<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>አፍሪካ - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/3169</link>
        <description>አፍሪካ, Africa </description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>አፍሪካ - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/3169</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Wed, 08 Apr 2026 19:11:23 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zkbgql-vomx-tpejvbq" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>የባለ ሥልጣናት መፈታት ለደቡብ ሱዳን ውጥረት መርገብ ቁልፍ ጉዳይ ነው ተባለ</title>
            <description>የደቡብ ሱዳን መንግሥት በሀገሪቱ የተፈጠረውን ውጥረት ተከትሎ የታሰሩ ባለሥልጣናትን እንዲፈታ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አባል ሀገራት መሪዎች ጥሪ አቅርበዋል።
የኢጋድ አባል ሀገራት ይኼንኑ የደቡብ ሱዳን ግጭት አስመልክተው ረቡዕ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም በበይነ መረብ ባደረጉት ስብሰባ የደቡብ ሱዳን መሪዎች ውጥረቱን ለማርገብ ውይይት እንዲጀምሩም ጠይቀዋል።
በደቡብ ሱዳን የጁባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር የኾኑት ፕሮፌሰር መልሃ ራውት ውጥረቱ የባለሥልጣናቱ መፈታት ውጥረቱን ለመርገብ መወሰድ ካለባቸው ቁልፍ ርምጃዎች አንዱ መኾኑን ገልጸዋል።
በአገሪቱ የቀጠለው የፀጥታ ችግር ዋነኛ ምክንያት ግን እ.አ.አ. በ2018 የተፈረመው የሰላም ስምምነት አተገባበር መጓተት መኾኑን ጠቅሰዋል።


