<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>አሜሪካ - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/7511</link>
        <description>America News and Features </description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>አሜሪካ - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/7511</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Wed, 08 Apr 2026 19:11:23 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zqbjqpl-vomx-tpeivro_" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>ትረምፕ ከአውሮፓ በሚገቡ የአልኮል መጠጦች ላይ ከበድ ያለ ታሪፍ እንደሚጥሉ አስታወቁ</title>
            <description>የአውሮፓ ኅብረት ከአሜሪካ በሚገባው ዊስኪ ላይ የ50 በመቶ ታሪፍ መጣሉን ተከትሎ፣ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ከአውሮፓ በሚገባው የወይን ጠጅ፣ ሻምፓኝና ሌሎች የአልኮል መጠጦች ላይ የ200 በመቶ ታሪፍ እንደሚጭኑ አስጠንቅቀዋል።
የ27 ሃገራት ስብስብ የሆነውን የአውሮፓ ኅብረት &quot;በዓለም የከፋው ታክስና ታሪፍ ጣይ&quot; ሲሉ የገለጹት ትረምፕ፣ &quot;እ.አ.አ በ1993 ሲመሠረት ዓላማው &quot;ከአሜሪካ የኢኮኖሚ ጥቅም ለማግኘት ነው&quot; ብለዋል። 
ባለፈው አንድ ወር ከአሜሪካ ከፍተኛ የንግድ ሸሪኮች፣ ማለትም ከሜክሲኮ፣ ካናዳ፣ ቻይናና የአውሮፓ ኅብረት ጋራ የታሪፍ ውዝገብ ውስጥ የገቡት ትረምፕ፣ ታሪፉን መጣሉ አስፈላጊ የሆነው ሃገራቱ ወደ አሜሪካ የሚገባውን አደገኛ  ዕጽ እና መድሃኒት እንዲያስቆሙና እንዲሁም የሸቀጥ አምራቾች በውጪ ያላቸውን ፋብሪካ ዘግተው ወደ አሜሪካ እንዲመጡ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/trump-tariffs/8009704.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/trump-tariffs/8009704.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 20:34:24 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a1531c9d-c3db-422b-0e43-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት በዩክሬይን ለ30 ቀናት ተኩስ እንዲቆም የቀረበውን ሐሳብ ደገፉ</title>
            <description>ዩክሬይን ለ30 ቀናት ተኩስ እንዲቆም በቀረበው ሐሳብ እንደምትስማማ ትላንት ይፋ ማድረጓን የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት በደስታ ተቀበሉት፡፡ ቀድሞ የተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ሊቀ መንበር የነበሩት ሪፐብሊካኑ ማይክል መኮል &quot;ስምምነት ላይ መደረሱ በጣም አበረታቶኛል፡፡ አሁን ፕሬዚደንቱ የተያዘውን የስለላ መረጃ እና የጦር መሣሪያ ለመልቀቅ የወሰኑ ይመስለኛል፡፡ በጣም ትልቅ ክንዋኔ ነው&quot; ማለታቸው ተጠቅሷል፡፡
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ እና የዩክሬይን ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ በኋይት ሐውስ ኦቫል ኦፊስ የተካረረ ንግግር ማድረጋቸውን ተከትሎ ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬይን የምትሰጠውን የጦር መሣሪያ ርዳታ እና የስለላ መረጃዎች ማጋራቷን እንደምታቋርጥ ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቀች ይታወሳል። ኾኖም በቀናት የተገደበው የተኩስ ማቆም ስምምነት ይፋ ከተደረገ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-congress-ukraine/8009685.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-congress-ukraine/8009685.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 20:24:40 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/3471c82e-4c7f-46c9-89af-c96f71d45c8b_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከታቀደው በላይ የቆዩትን ጠፈርተኞች ለመተካት ሊላክ የነበረው የስፔስ ኤክስ ተልእኮ ዘገየ</title>
            <description>ጠፈር ላይ ከጊዜያቸው በላይ የቆዩ የ ዩናይትድ ስቴትስ የኤሮኖቲክስ እና ጠፈር ምርምር (ናሳ) ጠፈር ተመራማሪዎችን ለመተካት ወደ  ሊላክ የነበረው የስፔስ ኤክስ መንኮራኩር የሮኬት ማስወንጨፊያ እክል ስለገጠመው ወደ ጠፈር ጣቢያው የሚያደርገው በረራ ዘግይቷል፡፡
ቡች ዊልሞር እና ሱኒ ዊሊያምስ የተባሉት ጠፈርተኞች ከዘጠኝ  ወራት  ቆይታ በኋላ ወደ ምድር ከመመለሳቸው በፊት እነሱን የሚተካ የጠፈርተኞች ቡድን ከዓለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ መድረስ ይኖርበታል፡፡
