሓላፊነቶች ዘርዝሯል፡፡


ስደተኛ


እ.አ.አ በ1951 በተፈረመው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስምምነት መሠረት፣ ስደተኛ ማለት፣ ከሀገሩ፥ በዘሩ፣ በሃይማኖቱ፣ በትውልድ ቦታው፣ በአባልነት በሚሳተፍበት ማኅበራዊ ቡድን ወይም በፖለቲካ አመለካከቱ ምክንያት በሚሰማው...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7146573.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7146573.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 21 Jun 2023 16:55:43 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>የኢትዮጵያ የስደት ቀውስ</category><category>የዓለም የስደተኞች ቀን</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-47da-08db725eaacf_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሊቢያ 165 ናይጄሪያውያን ፍልሰተኞችን ወደ አገራቸው መለሰች</title>
            <description>ሊቢያ፣ ትላንት ማክሰኞ፣ 165 ናይጄሪያውያንን ወደ አገራቸው መልሳለች፡፡ ይኸው ርምጃ፣ አገሪቱ ሰሞኑን የጀመረችውና ሕገ ወጥ ፍልሰተኞችን ወደ አገራቸው የመመለስ ዘመቻ አካል ነው፤ ተብሏል።


የዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት(IOM)፣ ፍልሰተኞቹን የመመለስ ሒደቱን እንደሚቆጣጠር፣ የአሶሺዬትድ ፕረስ ዘገባ አመልክቷል። 165ቱም ፍልሰተኞች፣ ሴቶች እንደኾኑም ታውቋል። የፍልሰት ድርጅቱ፣ አንዳንዶቹ ሴቶች፥ በመንገድ ላይ ልመና ተሠማርተው ነበር፤ ብሏል።


ባለሥልጣናቱ፣ ሌሎችንም የናይጄሪያ ፍልሰተኞች፣ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ አገራቸው እንደሚመልሱ ተናግረዋል። 


አፍሪካውያን ፍልሰተኞች፣ የሜዲትሬንያን ባሕርን አቋርጦ ወደ አውሮፓ ለመዝለቅ፣ ሊቢያን እንደ መነሻ ይጠቀማሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/libya-resumes-deportation-of-165-migrants/7146561.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/libya-resumes-deportation-of-165-migrants/7146561.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 21 Jun 2023 16:45:53 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>የዓለም የስደተኞች ቀን</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-c0a8-0242-52c7-08db725d989a_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሱዳናውያን ጦርነትን ሽሽት ወደ ኬንያ በሺሕዎች እየጎረፉ ናቸው</title>
            <description>በሺሕ የሚቆጠሩ ሱዳናውያን፣ ጦርነትን ሽሽት አገራቸውን ጥለው መውጣታቸውን ቀጥለዋል። አብዛኞቹ ሱዳናውያን፣ ወደ ደቡብ የሚወስደውን መንገድ ይዘው ወደ ኬንያ በመጉረፍ ላይ ናቸው።


ዕድለኛ የኾኑቱ ወዳጆቻቸው ሲያስጠልሏቸው፣ የሚበዙት ግን፣ ዳዳብ ተብሎ በሚጠራው የስደተኞች መጠለያ ለመቆየት ተገደዋል።


ጫናው ቢከብዳባትም፣ ኬንያ፣ ስደተኞቹን ማስተናገድም ኾነ ጦርነቱን ለማስቆም ጥረት ማድረጓ፣ ከአገሪቱ ጥቅም አንጻር እንደሚታይ ተንታኞች ይናገራሉ።


ቪክቶርያ አሙንጋ ከናይሮቢ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7145586.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7145586.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 21 Jun 2023 00:47:22 +0300</pubDate>
            <category>አፍሪካ</category><category>የዓለም የስደተኞች ቀን</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-b986-08db71d58999_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዓመታዊው የዓለም የስደተኛ ቀን እየተከበረ ነው</title>
            <description>ዛሬ፣ እ.አ.አ ሐምሌ 20 ቀን፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓመታዊው የዓለም የስደተኞች ቀን ነው። በዓለም ዙሪያ፣ ከግጭቶች እና ከሌሎችም ስጋቶቻቸው ከለላ ፍለጋ፣ አገራቸውን ጥለው ለወጡ ከ35 ሚሊዮን በላይ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች መፍትሔ ይፈለግላቸው ዘንድ፣ የመንግሥታቱ ድርጅት ባለሥልጣናት ተማጥኖ አቅርበዋል።


ስደተኞችን፣ በጥላቻ ዓይን ማየት እየጨመረ ባለበት በዚኽ ወቅት፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፥ በጦርነት፣ በመሳደድ፣ በሰብአዊ መብቶች ረገጣ፣ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በሌላም መከራ ምክንያት፣ ለስደት ስለተዳረጉ ሰዎች ጽናት እና ኅብረተሰባዊ አስተዋፅኦ ትኩረት በመስጠት፣ የዛሬውን የዓለም የስደተኞች ቀን በማክበር ላይ ነው።


የዘንድሮው የዓለም የስደተኞች ቀን፣ በዓለም ዙሪያ የመከራ ኑሮ እየገፉ ለሚገኙት፣ ከ35ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ስደተኞች...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7145576.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7145576.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 21 Jun 2023 00:00:49 +0300</pubDate>
            <category>ዓለምአቀፍ</category><category>የዓለም የስደተኞች ቀን</category><author> voadigital@voanews.com (ሊሳሽ ላይን, ቆንጂት ታየ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-c0a8-0242-38d9-08db71cabb82_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ለቀንዱ ስደተኞች ኹነኛ መፍትሔ እንዲፈለግ ተጠየቀ</title>
            <description>በአፍሪካ ቀንድ እና በምሥራቅ አፍሪቃ ያሉት፣ ቁጥራቸው 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን የሚደርሱ ስደተኞች፣ የቀጣናውን ሀገራት ተፈናቃዮች ለማስተናገድ እና ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት፣ ወደ ውስጣቸው ይመለከቱ ዘንድ ፍላጎታቸውን እየገለጡ ነው።


ሆኖም፣ በዩጋንዳዋ ዋና ከተማ ካምፓላ የተጀመረው እና ለአንድ ሳምንት የሚዘልቀው ጉባኤ ተሳታፊ ልዑካን፣ እንደ አለመቻቻል፣ አላዋቂነት እና የፖለቲካ ግጭት ያሉ ፈተናዎችን፣ በመንሥኤነት ይጠቅሳሉ።


ሃሊማ አቱማኒ ከካምፓላ ያጠናቀረችው ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/amh-wrd23-horn-of-africa-refugees-pkg-updated/7143644.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/amh-wrd23-horn-of-africa-refugees-pkg-updated/7143644.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 19 Jun 2023 20:04:27 +0300</pubDate>
            <category>ቪድዮ</category><category>የቪዲዮ ዘገባ</category><category>የዓለም የስደተኞች ቀን</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-c9cb-08db70e3ccca_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>