<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>መካከለኛው ምሥራቅ - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/5281</link>
        <description>VOA Amharic provides the latest news in the Middle East, with a focus on the lives of Ethiopians and Eritreans in the region.</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>መካከለኛው ምሥራቅ - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/5281</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Sat, 25 Apr 2026 04:16:50 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zkimqyemjmqy" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>ተመድ  የሶሪያ ግጭት እንዲቆም ጥሪ አቀረበ</title>
            <description>የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሶሪያ ልዩ መልዕክተኛ፣ ከፕሬዝደንት ባሽር አል አሳድ ሥልጣን መወገድ ተከትሎ  ባለፉት ሦስት ወራት ዐዲስ በተቀሰቀሰው ግጭት እየታመሰች ባለችው ሀገር ሁከቱ እንዲቆም ተማጸኑ፡፡ የሰላማዊ ዜጎች ደኅንነት እንዲጠበቅም  ጥሪ አቀረቡ፡፡
የመንግሥታቱ ድርጅት ልዩ መልዕክተኛ ጌር ፔደርሰን ጥሪያቸውን ያቀረቡት፣  የዲሞክራሲ ደጋፊዎች ሀገሪቱን ለዐስርት ዓመታት ወደ ዘለቀው የርስ በርስ ጦርነት ያመራው ጸረ  አሳድ ተቃውሞ የተጀመረበት 14ኛው ዓመት መታሰቢያ በሆነው በዛሬው ዕለት ነው፡፡
“የለውጥ ጥያቄ ጭካኔ የተሞላበት ከፍተኛ ብጥብጥ ገጥሞታል፣ በዘመናችን እጅግ አሰቃቂ ወደ ኾነ  ግጭት አምርቷል” ያሉት ፔደርሰን “ግጭቱ ጥልቅ  የሆነውን አስከፊውን የሰው ልጅ ጭካኔ አጋልጧል።” ብለዋል፡፡
“የሚወዷቸውን በሞት ያጡ ቤተሰቦች ሐዘን ላይ ናቸው፡፡ ማኅበረሰቦች ተበታትነዋል፡፡ ሚሊዮኖች ከቀያቸው ተነቅለዋል፣ብዙዎችም የጠፉባትን በማፈላለግ ላይ ይገኛሉ” ሲሉም ፔደርሰን አክለዋል፡፡
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት  ሶሪያ ውስጥ ግጭት ከ6 ሚሊዮን በላይ ስደተኞችን ጨምሮ ወደ 12 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን አፈናቅሏል ብሏል።
አሳድ እ.ኤ.አ. ታኅሣሥ 2024 ከሥልጣን ቢወገዱም ከመጋቢት 6 ጀምሮ በጠረፉ ክፍለ ግዛት በኩል በተጀመረ ሁከት ሀገሪቱ በርካቶችን ለሞት በዳረገ ሁከት ተንጣለች፡፡
የቀድሞ ፕሬዝደንት ታማኞች ከጸጥታ ኃይሎች ጋራ ባደረጉት አስከፊ ግጭት በርካታ ሲቪሎችን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሞተዋል፡፡


</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un---syria/8010894.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un---syria/8010894.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 20:17:30 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/c5473208-e41e-4ba1-0fa7-08dd5c8d307c_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሳዑዲ አረቢያ በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን መመለስ ዳግም ተጀመረ</title>
            <description>ዛሬ በሦስት በረራዎች ከ1 ሺሕ በላይ ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ አረቢያ ተመልሰዋል
በሳዑዲ አረቢያ በእስር ቤት እና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በዘመቻ የማስመለስ ተግባር ሲካሔድ የአሁኑ ለ4ኛ ዙር እንደሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ገልጸዋል፡፡
ከሳዑዲ አረቢያ መንግሥት ጋራ በተደረሰ ስምምነት መሰረት የተጀመረው የአሁኑ ዜጎችን የማስመለስ ተግባር፣ በሳምንት ውስጥ በሦስት ቀናት ዘጠኝ በረራዎችን በማድረግ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል፡፡
ዛሬ የተመለሱ ዜጎች በአየር መንገድ አቀባበል ከተደረግላቸው በኋላ ቃለመጠይቅ ለማድረግ ሞክረን የነበረ ሲኾን፣ ከአስተባባሪዎቹ ሁኔታዎች ሊመቻቹልን ባለመቻሉ ፣ አስተያየታቸውን ማካተት አልቻልንም፡፡
ይኹን እንጂ፣ “ለሦስ ዓመት እና ከዚያም በላይ በሳዑዲ አረቢያ መታሰራቸውን እና ለተለያየ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተጋልጠው መቆየታቸውን” አንዳንድ ተመላሾች ከአውሮፕላን በሚወርዱበት ወቅት ነግረውናል፡፡
አሁንም በርካታ መሰል ችግር ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ እንደሚገኙም ገልፀዋል፡፡
የተለያዩ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች እና ሀገራት፣ ሰነድ የሌላቸው ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ አረቢያ እስከሞት የሚደርስ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየተፈፀመባቸው እንደሚገኝ በተለያዩ ጊዜያት መግለጻቸው ይታወቃል፡፡
ከእዚህ መካከል የሆነው ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ የሳዑዲ ድምበር ጠባቂዎች ከመጋቢት 2014 እስከ ሰኔ 2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ “የየመን እና የሳዑዲ ድንበርን ለማቋረጥ የሞከሩ በትንሹ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ገድለዋል” ማለቱ አይዘነጋም።