ይሁን እንጂ ከኬኔዲ የጠፈር ማእከል ሊወነጨፍ ተዘጋጅቶ የነበረውን ፋልከን ሮኬት እክል ገጥሞታል፡፡
አሶስየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ሮኬቶቹን ደግፈው ከያዙት መሳሪያዎች መካከል አንዱን የሚቆጣጠረው የማስወንጨፊያ ክፍል (የማስነሻ ፓድ)  ችግር የገጠመው መኾኑን መሀንዲሶች በመናገራቸው ስፔስ ኤክስ (SpaceX) ተልዕኮውን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/https-www-voanews-com-a-launch-pad-problem-delays-spacex-flight-to-replace-nasa-s-stuck-astronauts-8009048-html/8009493.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/https-www-voanews-com-a-launch-pad-problem-delays-spacex-flight-to-replace-nasa-s-stuck-astronauts-8009048-html/8009493.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 18:18:13 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5ee089cb-5149-4b45-0757-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዩክሬን ሩሲያ አስቸኳይ የ30-ቀናት ተኩስ አቁም ተከትሎ የቡድን 7 ሀገራት ይወያያሉ</title>
            <description>በኢንዱስትሪ የበለጸጉ የቡድን 7 ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ የሦስት ዓመቱን የሩሲያ ወረራ እየመከተች ላለችው ዩክሬን የሚሰጡትን ድጋፍ ጨምሮ፣ በተለያዩ ጉዳዮች ለበርካታ ቀናት ለመምከር፣ በኩቤክ ካናዳ ይሰበሰባሉ፡፡  
ውይይቱ ዩክሬን እና አሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በሳዑዲ አረቢያ ጂዳ ከተገናኙ በኋላ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬን የምታደርገውን የመረጃ ልውውጥ እና የፀጥታ ድጋፍ እንድምትቀጥል ያሳለፈችውን ውሳኔ ተከትሎ ነው።
ዩክሬን ከሩሲያ ጋራ በሚደረገው ጦርነት “የ30 ቀን አስቸኳይ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም” የሚለውን የአሜሪካ ሐሳብ ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን ትላንት ማክሰኞ አስታውቃለች።
የጀርመኑ መሪ ቻንስለር ኦላፍ ሾልዝ ትላንት ረቡዕ ኤክስ በተሰኘ ገጻቸው እንደተናገሩት “ለዩክሬን ፍትሃዊ ሰላም ወሳኝ እና ትክክለኛ ርምጃ ነው” በማለት የ30 ቀን የተኩስ አቁም...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ubio-ukraine-g7/8008072.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ubio-ukraine-g7/8008072.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 17:36:17 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/c395cd8a-ce8a-4186-9789-c2a0489e14ad_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቡና ስርቆት በአሜሪካ</title>
            <description>በአሜሪካ የጭነት ተሽከርካሪዎች ኩባንያ መስሎ በመቅረብ በቡና ላይ የሚፈጸም ዝርፊያ በመጨመር ላይ ነው።
አሜሪካ በዓለም ከፍተኛ ቡና አስገቢ ሀገር ስትሆን፣ ባለፈው አንድ ዓመት ከዚህ በፊት ታይቶ በማያውቅ መጠን ዋጋው አሻቅቧል።
ጉዳዩ ሂውስተን ውስጥ በተካሄደው የአሜሪካ ብሔራዊ የቡና ማኅበር ዓመታዊ ኮንፈረንስ ላይ መነጋገሪያ ሆኗል።
ቡና ሞቃታማ የአየር ንብረት ባላቸው ሀገራት የሚመረት በመኾኑ፣ በዓለም ቀዳሚ ቡና ጠጪ የሆነችው አሜሪካ ምርቱን መቶ በመቶ ከውጪ ለማስመጣት ተገዳለች፡፡ ምርቱ በአብዛኛው ከወደብ ወደ ቡና መቁያ ፋብሪካዎች የሚጓጓዘው በጭነት መኪና ነው።
የዋጋውን መወደድ ያዩ ዘራፊዎች ታዲያ የጭነት ኩባንያ በመምሰል ቀርበው ቡናውን ጭነው ይሰወራሉ።
ባለፈው አንድ ዓመት በደርዘን የሚቆጠሩ የጭነት መኪኖች ቡና ይዘው ተሰውረዋል።
ቡና አምራች በሆኑ እንደ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/coffee-theft-surges-in-the-us-as-prices-for-the-beans-soar/8007651.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/coffee-theft-surges-in-the-us-as-prices-for-the-beans-soar/8007651.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 11:38:18 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a50c2c11-5831-476f-bd64-267470295a76_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አሜሪካ ለዩክሬን የምትሰጠውን የስለላ መረጃ እና የፀጥታ እርዳታ እንደገና ጀመረች</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ እና የዩክሬን ባለስልጣናት ማክሰኞ በሳዑዲ አረብያ፣ ጅዳ ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ፣ የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በዩክሬን የስለላ መረጃ ማጋራት ላይ ጥሎት የነበረውን እገዳ እንደሚያነሳ እና ለዩክሬን የፀጥታ ድጋፍ መስጠት እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአሜሪካ ባለስልጣናት በሚቀጥሉት ቀናት ከሩሲያ ባለስልጣናት ጋር እንደሚነጋገሩ ይጠበቃል። የትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮቭ በዚህ ሳምንት ከሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በሞስኮ ይገናኛሉ ተብሏል። 