</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/south-sudan-call-for-de-escalation/8011031.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/south-sudan-call-for-de-escalation/8011031.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 22:43:34 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/334741c0-bd9e-4b26-099c-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአፍሪካ የኅይል አቅርቦት ላይ ያተኮረውና በዋሽንግተን ዲሲ የተካሔደው ጉባኤ</title>
            <description>የአሜሪካ መንግሥት ባለሥልጣናት፣ የአፍሪካ ምኒስትሮች፣ ኢንቨስተሮች፣ የግል ገንዘብ አበዳሪዎች፣ እንዲሁም የአገልግሎትና የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች ዓመታዊ ለሆነውና በአፍሪካ የኅይል አቅርቦት ላይ በሚያተኩረው ጉባኤ ላይ ባለፈው ሳምንት በዋሽንግተን ዲሲ ተገናኝተው ነበር።
“መፃኢው የአሜሪካ እና የአፍሪካ የኅይል ትብብር” በተሰኘ መሪ ቃል በተካሄደው ጉባኤ፣ በአዲሱ የትረምፕ አስተዳደር የአሜሪካ መንግሥትም ሆነ የግል ኩባንያዎች የአፍሪካን የኤሌክትሪክ ኅይል ልማት፣ መሠረተ ልማት እንዲሁም የማዕድን ሃብትን በተመለከተ ያላቸውን ተሳትፎ እንደገና ለማዋቀር፣ የአሜሪካ ባለሥልጣናትና የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች ተወካዮች መክረዋል። 
የቪኦኤው አንተኒ ላብሩቶ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/labruto-us-africa-energy/8011019.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/labruto-us-africa-energy/8011019.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 22:40:33 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/f6e4fa2b-1590-4be5-09b6-08dd5c8b1668_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቆዳ ላይ ቀላል እብጠት መሰል ነገሮች እና የቆዳ ቀለምን የሚለውጡ ምልክቶች ለጤና ያሳስቡ ይኾን?</title>
            <description>በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የቆዳ ቀለምን የሚለውጡ ፣በእንግሊዝኛው አጠራር ‘ሞሎች’ በአንዳንድ ባህሎች ዘንድ እንደ ውበት ምልክት ይታያሉ። በተለይ የጥቁር ዝርያ ባላቸው ሕዝቦች ውስጥ፣ በስፋት የሚታዩና የተለመዱ ናቸው።
በአንጻሩ፣ ለጤና መታወክ ይዳርጉ ይኾን? በሚል ለጭንቀት የሚጋለጡ ወገኖች የሚሰሟቸውን ስጋቶች የሚያነሣው ጁማ ማጃንጋ፣ ለእነዚኽ እና ተያያዥ ጥያቄዎች ምላሽ ፍለጋ፣ ከናይሮቢ ኬንያ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/kenya-moles-and-skin-tags-tv-headline-skin-tags-and-moles-/8010760.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/kenya-moles-and-skin-tags-tv-headline-skin-tags-and-moles-/8010760.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 18:12:12 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/6b63bcf5-b100-4ef6-0fa4-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሶማሊያ ሆቴል ከበው ያጠቁት እና ሌሎች 50 የአልሸባብ ታጣቂዎች ተገደሉ</title>
            <description>በሶማሊያ የጸጥታ ኅይሎች በማዕከላዊ ቤለድዌን ከተማ የሚገኘውን ሆቴል ከበው ያጠቁትን ስድስቱን ታጣቂዎች መግደላቸውንና በኋላም ቢያንስ 50 የአልሸባብ ታጣቂዎች የአየር ጥቃት መገደላቸውን አስታወቁ፡፡
የቤለድዌን ወረዳ ኮሚሽነር ኦማር ኦስማን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በሆቴሉ ላይ የተፈጸመው የከበባ ጥቃት ዛሬ ረቡዕ ጧት ማብቃቱን አረጋግጠዋል።
ኮሚሽነሩ “የጸጥታ ኃይሎቻችን የሀገር ሽማግሌዎችና የጸጥታ ሃላፊዎች እየተገናኙ በሚመክሩበት ሆቴል ላይ ጥቃት ያደረሱ ስድስት ታጣቂዎችን በተሳካ ሁኔታ አስወግደዋል&quot; ብለዋል።
በዩናይትድ ስቴትስ በአሸባሪነት የተፈረጀው አልሸባብ ትላንት ማክሰኞ ለደረሰው የሆቴል ጥቃት ኃላፊነቱን ወስዷል።
በአፍሪካ ኅብረት ወታደሮች የሚደገፉት የመንግሥት ወታደሮች ሆቴሉ ውስጥ በታጣቂዎቹ የተከበቡትን የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወታደራዊ መኮንኖችን እና ሰላማዊ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/somalia-al-shabab-attack/8008367.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/somalia-al-shabab-attack/8008367.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 20:58:14 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/1497785a-dcdc-4c61-a007-4467888536cd_cx0_cy6_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የደቡብ ሱዳን መሪዎች በአስቸኳይ ውይይት እንዲጀምሩ ጥሪ ቀረበ</title>