የቪኦኤ አማርኛን ዋትስአፕ ቻናል ይከተሉ  
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-returnees-arrive-home/8008477.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-returnees-arrive-home/8008477.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 22:09:27 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ኬኔዲ አባተ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/25af83c4-25cf-489f-0d8f-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>&quot;ማንም ከሕግ በላይ መኾን አይችልም&quot; የሶሪያ የኃይማኖት ተኮር ጥቃቶች መርማሪ ኮሚቴ</title>
            <description>በሶሪያ የጦር ሠራዊት እና በቀድሞው የሀገሪቱ መሪ ባሻር አል አሳድ ታማኞች መካከል የሚካሄደውን ውጊያ የሚመረምረው ኮሚቴ &quot;ማንም ከሕግ በላይ አይኾንም፥ የድርጊቱን ተጠያቂዎች በሙሉ ታስረው ሕግ ፊት እንዲቀርቡ እናደርጋለን&quot; ሲል ተናገረ።
ብዙኅኑ ነዋሪዎች ከሥልጣን የተወገዱት ፕሬዝደንት ኃይማኖታዊ ማኅበረሰብ &quot;አላዊቶች&quot; በሆኑባቸው መንደሮች ብዙ መቶ ሲቪሎች መገደላቸውን ዕማኞች እና የጦርነት ተከታታይ ቡድን ሪፖርቶች ያመለከቱ ሲሆን በአክራሪ እስልምና አቀንቃኞች የሚመራው የሶሪያ መንግሥት ምርመራ እንዲከፍት ግፊቱ በርትቶ ቀጥሏል።
የመርማሪ ኮሚቴው ቃል አቀባይ ያሲር ፋርሃን ዛሬ ማክሰኞ በቴሊቭዥን በተላለፈ ጋዜጣዊ ጉባኤ ላይ ሲናገሩ&quot; ማንም ከሕግ በላይ መሆን አይችልም። የምርመራችንን ውጤት ለፕሬዝደንቱ እና ለፍትሕ ተቋሙ እናቀርባለን&quot; ብለዋል። መርማሪ ኮሚቴው ዕማኞችን እና የጥቃቱን ተጠርጣሪዎች ቃል ተቀብሎ በቂ ማስረጃ ያገኘባቸውን ተጠርጣሪዎች ለፍትሕ አካሉ እንደሚያስተላልፍ አስታውቀዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽን እንዳመለከተው የመንግሥቱ ጦር በጠረፉ ግዛት በአሳድ ታማኞች ላይ በከፈተው ኃይማኖት ተኮር ዘመቻ ቤተሰቦች ሴቶች እና ሕጻናትን ሳይቀሩ ተገድለዋል።
የሶሪያ የሽግግር ፕሬዝደንት አሕመድ አል ሻራ ትላንት ሰኞ በሰጡት ቃለ መጠይቅ የቀድሞዎቹን ሽምቅ ተዋጊ ቡድኖች በአንድ ተቋም ሥር ያዋሃደው የሀገሪቱ የመከላከያ ሚንስቴር ሠራዊት በግድያው ተሳትፎ እንደሁ ለመናገር አልችልም ማለታቸውን ሮይተርስ ጠቅሷል።
ብጥብጡ የተቀጣጠለው በጠረፉ ክፍለ ግዛት ያሉት የመንግሥቱ ኃይሎች በአሳድ መንግሥት ርዝራዦች ጥቃት እንደተከፈተባቸው የመንግሥቱ ባለሥልጣናት ሐሙስ ዕለት መናገራቸውን ተከትሎ ነው።
በሱኒ እስልምና አክራሪዎች የሚመራው መንግሥት &quot; የአሳድ መንግሥት ቅሪቶች በሚገባ የተዘጋጁበት ገዳይ ጥቃት&quot; ያለውን ለመደምሰስ ብዛት ያለው ጦር ወደአካባቢው አዝምቷል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/syrian-fact-finding-committee-for-sectarian-killings-says-no-one-above-the-law/8006941.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/syrian-fact-finding-committee-for-sectarian-killings-says-no-one-above-the-law/8006941.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 19:46:28 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/f7fdb16c-dfb1-4efb-928d-e28cc90557a5_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዩክሬይን በዩናይትድ ስቴትስ ለተወጠነው የሰላም ንግግር ዕቅድ ልታቀርብ ነው</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ እና የዩክሬን ባለሥልጣናት ዛሬ ማክሰኞ ሳዑዲ አረቢያ ላይ በኪየቭ እና ሞስኮ መካከል የከፊል ተኩስ የማቆም ስምነት የታለመ እቅዳቸውን እንዲያቀርቡ የሚጠበቅበት ንግግር ጀምረዋል።  
የዩክሬን እቅድ የረጅም ርቀት የሚሳዬል ጥቃቶችን ማቆም እና ጥቁር ባህርን የሚሸፍን የሰላም ስምምነት ያካትታል። 
የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ በዛሬው ንግግር አልተሳተፉም። በምትካቸው የፕሬዝደንታዊው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አንድሬ የርማክ፣ የዩክሬኑ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንድሪ ሲቢሃ፣ የመከላከያ ሚንስትሩ ረስተም ኡሜሮቭ እና ወታደራዊ አዛዡ ፓቭሎ ፓሊሳ ተወክለዋል።  
የርማክ ከስብሰባው አስቀድሞ ለጋዜጠኞች በሰጡት አስተያየት “ሰላምን እንዲመጣ ዩክሬን ሁሉንም ነገር ለማድረግ ዝግጁ ነች&quot; ብለዋል።.
ሀገራቸው የደኅንነት ዋስትና እንዲሰጣት ትሻ እንደሆን የተጠየቁት የርማክ &quot;አዎን! ዩክሬን ሩስያ ይህን መሰል የኃይል ጥቃቷን ፈጽሞ እንደማትደግም ማረጋገጥ ትሻለች&quot; ብለዋል።
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ2022 መጀመሪያ ላይ ሩስያ በዩክሬን ላይ ለከፈተችው መጠነ ሰፊ ወረራ አፋጣኝ ማብቂያ ለማበጀት በያዙት ጥረት የዩናይትድ ስቴትስን ልዑካን ቡድን የመሩት የዩናይትድ ስቴትሱ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ እና የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪው ማይክ ዋልትዝ ናቸው።
ሩቢዮ ትላንት ሰኞ ሲናገሩ ዩናይትድ ስቴትስ ለጊዜው የተቋረጠው ለዩክሬን ይሰጥ የነበረው ርዳታ ጉዳይም እልባት ያገኛል የሚል ተስፋ እንዳላት አመልክተዋል። 
ሩቢዮ አክለውም ከዩክሬይን ጋራ በሚደረገው ንግግር ላበረከቱት አስተዋፆ ብሪታንያን እና ፈረንሳይን አወድሰዋል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/rubio-ukraine/8006758.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/rubio-ukraine/8006758.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 18:40:25 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/d78f7d16-5b43-44a4-0b3f-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የየመን ሁቲዎች ለእስራኤል የጋዛን የእርዳታ እገዳ እንድታነሳ የአራት ቀናት ቀነ ገደብ ሰጡ </title>
            <description>የየመን ሁቲ አማጽያን መሪ እስራኤል በአራት ቀናት ውስጥ በጋዛ ላይ የጣለችውን የእርዳታ እገዳ ካላነሳች ቡድኑ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን የባህር ሃይል ጥቃት እንደሚቀጥል ትላንት አስታውቋል፡፡ 


ይህም  እ.ኤ.አ. በጥር ወር የተኩስ አቁም ስምምነት ከተደረሰ በኋላ እየቀነሰ የመጣው የሁቲዎች ጥቃት ሊባባስ እንደሚችል የሚጠቁም ነው ተብሏል፡፡ 


ኢራን አጋር የሆኑት የሁቲ አማጽያን እስራኤል በጋዛ በዩናይትድ ስቴትስ በሽብር የተፈረጀው ሃማስ ቡድን ላይ በከፈተችው ጦርነት ምክንያት ለፍልስጤማውያን አጋርነት ለማሳየት በሚል ከእአአ ህዳር 2023 ጀምሮ በመርከብ ላይ ያነጣጠሩ ከ100 በላይ ጥቃቶችን ፈጽሟል፡፡ 


መሪው አል-ሁቲ በኩል &quot;ለአራት ቀናት ቀነ ገደብ እንሰጣለን፡ ይህም የጊዜ ገደብም ለጋዛ የተኩስ አቁም አሸማጋዮች ለጥረታቸው ሲባል ነው&quot; ብሏል፡፡ 


እ.ኤ.አ መጋቢት 2 ጀምሮ እስራኤል የእርዳታ መኪኖችን ወደ ጋዛ እንዳይገቡ አግዳለች፡፡ ሃማስ እርዳታዎችን በመስረቅ  ለፍልስጤማውያን እንዳይደርስ አድርጓል ስትልም ትከሳለች፡፡ 


  