ስምንት ሰዓት ከፈጀ ንግግር በኃላ ዩክሬን ከሩሲያ ጋር በምታካሂደው ጦርነት &quot;አስቸኳይ የ30-ቀናት ተኩስ አቁም&quot; ለማድረግ ዩናይትድ ስቴትስ ያቀረበችውን ሃሳብ ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን ያስታወቀች ሲሆን፣ ክሬምሊንም ሀሳቡን መቀበል ይኖርበታል። 
የካቲት 26፣ 2017...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8007708.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8007708.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 05:34:42 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/c1389bad-4a73-4e8b-0c64-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዶናልድ ትረምፕ የክሪፕቶ ግብይት እና ዲጂታል ሀብትን በተመለከተ ከመስኩ መሪዎች ጋራ ምክክር አደረጉ</title>
            <description>ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ በክሪፕቶ ግብይት መሪ የኾኑ ግለሰቦችን ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በዋይት ሐውስ ጋብዘው ዲጂታል ሀብት መገንባትን በተመለከተ ምክክር አድርገዋል። ፕሬዝደንቱ የቢትኮይን ሀብት ክምችትን ለመፍጠር ያላቸውን ፍላጎት በተመለከተም ተወያይተዋል።
“አንዳንዶቻችሁ ሰዎች ስለ ጉዳዩ ምንም በማያውቁበት ወቅት ለረዥም ጊዜ ስትሠሩ ቆይታችኋል። እናም እንኳን ደስ አላችሁ እላለሁ። ይህ ትልቅ ቀን ነው” ብለዋል ትረምፕ፡፡
ስብሰባው አሜሪካ በክሪፕቶ መገበያያ ላይ ያላትን የፖሊሲ ለውጥ ያመለከተ ነው። የመስኩ መሪዎች በቀድሞው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን አስተዳደር ወቅት የነበሩ ደንቦችን በተመለከተ ቅሬታ ሲያሰሙ ቆይተዋል።
ትረምፕ በምርጫ ዘመቻቸው ወቅትም ክሪፕቶን እንደሚያሳድጉ ቃል ገብተው ነበር። የመስኩ ባለሀብቶችም ለምርጫ ዘመቻቸውና ለበዓለ ሲመታቸው በሚሊዮን ዶላር...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-crypto-summit/8007412.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-crypto-summit/8007412.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 03:04:30 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/8de60fd5-7ed3-4fa5-0cae-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የአሜሪካ አክሲዮን ገበያዎች አሽቆልቁለው አደሩ</title>
            <description>በአሜሪካ የሚገኙ ሦስቱም ዋና የአክሲዮን ገበያዎች ትላንት ሰኞ በከፍተኛ ደረጃ አሽቆልቁለው አድረዋል። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ በአሜሪካ የንግድ ሸሪኮች ላይ በጣሉት ታሪፍ እንዲሁም በሚቀጥሉት ወራት ኢኮኖሚው እንደማይዳከም ማስተማመኛ አለመስጥታቸው ኢንቨስተሮችን ያሳሰበ ጉዳይ ሆኗል።
በዳው ጆንስ የአክሲዮን ገበያ የነበሩ 30 ብሉ ቺፕስ አክሲዮኖች በ2.1 በመቶ  ሲያሽቆለቁሉ፣ የስታንዳርድ ኤንድ ፑር 500 (ኤስ ኤንድ ፒ 500) ደግሞ በ2.7 በመቶ ወርዷል። በአብዛኛው ቴክኖሎጂ ነክ አክሲዮኖችን የያዘው ናስዳክ ደግሞ በ4 በመቶ ዝቅ ብሏል።
ኤስ ኤንድ ፒ 500 ከአንድ ወር በፊት ከነበረበት ከፍተኛ ሽያጭ በ8.6 በመቶ ወርዷል። ናስዳክ ደግሞ ከመስከረም 2014 ዓ/ም ወዲህ በአንድ ቀን ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ሲያሽቆለቁል ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።
የትረምፕ ታሪፍ መጫን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/wall-street-jitters-us-stocks-plunge-amid-gloomy-economic-outlook/8007222.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/wall-street-jitters-us-stocks-plunge-amid-gloomy-economic-outlook/8007222.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 23:00:56 +0300</pubDate>
            <category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/30c46067-e2d2-4625-3068-08dd5c897904_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የምስጋና እና አንድነት ኢፍጣር በአሜሪካ</title>