            <description>በደቡብ ሱዳን ግጭት እየተሳተፉ የሚገኙ ሁሉም ወገኖች ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ግጭት እንዲያቆሙና የአገሪቱ መሪዎችም በአስቸኳይ ውይይት እንዲጀምሩ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ጥሪ አቀረበ።
የአባል ሀገራት መሪዎች ይኼንኑ የደቡብ ሱዳን ግጭት አስመልክተው ዛሬ በበይነ መረብ ባደረጉት ስብሰባ መክፈቻ ላይ የተናገሩት የኢጋድ ዋና ጸሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ውይይቱ ከኢጋድ አባል አገራት መሪዎች መካከል በአንዳቸው ሊመቻች እንደሚችል ጠቅሰዋል።
የደቡብ ሱዳን መንግሥት የታሰሩ ባለሥልጣናትን በፍጥነት እንዲፈታም ጥሪ አቅርበዋል ።
ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝደንት ሪክ ማቻር ጋራ ጥብቅ ግንኙነት ያለው የታጠቀ ቡድን፤ በደቡብ ሱዳን አፐር ናይል ግዛት፣ ናስር አካባቢ በሚገኝ የጦር ሠፈር ላይ ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ፣ በርካታ የምክትል ፕሬዝደንቱ አጋሮች...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/igad-south-sudan-summit/8008032.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/igad-south-sudan-summit/8008032.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 17:28:42 +0300</pubDate>
            <category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0e6565b8-ed50-4726-066c-08dd5c8b1668_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዩጋንዳ በደቡብ ሱዳን ልዩ ኃይሏን አሰማራች</title>
            <description>በደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር እና በተቀዳሚ ምክትላቸው ሪክ ማቻር መካከል የተፈጠረው አለመግባባት፤ ሀገሪቱን ወደ እርስ በርስ ጦርነት ሊመልሳት ይችላል የሚለው ስጋት እያየለ መሄዱን ተከትሎ፣ ዩጋንዳ ልዩ ኃይሏን በዋና ከተማዋ ጁባ ማሰማራቷን የኡጋንዳ ጦር አዛዥ ትላንት ማክሰኞ አስታወቁ።
ነዳጅ አምራች በኾነችው ደቡቡ ሱዳን የኪር መንግሥት ሁለት ሚኒስትሮችን እና በርካታ ከፍተኛ ወታደራዊ ባለሥልጣናትን ማሰሩን ተከትሎ ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል።
በጁባ የተካሄደው እስር እና በሰሜናዊው ናሲር ከተማ የተቀሰቀሰው ግጭት፣ በኪር እና በማቻር ታማኝ ኃይሎች መካከል የተካሄደውን እና ወደ 400 ሺህ ለሚጠጉ ሰዎች ህልፈት ምክንያት የሆነውን የእርስ በርስ ጦርነት ለማስቆም እ.አ.አ በ2018 የተፈረመውን የሰላም ስምምነት አደጋ ላይ እንደሚጥል ተገልጿል።
የኡጋንዳ የጦር አዛዥ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8007654.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8007654.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 11:40:34 +0300</pubDate>
            <category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/ef05245f-3f0a-42f9-8fb4-08dd5b02d8d7_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በማዕከላዊ ሶማሊያ ታጣቂዎች በለድዌን ከተማ የሚገኝ ሆቴል አጠቁ</title>
            <description>ማዕከላዊ ሶማሊያ በለድዌን ከተማ ውስጥ ታጣቂዎች ዛሬ ማክሰኞ የአገር ሽማግሌዎች እና የመንግሥት ባለሥልጣናት ስብሰባ ላይ የነበሩበትን ሆቴል  ወረዋል። ሆቴሉ አሁንም በታጣቂዎቹ እንደተወረረ መሆኑን ዕማኞች እና ሆቴሉ ውስጥ ያሉት ሰዎች ቤተሰቦች ተናግረዋል።
የበለድዌን ከተማ የፌዴራል መንግሥት ባለሥልጣን የሆኑት ዳሂር አሚን ጄሶው &quot;እስከአሁን ባወቅነው መሠረት ቢያንስ አራት ሰዎች ተገድለዋል&quot; ማለታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል። ፅንፈኛ እስላማዊው ታጣቂ ቡድን አልሻባብ  ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ ሲኾን ከዐስር የሚበልጡ ሰዎች ገድለናል ብሏል።
አሊ ሱሊማን የተባሉ ባለመደብር &quot;መጀመሪያ ኃይለኛ ፍንዳታ ሰማን። ከዚያም ተኩስ ቀጠለ። እንደገና ሌላ ፍንዳታ ተደገመ&quot; ማለታቸውን ሮይተርስ ጠቅሷል።  ታጣቂዎቹ እና የመንግሥቱ  ኃይሎች እየተታኮሱ ያሉበት ካሂራ ሆቴል በከፊል መፈራረሱን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/gunmen-storm-hotel-in-central-somalia-siege-ongoing/8006661.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/gunmen-storm-hotel-in-central-somalia-siege-ongoing/8006661.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 17:07:09 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/36a514dd-3318-4fea-8863-1e8158b012af_cx0_cy4_cw0_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አሜሪካ የምትሰጠው የውጭ ርዳታ መቀነሱ በአፍሪካ ገዳይ የሆነውን በሽታ ለመዋጋት የሚደረገውን ትግል  እንዳዳከመው ተገለጸ</title>
            <description>ይኽ ወር በአብዛኛው የአፍሪካ አካባቢ የወባ በሽታ የሚጀምርበት ወቅት ነው። በአህጉሩ ደግሞ እንደወባ በከፍተኛ ሁኔታ ገዳይ የሆነ በሽታ የለም፣ በተለይ ደግሞ ለሕፃናት።


የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር 90 ከመቶ የሚደርሰውን የአሜሪካ አለማቀፍ የልማት ድርጅት (ዩኤስኤይድ) የውጭ ርዳታ ውሎች ለማቋረጥ መወሰኑ ታዲያ የወባ በሽታ ስርጭትን በከፍተኛ ሁኔታ ሊጨምር ከፍተኛ ጥፋት ሊያስከትል እንደሚችል የአህጉሩ የሕክምና ባለሞያዎች እያስጠነቀቁ ነው።


በሌላ በኩል፣ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዬ ዛሬ ሰኞ በኤክስ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፣ የትራምፕ አስተዳደር ላለፉት ስድስት ሳምንታት የዩኤስኤይድ አብዛኛውን ፕሮግራም የመዝጋት ሥራ ማጠናቀቁን እና ከመዘጋት የተረፈው 18 ከመቶ የርዳታ እና ልማት ፕሮግራም በውጭ ጉዳይ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/african-affairs-uganda-malaria-usaid/8005670.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/african-affairs-uganda-malaria-usaid/8005670.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 21:49:19 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/85f2fd33-b60b-4b96-0ab8-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዩናይትድ ስቴትስ የመንግሥት ሠራተኞች ከደቡብ ሱዳን እንዲወጡ አዘዘች</title>
            <description>ዩናይትድ ስቴትስ ደቡብ ሱዳን ውስጥ እየታየ ያለው ውጥረት እየበረታ በመምጣቱ፣ ከአስቸኳይ ጊዜ ሠራተኞች ውጪ ያሉ የመንግሥት ሠራተኞች ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ አዘዘች።  


የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ፣ ዛሬ በአወጣው የአስቸኳይ ጊዜ የጉዞ ማስጠንቀቂያ፣ በደቡብ ሱዳን ጦርነቱ መቀጠሉንና፣ ሕዝብ በቀላሉ ሊያገኛቸው የሚችላቸው የጦር መሳሪያዎች መኖራቸውን በማመላከት፣ የአስቸኳይ ጊዜ ሠራተኞች ያልኾኑ የመንግሥት ሠራተኞች በሙሉ ከደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ እንዲወጡ አዟል።


ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝደንት ሪክ ማቻር ጋራ ጥብቅ ግንኙነት ያለው የታጠቀ ቡድን ማክሰኞ ዕለት በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል የሚገኝ የጦር ሰፈር ላይ ወረራ ማካሄዱን ተከትሎ፣ ለማቻር ታማኝ የነበሩት የጦሩ ምክትል አዛዥ ጀነራል ጋብሪኤል ዱፕ ላም እና ሁለት ሚኒስትሮች ለእስር...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8004349.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8004349.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 09 Mar 2025 20:32:08 +0300</pubDate>
            <category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/ef05245f-3f0a-42f9-8fb4-08dd5b02d8d7_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በየመንና ጅቡቲ ጀልባዎች ሰጥመው ፍልሰተኞች መሞታቸውንና በርካቶች የደረሱበት አለመታወቁን ተመድ አስታወቀ </title>
            <description>የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፍልሰተኞች ኤጀንሲ እንደገለፀው በየመንና ጅቡቲ የባህር ዳርቻ አራት የፍልሰተኞች ጀልባዎች ሰጥመው ሁለት ሰዎች ሲሞቱ 186 የሚሆኑት ደግሞ የደረሱበት አልታወቀም።


የዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) ቃል አቀባይ ታሚም ኤሊየን እንዳሉት ሁለት ጀልባዎች በየመን ባህር ላይ የሰጠሙት ሀሙስ ምሽት ሲሆን የጠፉት 181 ፍልሰተኞችና አምስት የየመን የጀልባው ሰራተኞች መሆናቸውን ለአሶሼትድ ፕሬስ ተናግረዋል። ሁለት የጀልባው ሰራተኞችን ማትረፍ ተችሏል ብለዋል፡፡


ሌሎች ሁለት ጀልባዎች ደግሞ በትንሿ አፍሪካዊቷ ሀገር ጅቡቲ በተመሳሳይ ሰዓት ላይ ሰጥመዋል ሲሉ ተናግረዋል። የሁለት ፍልሰተኞች አስከሬን የተገኘ ሲሆን በጀልባው ውስጥ የነበሩ ሌሎች ሰዎችንም ማትረፍ መቻሉን ገልጸዋል፡፡


በደቡብ ምእራብ የመን ታይዝ ግዛት በዱባብ ወረዳ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un-says-186-missing-and-at-least-2-dead-after-migrant-boats-capsize-off-yemen-and-djibouti-/8003609.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un-says-186-missing-and-at-least-2-dead-after-migrant-boats-capsize-off-yemen-and-djibouti-/8003609.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 08 Mar 2025 18:01:12 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/47136772-2e26-4d42-85e6-9a1f132ed136_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በብዙ አገሮች የሽብር ጥቃቶች እየበረከቱ በመጡበት አፍሪካ አስከፊ ጥቃቶችን ማስተናገዷ ተዘገበ</title>
            <description>ባለፈው ዓመት በዓለም እጅግ አውዳሚ መሆኑ የተነገረለት የአሸባሪዎች ጥቃት በአፍሪካ ሲፈፀም፤ የዓለም የምጣኔ ሃብት እና የሰላም ተቋም ይፋ ያደረገው የ2025 የዓለም አቀፍ የሽብር ጥቃቶች ጠቋሚ ሪፖርት እንዳመለከተው፤ በአጠቃላይ ከሽብር ጋር ከተዛመዱ ግድያዎች ከገሚስ በላይ የሚሆኑት የተፈጸሙት የዓለም አቀፍ የሽብር ጥቃቶች መናሃሪያ ሆኖ በቆየው የሳሕል ክልል ነው።


በሁለት ሀገራት የደረሱትን 3 አደገኛ የሽብር ጥቃቶች ጨምሮ በዓለም ዙሪያ ከተዘገቡት 20 ያህል እጅግ የከፉ ጥቃቶች ውስጥም 17ቱ የተፈጸሙት በአፍሪካ ነው። ባለፈው ዓመት በሰኔ፣ በሀምሌ እና በነሀሴ ወር በኒጀር እና ቡርኪና ፋሶ የተፈጸሙት ጥቃቶች ለ607 ሰዎች ህይወት መጥፋት ምክኒያት መሆናቸውን አክሎ ዋና መሥሪያ ቤቱን በአውስትራሊያ ያደረገው ይሄው የጥናት ቡድን አረጋግጧል።


በዚሁ ዓመት በሳህል...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/africa-global-terrorism/8002890.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/africa-global-terrorism/8002890.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 Mar 2025 22:55:00 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሃሩን ማሩፍ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/efe6cbcf-315a-498b-024b-08dd5c8b1668_cx42_cy14_cw36_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሩቶና ኦዲንጋ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ</title>
            <description>የኬንያው ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ ከቀድሞው ዋና ተፎካካሪያቸው ከራይላ ኦዲንጋ ጋራ በፖለቲካ ጉዳዮች ትብብር ለማድረግ ስምምነት ተፈራርመዋል።