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/yemen-s-houthis-give-israel-four-day-deadline-to-lift-gaza-aid-blockage-/8003650.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/yemen-s-houthis-give-israel-four-day-deadline-to-lift-gaza-aid-blockage-/8003650.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 08 Mar 2025 19:03:06 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/95585d2f-459e-48cc-ac74-170ae4c41f00_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሐማስ የትረምፕ አስተያየት እስራኤል ከስምምነቱ እንድታፈገፍግ ያበረታታል አለ</title>
            <description>ዩናይትድ ስቴትስ በሽብርተኝነት የተፈረጀው ሐማስ  “የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ ዛቻዎች እስራኤል ከጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት እንድትወጣ እያበረታታ ነው” ሲል ዛሬ ሐሙስ ተናገረ።


ሐማስ ይህን የገለጸው፣ ትረምፕ ሐማስ ጋዛ የሚገኙ ቀሪዎቹን ታጋቾች ካልፈታ “ ከባድ ቅጣት ያገኘዋል” ካሉ አንድ ቀን በኋላ ነው።


ትረምፕ ትሩዝ ሶሻል በተባለው የማኅበራዊ መገናኛ መድረካቸው ላይ “ሁሉንም ታጋቾች ሳይዘገይ፣ አሁኑኑ ልቀቁ ፣ የገደላችኋቸውን ሰዎች አስከሬንም በሙሉ አሁኑኑ መልሱ፡፡ ካልሆነ አለቀላችሁ።” ብለዋል፡፡


ትረምፕ አክለውም “እስራኤል ሥራውን ለማጠናቀቅ የሚያስፈልጋትን ሁሉን ነገር እየላኩ ነው፡፡ ያልኩትን  ካላደረጋችሁ አንድም የሐማስ አባል አይተርፍም” ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡


የተኩስ አቁሙ የመጀመሪያው ምዕራፍ ባለፈው ቅዳሜ አብቅቷል። በስምምነቱ መሠረት ሐማስ 33 እስራኤላውያን ታጋቾችን እና አምስት የታይላንድ ዜጎችን ሲለቅ፣ እስራኤል 2 ሺሕ የሚጠጉ የፍልስጤም እስረኞች ለቃለች።


ኋይት ሀውስ ከሐማስ ጋራ በቀጥታ ውይይት ማድረጉን ትላንት ረቡዕ አረጋግጧል። “ውይይቱ ያተኮረው አሁንም በጋዛ ታግተው የሚገኙ አሜሪካውያንን ስለ መልቀቅ ነው” ሲሉ፣ ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ምንጮች ገልጸዋል።


የኋይት ሐውስ ቃል አቀባይ ካሮላይን ሌቪት ንግግሮቹን “ለአሜሪካ ሕዝብ የሚጠቅመውን ለማድረግ በቅን ልቦና የተደረገ ጥረት ነው” ሲሉ ገልፀውታል።


የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጽሕፈት ቤት በሰጠው መግለጫ ደግሞ እስራኤል &quot;ከሐማስ ጋራ በቀጥታ መነጋገርን በሚመለከት ያላትን አቋም ለአሜሪካ አስታውቃለች&quot; ብሏል።


የጋዛ ጦርነት የጀመረው፣ ሐማስ እ.ኤ.አ ጥቅምት 2023 እስራኤል ላይ ባደረሰው ድንገተኛ ጥቃት፣ 1ሺሕ 200 የሚጠጉ ሰዎችን ከገደለ እና 250 ሰዎች አግቶ ከወሰደ በኋላ ነበር።


እስራኤል በአፀፋው ጋዛ ላይ በወሰደችው ጥቃት ከ48 ሺሕ 400 በላይ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል ሲል የጋዛው ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-hamas-talks/8001007.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-hamas-talks/8001007.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 06 Mar 2025 17:37:41 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9308cab3-ded2-4380-0088-08dd5c8b1668_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>እስራኤል ዕርዳታ ወደ ጋዛ እንዳይገባ በማገዷ የረድኤት ድርጅቶች ስጋት ገብቷቸዋል</title>
            <description>እስራኤል ከውሃ በስተቀር ማንኛውም የሰብአዊ ዕርዳታ ወደ ጋዛ ሰርጥ እንዳይገባ ማገዷ፣ ወትሮውንም በሕይወት ለመቆየት ትግል ላይ ባሉት ሕፃናትና ቤተሰቦቻቸው ላይ አደገኛ ሁኔታ ሊፈጥር እንደሚችል የተባበሩት መንግሥታት  የሕፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) አስታውቋል።


“ትላንት በዕርዳታ ላይ የተጣለው እገዳ የሲቪሎችን ሕይወት ለመታደግ በሚደረገው ጥረት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳድራል” ሲሉ የቀጠናው የዩኒሴፍ ኅላፊ ኤድዋርድ ቤግበደር አስታውቀዋል።


የሕፃናትን ደህንነት ለመጠበቅ ወሳኝ የሆነው የተኩስ አቁም መቀጠሉ አስፈላጊ እንደሆነም ኅላፊው ጨምረው ተናግረዋል።


በመካከለኛው ምሥራቅ የአሜሪካ ልዑክ የሆኑት ስቲቨን ዊትኮፍ ተኩስ አቁሙ እስከ እ.አ.አ ሚያዚያ 20 ድረስ እንዲራዘም መጠየቃቸውን ያወሱት የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ፣ ይህም የረመዳን ወር እና የአይሁድ በዓላትን የሚሸፍን ሲሆን፣ በዚህ ወቅት በመጀመሪያው ቀን ሃማስ ግማሽ የሚሆኑ ታጋቾችን እንደሚለቅ፣ በመቀጠል ቋሚ የተኩስ ማቆም ሲፈጸም ደግሞ የተቀሩትን ታጋቾች እንደሚለቅ ተናግረዋል።


“ይህን ሃሳብ እቀበላለሁ፣ ሃማስ ግን እስከ አሁን እየተቃወመው ነው” ሲሉ አክለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።


እስራኤል ዕርዳታ እንዳይገባ ያገደችው ሃማስ ዕርዳታውን በመስረቁ እና ፍልስጤማውያን እንዳያገኙት በማድረጉ እንደሆነም ኔታንያሁ አስታውቀዋል። “ዕርዳታውን ለሽብር ተግባር እየተጠቀመብት ነው” ሲሉም ክስ አሰምተዋል። የተመድ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪክ ኔታንያሁ የጠቀሱት ጉዳይ ስለመከሰቱ በሥፍራው የሚገኙ ባልደረቦቻቸው ሪፖርት እንዳላደርጉ አስታውቀዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/humanitarians-fearful-for-gaza-as-israel-halts-aid-deliveries/7997670.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/humanitarians-fearful-for-gaza-as-israel-halts-aid-deliveries/7997670.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 05 Mar 2025 00:08:06 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9c042a32-dace-43d9-0761-08dd4a817621_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>እስራኤል በጋዛ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ለማድረግ የአሜሪካን ዕቅድ ስትደግፍ ሀማስ ተቃውሟል</title>
            <description>የእስራኤል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፤ በእስራኤል እና ሀማስ መካከል የተደረሰው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ሊያበቃ የሰዓታት ጊዜ በቀሩት ወቅት፤ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልዑክ የሆኑት ስቲቭ ዊትኮፍ፤ በረመዳን እና በፋሲካ የጾም ወቅት በጋዛ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ያቀረቡትን ሀሳብ ሀገራቸው መቀበሏን  እሁድ ማለዳ አስታውቋል።