            <description>ከዋሺንግተን ዲሲ እና ከአቅራቢያው ግዛቶች የተሰባሰቡ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዓመታዊውን የ&quot;ምስጋና እና አንድነት ኢፍጣር&quot;  በቨርጂኒያ አካሒደዋል። 
የእስልምና እምነት ተከታዮች በአንድ ስፍራ ተገናኝተው  ማዕድ በተጋሩበት ምሽት፣ ለማኅበረሰቡ ለሚበጁ ግንባታዎች የሚውል ድጋፍም ተሰባስቦበታል። የረመዳን ጾምን ድባብ የሚያጎሉ መልዕክቶች ተላልፈውበታል ፣ ኃይማኖታዊ ሥርዓቶችም ተከናውነውበታል።
በአናንዴል ቨርጂኒያ የተከናወነውን ሥነ ስርዐት የተከታተለው ሀብታሙ ስዩም በአጭሩ ያስቃኘናል። 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethio-american-muslim-community-annual-iftar/8007060.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethio-american-muslim-community-annual-iftar/8007060.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 21:42:04 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሀብታሙ ስዩም)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/f038ae8b-91d2-481d-05b2-08dd5c8b1668_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዛሬው የግሪንላንድ ምርጫ ነጻ አገር የመሆን ምኞቶች የሚፈተሹበት ነው ተባለ</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በማዕድን የበለጸገችውን ደሴት ለመቆጣጠር ፍላጎት እንዳላቸው ያንጸባረቁበት ውጥን ዓለም አቀፍ ትኩረት በሳበበት በዚህ ወቅት ፤ የግሪንላንድ ነዋሪዎች ዛሬ ማክሰኞ  ምርጫ እያካሄዱ ነው። 
ትረምፕ  ሥልጣን እንደተረከቡ ነበር ‘ለዩናይትድ ስቴትስ የደህንነት ጥቅም አስፈላጊ ናት’ ሲሉ ከፊል ራስ ገዟን የዴንማርክ ግዛት የዩናይትድ ስቴትስ አካል ለማድረግ ያላቸውን ፍላጎት ይፋ ያደረጉት።
57, 000 ሕዝብ ብቻ ያላት ደሴቲቱ ግዛት የከበባት በረዶ አለት መቅለጥ የተፈጥሮ ሃብቷን ይበልጥ ተደራሽ እያደረገ በመጣበት እና አዳዲስ የመርከቦች መመላለሻ መንገዶች እየተከፈቱ ባለበት፤ የአርክቲክ ውቅያኖስን እና አካባቢውን በበላይነት ለመቆጣጠር የተያዘው እሽቅድምድም ሆናለች። ሩስያ እና ቻይናም በአካባቢው  ወታደራዊ እንቅስቃሴያቸውን አጠናክረው...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8007019.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8007019.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 20:45:35 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/70bfa989-42d8-4bd9-a8ee-41006978a74e_cx0_cy7_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የአላባማዋ ሰልማ ከተማ 60ኛውን &apos;የሰንበት ሰቆቃ&apos; መታሰቢያ አከበረች</title>
            <description>እ.አ.አ በመጋቢት 7፣ 1965፣ በዩናይትድ ስቴትስ አላባማ ግዛት፣ ሰልማ ከተማ ውስጥ የመምረጥ መብት እንዲሰጣቸው ጥንድ ጥንድ እየሆኑ በኤድመንድ ፔተስ ድልድይ ላይ የተጓዙ ሰልፈኞችን ከፊት ከሚመሩት መካከል አንዱ ቻርለን ሞልዲን ነበሩ።  
ሰልፈኞቹ ነጭ ባለሥልጣናት፣ ጥቁር አላባማውያን ድምፅ ለመስጠት እንዳይመዘገቡ መከልከላቸውን እና ከቀናት በፊት ጂሚ ሊ ጃክሰን የተሰኘው ሚኒስትር እና የመምረጥ መብት አደራጅ፣ በመንግሥት ወታደሮች ተተኩሶበት መገደሉን ተቃውመው ድምፃቸውን በማሰማት ላይ ነበሩ።
ድንገት ግን ከአላባማ ወንዝ ጫፍ ላይ ምን እንደሚጠብቃቸው ተመለከቱ፤ በፈረስ ላይ የተቀመጡ ሰዎች፣ የመንግስት ተወካዮች እና ወታደሮች። እየቀረቡ ሲመጡ የሕግ አስከባሪ አካላት እንዲበታተኑ ማስጠንቀቂያ ሰጧቸው፣ ብጥብጥም ተፈጠረ።
በወቅቱ የ17 ዓመት ወጣት የነበሩት ሞልዲን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/selma-alabama-marks-60th-anniversary-of-bloody-sunday-protest-attack/8006457.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/selma-alabama-marks-60th-anniversary-of-bloody-sunday-protest-attack/8006457.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 14:06:43 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/95f8c287-7514-4674-09cd-08dd5c8d307c_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የአሜሪካ ታጋቾች ተደራዳሪ ከሐማስ ጋራ የነበራቸውን ንግግር “ጠቃሚ” ብለውታል</title>
            <description>የትረምፕ አስተዳደር የታጋቾች ተደራዳሪ በቅርቡ በአሜሪካ ከተሰየመው የሽብር ቡድን ሐማስ ተወካዮች ጋር ያደረጉትን ንግግር “ጠቃሚ” ብለውታል።