ዊትኮፍ ባቀረቡት ዕቅድ መሰረትም በመጀመሪያው ቀን በጋዛ በህይወትም ያሉት እና ከሞቱትም ታጋቾች ግማሾቹ እንደሚለቀቁ የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጽህፈት ቤት የገለጸ ሲሆን፥ ቀሪዎቹ ታጋቾችም ዘላቂ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ከተደረሰ በኋላ እንደሚለቀቁ ገልጿል።


ዊትኮፍ በቋሚ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመነጋገር ተጨማሪ ጊዜ እንደሚያስፈልግ በመረዳታቸው፤ አሁን ያለውን የተኩስ አቁም ለማራዘም ሀሳብ አቅርበዋል ሲል የኔታኒያሁ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።


በዩናይትድ ስቴትስ አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀው የሐማስ ቡድን ቃል አቀባይ ሀዜም ቃሴም ከቅዳሜ  ዕለት ቀደም ብሎ ቡድኑ በጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት የመጀመሪያ ምዕራፍ መራዘሙን ውድቅ ማድረጉን ቢገልጹም የዊትኮፍ እቅድን በግልፅ አልጠቀሱም።


እስራኤል በዊትኮፍ እቅድ ላይ ሀማስ ከተስማማ ወዲያውኑ ድርድር ታካሂዳለች ሲል የኔታኒያሁ ቢሮ አስታውቋል።


“በስምምነቱ መሰረት እስራኤል ከ42ኛው ቀን በኋላ ድርድሩ ውጤታማ እንዳልሆነ ከተሰማት ወደ ጦርነት መመለስ ትችላለች”  በማለት የኔታኒያሁ ጽህፈት ቤት ሀማስ ስምምነቱን ጥሷል ሲል ከሷል።


ሁለቱም ወገኖች አንዱ ሌላኛውን ስምምነቱን ጥሷል በሚል ሲከሱ ቆይተዋል።


ስለድርድሩ የሚያውቁ ሁለት የፍልስጤም ባለሥልጣናት ለሮይተርስ እንደተናገሩት እስራኤል ወደ ሁለተኛው የስምምነት ምዕራፍ ለመግባትም ሆነ በዚህ ጉዳይ ላይ ድርድር ለመጀመር ፈቃደኛ አልሆነችም ብለዋል።


በምትኩ፣ እስራኤል ሳምንታቶቹን በማራዘም ለተራዘመው ለእያንዳንዱ ሳምንት በርካታ ታጋቾችን እና አካላት እንዲለቀቁላት ጠይቃለች።


ቅዳሜ ዕለት የሀማስ ታጠቂ ክንፍ የእስራኤል ታጋቾች አሁንም በጋዛ በእስር ላይ እንደሚገኙ የሚያሳይ ቪዲዮ የለጠፈ ሲሆን፤  የተቀሩት ታጋቾች ሊፈቱ የሚችሉት በጎርጎርሳውያኑ ጥር 19 የተጀመረው የተኩስ አቁም ስምምነት ሲጠናቀቅ ብቻ መሆኑን አፅንዖት ሰጥቷል።


የተኩስ አቁም ንግግሮች በቅርቡ በካይሮ ቢደረጉም ስምምነት ላይ ሳይደረስ ተጠናቀዋል።


በተያያዘ ዜና ዛሬ እሁድ እስራኤል ሀማስ በቋፍ ላይ ያለውን የተኩስ አቁም የማይቀበል ከሆነ ወደ ጋዛ ሰርጥ የሚገቡ ምርቶችና ሸቀጦችን እንደምትገድብ እና “ተጨማሪ መዘዞች” እንደሚከተሉ አስታውቃለች።


ሀማስ እስራኤል ጫፍ ላይ ያለውን የተኩስ አቁም ስምምነት ለማደናቀፍ እየሞከረች ነው በማለት የከሰሰ ሲሆን፤  ዕርዳታውን ለማቆም የወሰነችው ውሳኔም “ርካሽ ዘረፋ፣ የጦር ወንጀል እና ግልጽ ጥቃት” ነው ብሏል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/israel-backs-us-plan-for-temporary-ceasefire-in-gaza-hamas-rejects-it/7994307.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/israel-backs-us-plan-for-temporary-ceasefire-in-gaza-hamas-rejects-it/7994307.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 02 Mar 2025 19:40:16 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/d9700e22-b6fe-43ab-9262-08dd4a843460_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ተቃራኒ ፍላጎቶች እና የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት</title>
            <description>በእስራኤል እና በሐማስ መካከል የተደረሰው የጋዛ ጦርነት የተኩስ አቁም ድርድር፣ በተቃራኒ ዘላቂ ፍላጎቶች የተወሳሰበ ነው፤ ሲሉ ሁለት ምሁራን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።




በታጋቾች እና እስረኞች ልውውጥ ላይ በተመሠረተ የተኩስ አቁም ድርድር ላይ ባለው በጋዛው ጦርነት፣ በሁለቱም ወገኖች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ምሁራኑ አመልክተዋል፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ መፍትሔ ማግኘት ይቻላል የሚል እምነት እንደሌላቸውም ገልጸዋል።


በቴል አቪቭ ዩኒቨርሲቲ የሴማዊ ቋንቋ መምህር የኾኑትን ዶር. አንበሴ ተፈራንና ዶ.ር አደም ካሚልን አነጋግረናል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/israel-and-hamas-conflict/7983714.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/israel-and-hamas-conflict/7983714.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 24 Feb 2025 17:18:18 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/678882c2-2a51-4029-9275-188dd7dad6b8_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ታጋቾቿ &apos;አሸማቃቂ&apos; በሆነ መንገድ ተለቀዋል ያለቸው እስራኤል የፍልስጤም እስረኞችን የመልቀቁን ሂደት አዘገየች  </title>
            <description>እስራኤል ቀጣዮቹ ታጋቾቿ መፈታታቸው እስከሚረጋገጥ እና በጋዛ በሚካሄደው የእስረኛ ልውውጥ ወቅት ይፈፀማል ያለችው አሸማቃቂ ሥነስርዓት እስከሚነሳ ድረስ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ የፍልስጤም እስረኞችን የመልቀቁን ሂደት ማዘግየቷን አስታውቃለች። 


የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ፅህፈት ቤት ዛሬ እሁድ ያወጣው መግለጫ ይፋ የሆነው እስረኞችን የጫኑ ተሽከርካሪዎች ከኦፈር ማረሚያ ቤት እየወጡ ባሉበት ወቅት ሲሆን፣ መኪናዎቹ አዙረው ወደ እስርቤቱ ተመልሰዋል። 


ስድስቱ የእስራኤል ታጋቾች ቅዳሜ እለት መለቀቃቸውን ተከትሎ ከእስር መፈታት የነበረባቸው 620 የፍልስጤም እስረኞች እስካሁን እንዳልተፈቱም ተገልጿል። ይህ ድንገተኛ የእስራኤል መግለጫ፣ የተኩስ ማቆሙን ስምምነት እጣፈንታ ጥርጣሬ ላይ ጥሎታል። 


የእስረኞቹ መፈታት መዘግየቱን የፍልስጤም አስተዳደር እስረኞች ጉዳይ ኮሚሽን ያስታወቀ ሲሆን ዌስት ባንክ ውስጥ የተቀረፀው የአሶሽዬትድ ፕሬስ ምስል፣ የእስረኛ ቤተሰቦች እጅግ በጣም በሚቀዘቅዘው አየር ውስጥ ሆነው ሲጠባበቁ እና በመጨረሻ ሲበተኑ ያሳያል። 


ቅዳሜ እለት የተለቀቁት ስድስቱ ታጋቾች፣ በመጀመሪያው ዙር የተኩስ ስምምነት ይለቀቃሉ ተብለው ከተጠበቁት በህይወት ያሉ የመጨረሻዎቹ ታጋቾች ሲሆኑ፣ ይህ ዙር ከአንድ ሳምንት በኃላ ይጠናቀቃል። ለሁለተኛው ዙር የተኩስ ስምምነት የሚደረገው ድርድር ገና አለመጀመሩም ተመልክቷል። 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7985134.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7985134.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 23 Feb 2025 19:01:30 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/666669d3-d6a6-455d-b6e9-8e008e04579e_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሃማስ ተጨማሪ እስራኤላውያን ታጋቾችን ለቀቀ </title>
            <description>የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል በሆነው የታጋቾችና እስረኞች ልውውጥ ሁለት እስራኤላውያን ታጋቾች ዛሬ አስቀድመው የተለቀቁ ሲሆን ሌሎች ሶስት ታጋቾች ደግሞ ቆይተው ተለቀዋል፡፡ በዚህ ምትክም በመቶ የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን እስረኞች የሚለቀቁ ይሆናል፡፡ 


 ከጋዛ አርብ የተመለሰው አስከሬንም የታጋች ሺሪ ቢባስ መሆኑም ተረጋግጧል፡፡ 


አስቀድመው ከተለቀቁት ታጋቾች መካከል የ40 አመቱ ታል ሾሃም፣ እአአ ጥቅምት 7፣ 2023  ሃማስ በእስራኤል ላይ ባደረሰው ጥቃት ከኪቡትዝ ቢኤሪ ታግቶ የተወሰደ ሲሆን ሁለተኛው የ39 አመቱ አቬራ መንግስቱ ደግሞ ከአስር አመት በፊት ብቻውን ወደ ጋዛ ገብቶ የነበረ ነው፡፡  


ታጋቾችን ሃማስ ዛሬ ቅዳሜ ረፋድ ላይ በጋዛ ራፋህ ከተማ ለቀይ መስቀል አስረክቧቸዋል፡፡ በርክክቡ  ወቅት አውቶማቲክ መሳሪያ የያዙ እና ወታደራዊ ልብስ የለበሱ የሃማስ ተዋጊዎችን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ዝናባማ በሆነው የአየር ሁኔታ ራፋህ አደባባይ ላይ ቁመው ታይተዋል፡፡ 


ሃማስ ቆይቶም የ27 ዓመቱን ኤሊያ ኮኸን፣ የ22 አመቱ ኡመር ሸህም ቶቨ እና የ23 አመቱ ኡመር ዌንከርት የተባሉ ሶስት እስራኤላውያን ታጋቾችን ለቋል፡፡ 


ኮኸን፣ ቶቭ እና ዌንከርት እአአ ጥቅምት 7፣ 2023 በአሜሪካ በሽብርተኝነት የተፈረጀው ሃማስ  በእስራኤል ላይ  ጥቃት ባደረሰበት ወቅት ከሙዚቃ ፌስቲቫል ላይ አግቶ የወሰዳቸው ናቸው፡፡ 


በቴል አቪቭ የእስራኤልን ባንዲራ የሚያውለበልቡ እና የታጋቾቹን ምስል የያዙ ሰዎችም የታጋቾችን መለቀቅ በቪድዮ ሲከታተሉና ደስታቸውን ሲገልጹ ታይተዋል፡፡ 


በተለቀቁት ታጋቾች በምትኩ እስራኤል ከ600 በላይ ፍልስጤማውያንን እስረኞችን ትፈታለች። 


ሌላ አንድ ታጋች ዛሬ አመሻሽ ላይ ይለቀቃ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን አጠቃላይ የተለቀቁት ስድስቱ ታጋቾችም  በመጀመሪያው ምዕራፍ የተኩስ አቁም ወቅት ነፃ የሚወጡት የመጨረሻዎቹ ታጋቾች ይሆናሉ ተብሎም ይጠበቃል። 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7984395.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7984395.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 22 Feb 2025 16:59:33 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/3a921b74-e604-459c-97c0-7423c6f73502_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሃማስ የአራት ታጋቾች አስከሬን ለእስራኤል አስረከበ</title>
            <description>ሃማስ በዛሬው ዕለት ደቡባዊ ጋዛ ካን ዩኒስ ውስጥ ለእስራኤል ኃይሎች ያስረከባቸው አራት እስራኤላዊ ታጋቾችን አስከሬን የያዙ ሳጥኖች በቀይ መስቀል ተሽከርካሪዎች ወደ ቴላቪቭ ተጓጉዘዋል።


ባንዲራዎች እና ጹሑፎች የሰፈሩባቸው ጨርቆች በታዩበት መድረክ ሃማስ አስከሬኖቹን የተሸከሙትን አራት ጥቋቁር ሳጥኖች ባስረከበበት በዚህ ሥነ ስርዐት በብዙ መቶዎች የተቆጠሩ ሰዎች ተገኝተዋል።


አንዳንዶች ካነገቧቸው የተለያዩ መልዕክቶች ከሰፈረባቸው ጨርቆች አንዱ የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በጦር ወንጀለኝነት ይከሳል። የእስራኤል የአየር ጥቃት ለታጋቾቹ ሞት ‘ምክንያት ሆኗል’ ሲልም ይወነጅላል።


ቀይ መስቀል አራቱን የሬሳ ሳጥኖች ለእስራኤል ጦር ሠራዊት ማስረከቡን እና የሟቾቹን ማንነት ለማረጋገጥ አስከሬኖቹ ቴል አቪቭ ወደሚገኘው ብሔራዊ ልዩ ምርመራ ማዕከል መወሰዳቸውን የኔታንያሁ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።


ለእስራኤል ተላልፈው የተሰጡት አስከሬኖች፤ በታገቱበት ወቅት የዘጠኝ ወር ዕድሜ የነበረውን ጨቅላ ልጃቸውን እና የታላቅ ወንድሙን የአራት  ዓመቱን አርየል ቢባስን፤ የአባታቸውን የክፊር ቢባስን እና እንዲሁም የእናታቸውን ሺሪ ቢባስን ጨምሮ የአራቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት ይገኙበታል። 


የቢባስ ቤተሰብ አባላት እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር ጥቅምት 7 ቀን 2023 ዓ.ም  ከኪቡትዝ ኒር ኦዝ በሃማስ ታጣቂዎች ታግተው ከተወሰዱት ውስጥ ናቸው።