ንግግሩ በሐማስ ተይዞ የነበረውን አሜሪካዊ-እስራኤላዊን በመልቀቅ ላይ ያተኮረ ነበር።


ንግግሩ የተካሄደው እስራኤል በዚህ ሳምንት የተኩስ አቁም ድርድር ላይ ለመወያየት የልዑካን ቡድን ልታሰማራ እንደሆነ በገለጸችበት ወቅት ነው፡፡


የቪኦኤ አራሽ አራብሳዲ የላከቸውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-israel-hamas/8005725.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-israel-hamas/8005725.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 22:08:48 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/47e1c240-fcf0-48b1-0469-08dd5c8b1668_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሀገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት የኢሚግሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ኃላፊውን በዐዲስ አመራር ተካ</title>
            <description>የሀገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት ‘ተጓተተ’ ባለው ስደተኞችን ከሀገር የማስወጣት ሥራ የተነሳ፣ የኢሚግሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ኃላፊውን በዐዲስ አመራር ተካ።


የሀገር ውስጥ ደኅንነት ሚንስትሯ ክሪስቲ ኖም በትላንትናው ዕለት የኢሚግሬሽን እና የጉምሩክ ጉዳዮች አስፈጻሚ መሥሪያ ቤት አስተዳዳሪን ከሥራ ኃላፊነታቸው በማንሳት በዐዲስ ተክተዋል።


ለዚህም ምክኒያቱ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ‘አሳካለሁ’ ያሉትን እና “በሕገ ወጥ መንገድ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ የፈለሱ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ስደተኞች ከሀገር ለማስወጣት የተያዘ ዕቅድ ዕውን ለማድረግ ነው” ተብሏል።