የእገታውን ትዕይንት የሚያሳይ የቪዲዮ ምስል ሺሪ ቢባስ ሁለቱን ወንዶች ልጆቻቸውን በብርድ ልብስ ሲሸፋፍኑ እና በታጣቂዎች በኃይል እየተገፉ ሲወሰዱ ያሳያል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/israel-hamas-fighting/7982024.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/israel-hamas-fighting/7982024.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 20 Feb 2025 19:40:59 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/b99384d3-a126-4ccb-892f-08dd4a843460_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ አምስት ቦታዎች ወታደሮቿን አስቀምጣለች</title>
            <description>የእስራኤል ወታደሮች ከታጣቂው ሄዝቦላህ ጋራ በተደረሰበት የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት፣ አካባቢውን ለቀው መውጣት በሚገባቸው የዛሬው ማክሰኞ ቀነ ገደብ  ከአንዳንድ የደቡብ ሊባኖስ አካባቢዎች ለቀው አለመውጣታቸው ተነገረ፡፡


እስራኤል በክልሉ ከሚገኙ አንዳንድ መንደሮች ለቃ ብትወጣም፣ የሰሜናዊ እስራኤልን የተወሰኑ ክፍሎችን ለመጠበቅ አስፈላጊ ናቸው ካለቻቸው አምስት ቦታዎች ኃይሏን ያላስወጣች መሆኑን ተናግራለች።


የሊባኖስ ፕሬዝደንት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የፓርላማ አፈ-ጉባኤ ዛሬ ማክሰኞ በሰጡት የጋራ መግለጫ የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት እስራኤል በአስቸኳይ እንድትወጣ እንዲጠይቅ ጥሪ አቅርበዋል።


መግለጫው &quot;በማንኛውም ስንዝር የሊባኖስ ግዛት ውስጥ የእስራኤል ጦር መገኘት ወረራ ነው፣ በዓለም አቀፍ ሕግ መሰረት የሚያስከትላቸው መዘዞች አሉት&quot; ሲል ገልጿል።


የተኩስ አቁም ስምምነቱ ሂዝቦላህ ከእስራኤል ድንበር ርቆ እንዲሄድ እና የተባበሩት መንግሥታት የሰላም አስከባሪ ኃይሎች ከሊባኖስ ወታደሮች ጋራ በተለቀቀው የመከላከያ ቀጠና እንዲሰማሩ ከማድረግ ጋራ፣ እስራኤል በጥር መጨረሻ ለቃ እንድትወጣ ይጠይቃል፡፡ የተራዘመው ቀነ-ገደብ ወደ ዛሬ ማክሰኞ እንዲገፋ መደረጉም ተመልክቷል፡፡ ፡፡


የተባበሩት መንግሥታት የሊባኖስ ተወካይ ጄኒን ሄኒስ-ፕላስቻርት እና በሊባኖስ የተባበሩት መንግሥታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል አሮልዶ ላዛሮ በጋራ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት የተኩስ አቁም ስምምነቱን ተግባራዊ የሚደረግበት ሌላ የተራዘመ ቀን መኖሩ “እኛ ይሆናል ብለን ያሰብነው አይደለም” ብለዋል።


መግለጫው አክሎም &quot;ሁለቱም ወገኖች ግዴታቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን። በመንደሮቻቸው እና በከተሞቻቸው ላይ እየደረሰ ካለው መጠነ ሰፊ ውድመት ጋር የሚታገሉት የደቡብ ሊባኖስ ማህበረሰቦች፣ እንዲሁም ቤታቸውን ለቀው ለመውጣት የተገደዱት የሰሜን እስራኤል ነዋሪዎች ሁኔታ በአንድ ጀምበር የማይፈታ እና መፍትሄዎቻቸው ከወታደራዊ ዘመቻዎች ሊገኙ አይችሉም ።” ብሏል፡፡


የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ ሠራዊቱ &quot;ሊባኖስ ውስጥ ከጦርነት ቀጠና ውጭ፣ በሚቆጣጠራቸው አምስት ቦታዎች እንደሚቆይ እና ማንኛውም የሂዝቦላ ጥሰት ቢኖር በኃይል እና ያለማወላወል ርምጃ ለመውሰድ መሥራቱን ይቀጥላል&quot; ብለዋል ።


በኅዳር ወር መጨረሻ የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት፣ በሊባኖስ ከአንድ ዓመት በላይ የቆየውን ጦርነት አስቁሟል። ይህም የተኩስ አቁም ስምምነት ከመደረጉ በፊት በነበሩት ወራት ውስጥ የእስራኤል ወታደሮች ሊባኖስ ውስጥ የምድር ዘመቻ ሲያደርጉ እና በሂዝቦላ ላይ ተደጋጋሚ የአየር ድብደባ አጠናክረው ሲፈጽሙ ቆይተዋል።


የጋዛ ሰርጥ የሃማስ ታጣቂዎች ሰሜን እስራኤል ላይ ጥቃት በመፈጸም 1 ሺሕ 200 የሚጠጉ ሰዎችን ከገደሉ እና 250 ታጋቾችን ከወሰዱ አንድ ቀን በኋላ ታጣቂዎቹ እኤአ ጥቅምት 2023 በርካታ ድንበር ተሻጋሪ ሮኬቶችን መተኮስ ጀምረዋል፡፡


እስራኤል በሃማስ ላይ ባካሄደችው አጸፋዊ ጥቃት ከ48 ሺሕ 200 በላይ ፍልስጤማውያንን ተገድለዋል ሲል የጋዛ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ገልጿል። ሚኒስቴሩ በታጣቂዎችና በሲቪሎች መካከል ያለውን የሟቾችን ቁጥር ለይቶ አላመለከተም፡፡ እስራኤል በበኩሏ ከ17 ሺሕ 000 በላይ ታጣቂዎችን መግደሏን አስታውቃለች።


የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት የመጀመሪያው ምዕራፍ በመጋቢት ወር መጀመሪያ ላይ ያበቃል። እስካሁን ባለው የተኩስ አቁም ስምምነት፣ ሃማስ 24 ታጋቾችን መልቀቁን እና እስራኤል ከ1 ሺሕ በላይ የፍልስጤም እስረኞችን መፍታቷን ያካትታል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7980124.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7980124.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 19 Feb 2025 05:01:02 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/4da74d03-2cd8-408d-bc08-1e383a4e19a6_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሃማስ መደምሰስ እንዳለበት ሩቢዮ ተናገሩ</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ የአሜሪካው የውጪ ጉዳይ ምኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ሃማስ መደምሰስ እንዳለበት ተናገሩ። ሩቢዮ እስራኤሉ ጠቅላይ ምኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋራ በመኾን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሃማስ ተጽእኖ ነፃ የሆነች ጋዛን በተመለከተ ያላቸውን ራዕይ አስተጋብተዋል።


የቪኦኤዋ አራሽ አራባሳዲ ያሰናዳውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/israel-hamas-/7978093.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/israel-hamas-/7978093.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 17 Feb 2025 21:21:28 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/7d2c75d4-7518-4ed6-f9f0-08dd4a817620_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሃማስ ሦስት እስራኤላውያን ታጋቾችን ሲለቅ እስራኤል ተጨማሪ እስረኞችን ፈታች</title>
            <description>ምንም እንኳን ውጥረት እና ስጋት ውስጥ ባለ የተኩስ አቁም ስምምነት መካከል ቢሆኑም፤ እስራኤል ፍልስጤማውያን እስረኞችን ስትፈታ በምትኩ ሃማስ ሦስት ተጨማሪ ታጋቾችን ለቋል።


ከተለቀቁት ታጋቾች አንዱ በደቡባዊ እስራኤል የኪቡትዝ ኒር ኦዝ ነዋሪ የሆነው የ36 ዓመቱ እስራኤላዊ አሜሪካዊ ሳጊ ዴከል ቼን በጎርጎርሳውያኑ ጥቅምት 7 ቀን 2023 በደቡብ እስራኤል በተፈጸመው የሽብር ጥቃት በሃማስ ታጣቂዎች በምርኮ መያዙ ተዘግቧል። 


ሁለተኛ የተለቀቀው ታጋች የ29 ዓመቱ እስራኤል-ሩሲያዊው ሳሻ ትሮፋኖቭ ሲሆን ከእናቱ፣ አያቱ እና እጮኛው ጋር አብሮ ነበር የታገተው፤ አባቱ በእገታው ወቅት ተገድሎበታል። ሦስቱ ሴቶች በቀደሙት የታጋች ልውውጦች ተለቀዋል። ሦስተኛው ታጋች ደግሞ ከወንድሙ ጋር አብሮ መታገቱ የተገለጸው አርጀንቲናዊ ኢየር ሆርን የተሰኘ ግለሰብ መሆኑ ተገልጿል።


ሦስቱ ታጋቾች በጋዛ ካኻን ዩኒስ በሚገኘው ለአለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ተላልፈው ተሰጥተዋል። በተመሳሳይ የተፈቱ ፍልስጤማውያንን የጫነ አውቶቡስ ራማላህ ገብቷል። ሃማስ 369 የሚደርሱ ፍልጤማውያን ዛሬ ቅዳሜ እንደሚለቀቁ አስታውቆ ነበር።


የአሁን የእስረኛ እና የታጋቾች ልውውጥ እ.ኤ.አ በጥር 19/2025 በሁለቱ ወገኖች መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት አካል ሲሆን፤ ስድስተኛው ነው። 


ሃማስ ታጋቾቹን በ369 ፍልስጤማውያን እስረኞች እና እስረኞች እንቀያየራለን ብሏል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/hamas-releases-3-more-israeli-hostages-israel-frees-more-prisoners/7976376.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/hamas-releases-3-more-israeli-hostages-israel-frees-more-prisoners/7976376.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 15 Feb 2025 21:35:50 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/dd1a0595-ebf1-4bf8-e0df-08dd4a81f35f_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሊባኖስ የኢራን መንገደኞች አውሮፕላን ወደ ቤይሩት እንዳይገባ አገደች</title>
            <description>እስራኤል ኢራን የሲቪል ማመላለሻ አውሮፕላኖችን በመጠቀም ለአሸባሪው ሂዝቦላህ ቡድን ገንዘብ ታቀብላለች የሚል ክስ ከአቀረበች ከአንድ ቀን በኃላ፣ ሊባኖስ ማሃን የተሰኘው የኢራን አየር መንገድ ንብረት የሆነ በረራ ወደ ቤይሩት እንዳይገባ አግዳለች።


ሊባኖስ የማረፍ ፍቃድ መከልከሏን ተከትሎም፣ የኢራኑ አየር መንገድ ወደ ቤይሩት ሊያደርገው የነበረውን በረራ አውሮፕላኑ ከመነሳቱ በፊት መሰረዙን፣ የታህራን ኢማም ኮሜይኒ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰኢድ ቻላንድሪ ለኢራን መንግሥት የዜና ወኪል ተናግረዋል።


አንድ የኢራን ጋዜጠኛ ኤክስ በተሰኘው መተግበሪያ ላይ ባጋራው እና የቪኦኤ የፋርስ ቋንቋ አገልግሎት ትክክለኛነቱን ባረጋገጠው የቪዲዮ መረጃ፣ በአውሮፕላኑ ተሳፍረው የነበሩ መንገደኞች ሲጠባበቁ እና ትእግስቱ ያለቀ አንድ ግለሰብ በመቆየቱ ተሰላችቶ ሲጮህ ያሳያል።


የሊባኖስ ሲቪል አቪዬሽን በውሳኔው ዙሪያ ከአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ አርብ እለት ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ አልሰጠም።


ሆኖም መስሪያቤቱ ባወጣው መግለጫ፣ ሊባኖስ መካከለኛው ምስራቅ አየር መንገድ ከተሰኘው ብሔራዊ አየር መንገድ ጋር በመተባበር፣ በታህራን የሚገኙት ዜጎች ወደ ቤይሩት የሚመለሱበትን መንገድ እያመቻቸ መሆኑን ገልጿል።


ሊባኖስ ርምጃውን የወሰደችው የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ አቪቻይ አድራኤ፣ ረቡዕ ዕለት በአረብኛ በሰጡት መግለጫ፣ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጋርድ ኃይል ወደ ቤይሩት የሚበሩ የመንገደኞችን በረራ በመጠቀም ለሂዝቦላህ ገንዘብ ያዘዋውራል በማለት መክሰሳቸውን ተከትሎ ነው።  


ማሃን የተሰኘው የኢራን አየር መንገድ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ለሂዝቦላህ የገንዘብ እና ጦር መሳሪያ ድጋፍ ያደርጋሉ በማለት ማዕቀብ ከጣለችባቸው የኢራን ተቋማት አንዱ ነው።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/lebanon-blocks-iranian-passenger-flight-to-beirut-analysts-cite-israeli-pressure/7975157.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/lebanon-blocks-iranian-passenger-flight-to-beirut-analysts-cite-israeli-pressure/7975157.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Feb 2025 19:01:12 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/ee2fa5c2-639c-4a76-f77b-08dd4a817620_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሃማስ ከእስራኤል ጋራ የተደረሰውን ተኩስ አቁም ስምምነት እንደሚያከብር ቃል ገባ </title>
            <description>አክራሪው  ሃማስ ከእስራኤል ጋራ የተደረሰውን የተኩስ አቁም ውል እንደሚያከብር ዛሬ ሐሙስ ቃል ገብቷል፡፡ ይህ የሆነው ተኩስ አቁሙን ጥሷል በማለት አንዱ ሌላኛውን ወገን እየወነጀሉ ባሉበት እና ጦርነቱ ሊያገረሽ ይችላል የሚል ስጋት በሚሰማበት በዚህ ወቅት ነው፡፡


የሃማስ ቃል አቀባይ አብደል ላቲፍ አል ካኑዋ  “የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲፈርስ አንፈልግም፡፡ ስለዚህም አፈጻጸሙ በጥንቃቄ  ሥራ  ላይ እንዲውል ብርቱ ፍላጎት አለን” ያሉ ሲሆን &quot;ወራሪዋ እስራኤልም ይሄን እንድታረጋግጥ&quot; ብለዋል፡፡  


በተጨማሪም ካኑዋ ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ እና ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሚሰነዘር “የማስፈራራት እና የዛቻ ቋንቋ” የተኩስ አቁም ስምምነቱን አፈጻጸም አያግዝም ብለዋል፡፡