ትራምፕ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ስደተኞችን ከሀገር ለማባረር የገቡት ቃል የምርጫ ዘመቻቸው አብይ ትኩረት አድርገውት እንደነበር ይታወሳል። የዩናይትድ ስቴትስ የኢሚግሬሽን እና የጉምሩክ አስፈጻሚ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-homeland-security-chief-replaces-ice-leadership-over-lagging-deportations/8005292.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-homeland-security-chief-replaces-ice-leadership-over-lagging-deportations/8005292.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 18:06:57 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/902fb3a2-dfcf-4cae-09de-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኒው ዮርክ ተነስቶ የነበረው እሳት በቁጥጥር ሥር ዋለ</title>
            <description>በሎንግ አይላንድ፣ ኒው ዮርክ ቅዳሜ ዕለት ተከስቶ የነበረው የዱር እሳት በቁጥጥር ሥር ቢውልም፣ በሥፍራው የሚታየው ጠንካራ ነፋስ አካባቢውን አኹንም ለእሳት ተጋላጭ ሊያደርገው እንደሚችል ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።


ቅዳሜ ዕለት በሎንግ አይላንድ አራት ሥፍራዎች እሳት ከተስቶ አውራ ጎዳናዎችንና በአካባቢው የሚገኘውን ወታደራዊ ሠፈር እንዲዘጋ ማስገደዱን ተከትሎ፣ የግዛቲቱ መሪ ካቲ ሆቹል የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ አውጀዋል።


በዐይን ሊታይ የሚችለው እሳት ሁሉ እንደጠፋና፣ በነፋስ አማካይነት ወደ ሌላ ሥፍራ እንዳይስፋፋ የእሳት አደጋ ሠራተኞች ዙሪያውን እንደተቆጣጠሩ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። ትላንት እሑድ የነፋሱ ፍጥነት በሰዓት 48 ኪሎ ሜትር ስለነበር ስጋት ቢፈጠርም፣ አዲስ የተስፋፋ እሳት እንዳልነበር ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።


ሁለት የእሳት አደጋ ሠራተኞች ጉዳት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/firefighters-knock-down-wind-driven-brush-fire-on-long-island-but-risk-remains-with-high-winds/8005211.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/firefighters-knock-down-wind-driven-brush-fire-on-long-island-but-risk-remains-with-high-winds/8005211.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 17:19:02 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/982f6f7c-d0f0-40e6-0975-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በዋይት ሐውስ አቅራቢያ የታጠቀ ግለሰብ በፕሬዝደንታዊ የደኅንነት ጥበቃ ሠራተኞች ተመታ </title>
            <description>አንድ ከኢንዲያና ግዛት አካባቢ እንደመጣ የተገመተ እና በዋይት ሐውስ አካባቢ መሳሪያ ታጥቆ፣ ከፖሊስ ጋራ እሰጥ አገባ ውስጥ ገብቷል የተባለ ግለሰብ ፣ “ሴክሬት ሰርቪስ” በመባል በሚታወቀው፣ ዩናይትድ ስቴትስ የፕሬዝደንታዊ የደኅንነት ጥበቃ አባላት መመታቱን ባለሥልጣናት አስታወቁ።


ከዋይት ሐውስ በአንድ አካፋይ መንገድ ብቻ በሚርቅ ቦታ ላይ፣ እኩለ ሌሊት አካባቢ በተፈጠረው በዚኽ ክስተት ከታጠቀው ገለሰብ በስተቀር የተጎዳ ሌላ ሰው አለመኖሩን የ&quot;ሴክሬት ሰርቪሱ&quot; መግለጫ አመልክቷል። በሰዓቱም ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ፍሎሪዳ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ነበሩ ተብሏል።


የጥበቃ አገልግሎቱ፣ &quot;አንድ ራሱን ሊያጠፋ ነው&quot; በሚል የሚጠረጠር ግለሰብ ከኢንዲያና ተጉዞ መምጣቱን ከአካባቢ ፖሊስ መረጃ እንደደረሰው ገልጾ፣ ከተሰጠው ዝርዝር መግለጫ ጋራ የሚመሳሰለውን መኪና እና...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/armed-man-shot-by-secret-service-near-white-house-while-trump-out-of-town-/8004228.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/armed-man-shot-by-secret-service-near-white-house-while-trump-out-of-town-/8004228.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 09 Mar 2025 16:48:26 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-c0a8-0242-08b5-08dbe4556d4a_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፕሬዘዳንት ትራምፕ የቴሌቭዥን አቅራቢ የሆኑትን ላውራ ኢንግራሃምንና ማሪያ ባርቲሮሞን ለኬኔዲ ማዕከል ቦርድ አድርገው ሾሙ </title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት እንዳስታወቁት የፎክስ ኒውስ ፕሮግራም መሪ ላውራ ኢንግራሃምንና የጣቢያው ቢዝነስ ዘገባ አቅራቢ ማሪያ ባቲሮሞንን ለጆን ኤፍ ኬኔዲ የስነ ጥበባት ማዕከል ቦርድ ሹመዋል፡፡ 


ትራምፕ ስልጣን ከያዙ ከሳምንታት በኋላ የካቲት ወር ላይ የማዕከሉን ፕሬዝዳንት በማባረር የባለአደራ ቦርድ የተከኩ ሲሆን የድርጅቱን ሊቀመንበርም ሰይመዋል። 


ርምጃዎቹ የክብር ትርኢት የሚቀርቡበትና የብሄራዊ ሲምፎኒ ኦርኬስትራ እንዲሁም የዋሽንግተን ብሄራዊ ኦፔራ የሚቀርብበት የባህል ተቋም የሆነውን የኬኔዲ ማዕከል ትራምፕን መቆጣጠራቸውን ያሳያል ተብሏል፡፡ 


ትራምፕ የኢንግራሃም እና የባርቲሮሞ ሹመት ካስታወቁ በኋላ &quot;ይህ ምርጫችንን ያጠናቅቃል&quot; ሲሉ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡ 


ትራምፕ ባለፈው ወር የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/trump-appoints-anchors-laura-ingraham-maria-bartiromo-to-kennedy-center-board-/8003638.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/trump-appoints-anchors-laura-ingraham-maria-bartiromo-to-kennedy-center-board-/8003638.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 08 Mar 2025 18:48:48 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/195d0362-0d33-43cd-b995-7d8d3e221d8a_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የትረምፕ አስተዳደር ለኮሎምቢያ ዩንቨርስቲ ሊሰጥ የነበረውን የ400 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ሰረዘ  </title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትረምፕ አስተዳደር እንዳስታወቀው በኒዮርክ በሚገኘው የኮሎምብያ ዩንቨርስቲ ካምፓስና አካባቢው ባለው ፀረ ሴማዊ ትንኮሳ ምክንያት ለዩንቨርስቲው ሊሰጡ የነበሩ ወደ 400 ሚሊዮን ዶላር የሚገመቱ ዕርዳታዎችን እና ውሎችን መሰረዙን አስታውቋል፡፡


ውሳኔው ትላንት ይፋ የተደረገው የፍትህ፣ የትምህርት ፣ የጤና እና የሰብአዊ አገልግሎት እንዲሁም የአጠቃላይ አገልግሎት አስተዳደር መምሪያዎች በጋራ ባወጡት መግለጫ ነው። 


የትራምፕ አስተዳደር የገንዘብ ድጎማዎች እና ውሎች በመቋረጡ ሊጎዱ የሚችሉትን ዘርፎች አልያም የፀረ ሴማዊ ትንኮሳ ማስረጃውን ለመግለጽ ፈቃደኛ አይደለም፡፡ ይሁንና ይህ ድጋፍ ለዩንቨርስቲው ቃል ከተገባለት ከ 5 ቢሊዮን ዶላር በላይ  እርዳታ መካከል ተቀናሽ የሚሆን ነው ተብሏል፡፡ 


አብዛኛው የገንዘብ ድጋፍ ለጤና...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-cancels-400-million-in-grants-contracts-to-columbia-university-over-antisemitism-allegations-/8003566.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-cancels-400-million-in-grants-contracts-to-columbia-university-over-antisemitism-allegations-/8003566.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 08 Mar 2025 16:51:55 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/d713c53d-f747-4679-02b9-08dd5c8b1668_cx0_cy9_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አሜሪካ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ተኩስ አቁም እንዲደረግ በድጋሚ ጥሪ አደረገች</title>
            <description>ዋሽንግተን  — የአሜሪካ መንግሥት፣ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ በመቀጠል ላይ ያለው ግጭት እንዲቆም ጥሪውን በድጋሚ አሰምቷል።