ሃማስ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ እስራኤል በጋዛ የአየር ድብደባ በመፈጸም  እና ርዳታ እንዳይገባ በመገደብ ስምምነቱን ጥሳለች ሲል የከሰሰ ሲሆን፤ ቡድኑ የሚለቀቁት ታጋቾች ለሌላ ጊዜ እንደሚያስተላልፍም ተናግሯል።


ትላንት ረቡዕ እስራኤል ወታደራዊ ተጠባባቂዎቿን ከጠራች በኋላ፤ የሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ የትረምፕን ማስጠንቀቂያ ደግመዋል።


ካትዝ “ሃማስ ታጋቾቹን መልቀቅ ካቆመ የተኩስ አቁሙ አይኖርም፤ ጦርነት ይሆናል ማለት ነው።” ያሉ ሲሆን ጦርነቱ የበለጠ ጠንካራ እንደሚሆን እና “ትራምፕ ለጋዛ ያላቸውን ራዕይ እውን ለማድረግ የሚያስችል ይሆናል” በማለት አክለዋል።


የተኩስ አቁም ስምምነቱ ባለፈው ወር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ፤ በዩናይትድ ስቴትስ በአሸባሪነት የተፈረጀው ሃማስ 21 ታጋቾችን ሲለቅ  በአንጻሩ እስራኤል ከ730 በላይ እስረኞችን መልቀቋ ይታወሳል። የፊታችን ቅዳሜ በሚካሄደው የታጋቾች ልውውጥ በእስራኤል  በመቶዎች በሚቆጠሩ የፍልስጤም እስረኞች ለውጥ ተጨማሪ ሶስት እስራኤላውያን እንዲፈቱ ተጠይቋል።


የጋዛ ጦርነት የተቀሰቀሰው በጎርጎሮሳውያኑ ጥቅምት 2023 ሃማስ በእስራኤል ላይ ባደረሰው የሽብር ጥቃት 1200 ሰዎችን ገድሎ፤ 250 ሰዎችን ማገቱን ተከትሎ ነው ። እስራኤል በፈጸመችው የአጸፋ ጥቃት ከ48 ሺህ 200 በላይ ፍልስጤማውያንን የተገደሉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ሴቶች እና ህጻናት መሆናቸውን የአካባቢው የጤና ባለሥልጣናት አስታውቀዋል፡፡  እስራኤል በበኩሏ ከተገደሉት  ወስጥ 17 ሺህ የሚሆኑት ታጣቂዎች ናቸው ብላለች፡፡


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/israel-hamas-fighting-/7973876.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/israel-hamas-fighting-/7973876.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Feb 2025 20:52:36 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/7a6504ad-e702-4eb7-82de-08dd4a843460_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ትረምፕ ከዮርዳኖስ ንጉሥ ጋር ባደረጉት ውይይት ጋዛን የመቆጣጠር እቅዳቸውን ገፍተውበታል</title>
            <description>ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ፣ የዮርዳኖስ ንጉሥ ዳግማዊ አብዱላህ ጋዛን በመቆጣጠር ፍልስጤማውያንን በዘላቂነት ለመያዝ ያቀዱትን እቅድ እንዲደግፉ ያቀረቡትን ጥያቄ በእጥፍ አሳድገዋል፡፡ የማክሰኞው የዋይት ሀውስ ስብሰባ የተካሄደው በቋፍ ያለው የሃማስ እና የእስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነት ሊፈርስ ይችላል በሚባልበት ወቅት ነው፡፡


የዋይት ሀውስ ቢሮ ዘጋቢ ፓትሲ ዊዳክስዋራ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-jordan-/7972634.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-jordan-/7972634.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Feb 2025 22:59:07 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/424de92d-37d3-47a7-8272-08dd4a843460_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የእስራኤል ሐማስ የተኩስ አቁም ስምምነት ቀጥሏል</title>
            <description>

የእስራኤል ሐማስ የተኩስ አቁም ስምምነት የቀጠለ ሲኾን፣ ዶናልድ ትረምፕ ባላፈው ሳምንት ጋዛን ስለመቆጣጠር የሰጡትን አስተያየት ለተቹ ወገኖች፣ የዩናይትድ ስቴትስ ብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ ማይክ ዋልዝ ፕሬዝደንት ምላሽ ሰጥተዋል። የመካከለኛው ምስራቅ የእስራኤል ሐማስ የእርቅ ስምምነት፣ በእስረኞች ልውውጥ ታጋቾችን የማስለቀቅ ሌላ ስሌት አስገኝቷል። የቪኦኤዋ ቬሮኒካ ባልደራስ ኢግሌሲያስ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/israel-hamas-ceasefir/7969747.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/israel-hamas-ceasefir/7969747.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Feb 2025 22:51:29 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/56b396d7-1cea-44ca-6d03-08dd481b3e99_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>እስራኤልና ሐማስ ተጨማሪ የታጋቾች እና እስረኞች ልውውጥ አደረጉ</title>
            <description>ሐማስ ተጨማሪ ሶስት እስራኤላዊያንን ሲለቅ፣ እስራኤል 183 ፍልስጤማውያን እስረኞችን ለቀቀች።


በተኩስ ማቆም ስምምነቱ መሠረት የተለቀቁት እስራኤላውያን የገረጡና የተዳከሙ መሆናቸው ተዘግቧል። የእስራኤላውያኑ ገርጥቶ መታየት እና ሐማስ በሚልቀቁበት ወቅት ያዘጋጀው ሥነ ሥርዓትና ንግግር እንዲያደርጉ ማስገደዱ፣ በእስራኤል በርካቶችን አስቆጥቷል ተብሏል። ለስድስት ሳምንት የታቀደውን የመጀመሪያ ደርጃ የተኩስ አቁም ስምነት እንዲያራዝሙም በእስራኤሉ ጠቅላይ ምኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ላይ ግፊት እንዲጨምር ያደርጋልም ተብሏል።


ሐማስ እስከ አሁን 13 እስራኤላውያን ታጋቾች እና ሶስት የታይላንድ ሠራተኞችን ሲለቅ፣ እስራኤል ደግሞ በአብዛኛው ፍልስጤማውያን የሆኑ 600 እስረኞችን ለቃለች፡፡ በስድስት ሳምንቱ የመጀመሪው ደረጃ ስምምነት 33 እስራኤላውያን ታጋቾችና በመቶ የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን እስረኞች እንደሚለቀቁ ይጠበቃል።


የዛሬው ልውውጥ የመጣው የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ከጋዛ ነዋሪዎች እንዲወጡ ተደርገው ሠርጡን አሜሪካ በባለቤትነት ትያዝ የሚለውን ሃሳባቸውን እየገፉ ባለበት ወቅት ነው።


የትረምፕን ሃሳብ የአሜሪካ አጋሮችም ሆኑ ባላንጣ የሆኑ ሃገራት ሲቃወሙት፣  ቤንጃሚን ኔታንያሁ ግን “ከረዥም ከዓመታት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የቀረበ አዲስ ሃሳብ” ሲሉ አሞካሽተውታል።


 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7967873.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7967873.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 08 Feb 2025 18:51:25 +0300</pubDate>
            <category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/62f10e18-fb29-43fd-8901-9d3301a4cc11_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>