የኤም 23 አማፂያን በርካታ ቦታዎችን በመቆጣጠር ላይ ባሉበት በዚህ ወቅት፣ የአሜሪካንን መንግሥት ጥሪ በድጋሚ ያሰሙት የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ታሚ ብሩስ፣ የውጪ ጉዳይ ምኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ ከዚህ በፊት በጉዳዩ ላይ ያሳዩትን አቋም በድጋሚ አንጸባርቀዋል።


ሩቢዮ ከሩዋንዳው ፕሬዝደንት ፖል ካጋሜ እና ከኮንጎው ፕሬዝደንት ፊሊክስ ቸሰደኪ ጋራ መነጋገራቸውን ያወሱት ቃል አቀባዩ፣ ግጭቱ በአስቸኳይ እንዲቆምና ለተከሰተው የሰብአዊ መብት ጥሰት ተጠያቂነት እንዲኖር ማስገንዘባቸውን ተናግረዋል።


ለኮንጎ ሕዝብ እና ለኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ሉአላዊነት ያላቸውን ድጋፍ የውጪ ጉዳይ ምኒስትሩ ማስታወቃቸውንም ቃል አቀባዩ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-drc-crisis/8003559.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-drc-crisis/8003559.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 08 Mar 2025 16:28:27 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/138a051d-950e-495b-b454-b299e8b6c756_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዶናልድ ትረምፕ የኑክሌር ድርድር እንዲደረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለኢራን ላኩ</title>
            <description>የአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ከኢራን ጋራ የኑክሌር ድርድር ማድረግ እንደሚሹ ለሀገሪቱ መሪዎች ትላንት ሐሙስ ደብዳቤ መላካቸውን አስታውቀዋል።


የኢራን መሪዎች ለመነጋገር ይስማማሉ ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉም ትረምፕ አስታውቀዋል።


ትረምፕ ከፎክስ ኒውስ ጋራ ባደረጉት ቃለ መጠይቅ፣ ኢራን ለድርድር ትቀርባለች ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉና፣ ይህም ለኢራን መልካም ሁኔታዎችን ሊፈጥር እንደሚችል ጠቁመዋል።


“ደብዳቤውን ለማግኘት የፈለጉ ይመስለኛል፣ ሌላው አማራጭ ግን አንድ ነገር ማድረግ ይኖርብናል፣ ምክኒያቱም የኑክሌር መሣሪያ እንዲኖራቸው መፍቀድ  አይቻልም “ ብለዋል ትረምፕ፡፡


ደብዳቤው የተላከው ለኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ ኻሚኒ እንደሆነ  የተገመተ ሲሆን፣ ይህንኑ ከኋይት ሃውስ ለማጣራት የተደረገው ሙከራ መልስ ባለመገኘቱ እንዳልተሳካ የሮይተርስ ዘገባ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/trump-says-he-sent-letter-to-iran-leader-to-negotiate-nuclear-deal/8002765.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/trump-says-he-sent-letter-to-iran-leader-to-negotiate-nuclear-deal/8002765.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 Mar 2025 22:02:12 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/e3de19c8-2411-4bd3-2e31-08dd5c897904_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዩናይትድ ስቴትስ ከሐማስ ጋራ መነጋገሯን ያረጋገጡት ትረምፕ ቡድኑ ታጋቾቹን በአስቸኳይ እንዲለቅቅ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጡ</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ሐማስ የተቀሩትን እስራኤላዊያን ታጋቾች በአስቸኳይ መልቀቅ እንዳለበት ትላንት ሐሙስ በድጋሚ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል::


በዩናይትድ ስቴትስ በሽብርተኛ ቡድንነት የተመዘገበው ሐማስ በበኩሉ &quot;ታጋቾቹን የምለቀው ዘላቂ የተኩስ አቁም  ከተደረገ ብቻ ነው&quot; ብሏል:: በተጨማሪም ዩናይትድ ስቴትስን እና እስራኤልን &quot;ከድርድሮቹ ወደኋላ ለማፈግፈግ እየሞከሩ ነው&quot; በማለት ወንጅሏል::

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-hamas-talks/8002708.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-hamas-talks/8002708.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 Mar 2025 21:45:19 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/6be994c6-bae2-4edc-0222-08dd5c8b1668_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>