ሁለቱ ወገኖች እየጨመረ ያለውን የሃገሪቱን ዕዳ እና ሙስናን ጨምሮ ሌሎቹንም ሃገሪቱን የገጠሟትን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ አብረው ለመሥራት ተስማምተዋል።


ሩቶ የግብር ጭማሪ እንደሚያደርጉ ማስታወቃቸውን ተከትሎ በሃገሪቱ በተነሳው ተቃውሞ ቢያንስ 60 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። የነበራቸው የሕዝብ ድጋፍም እያሽቆለቆለ መጥቷል።


ተቃውሞው በመበርታቱም ሩቶ ከተቃዋሚያቸው ከኦዲንጋና ከበርካታ የፓርቲ አባሎቻቸው ጋራ”ሰፊ መሠረት ያለው” መንግሥት ለመመስረት እንዲሠሩ አስገድዷቸዋል። ይህንን ስምምነትም ዛሬ በይፋ በመፈረም ሃገሪቱ የገጠማትን ችግሮች ለመቅረፍ በጋራ እንደሚሠሩ አስታውቀዋል።


ጉምቱ የተቃዋሚ ፖለቲከኛው ራይላ ኦዲንጋ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/kenya-ruto-odinga/8002781.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/kenya-ruto-odinga/8002781.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 Mar 2025 22:07:56 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/953a171d-a1a9-41fc-2e58-08dd5c897904_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፍልሰተኞችን የያዙ አራት ጀልባዎች ሰመጡ</title>
            <description> ካይሮ — ፍልሰተኞችን የያዙ አራት ጀልባዎች በየመንና ጂቡቲ ባህር ዳርቻ ሰምጠው ቢያንስ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ 186 የሚሆኑት የደረሱበት እንደማይታወቅ የዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) አስታውቋል።


አደጋው የደረሰው ትላንት ሐሙስ ምሽት ሲኾን፣ በባህረ ሰላጤው ሀገራት ሥራ ለማግኘትና ከግጭት ለመሸሽ ኢትዮጵያን በሚጠቀሙበት የጉዞ መሥመር ላይ እንደኾነም የአጃንስ ፍራንስ ፕረስ ዘገባ አመልክቷል።


በየመን ዳርቻ ከሰመጡት ጀልባዎች በአንደኛው ላይ 150 ኢትዮጵያውያንና አራት የጀልባው ሠራተኞች ተሳፍረው የነበረ ሲሆን፣ በሌላኛው ጀልባ ላይ ደግሞ 31 ኢትዮጵያውያንና ሦስት የመናውያን የጀልባው ሠራተኞች ተሳፍረው እንደነበር ታውቋል።


አሶስዬትድ ፕረስ በበኩሉ በየመን ዳርቻ የሰመጡት ሁለት ጀልባዎች ሠራተኞች ከአደጋው ሲድኑ፣ 181 ፍልሰተኞችና አራት የመናዊ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/yemen-migrants/8002549.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/yemen-migrants/8002549.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 Mar 2025 19:43:21 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP, ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a8ecce85-8152-47be-2e13-08dd5c897904_cx0_cy7_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሶማሊያ ፑንትላንድ እስላማዊ መንግሥት እያፈገፈገ ነው </title>
            <description>ዋሽንግተን  — ሶማሊያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የእስላማዊ መንግሥት ቡድን ታጣቂዎች፣ ከፑንትላንድ ጦር ጋር ለሁለት ወራት ካደረጉት ተከታታይ ውጊያ በኋላ፣ እንዲያፈገፍጉ ማድረጉን የክልሉ ባለሥልጣናት ተናግረዋል።


ባለፈው ሳምንት የፑንትላንድ ጦር  በቡክ ካሌድ የቡድኑን አሚር አብዱልቃድር ሙሚን ዋና መሥሪያ ቤት በቁጥጥር ስር አውሏል።


የአካባቢው ባለሥልጣናት በኩራ መንደር አቅራቢያ በተካሄደ ውጊያ 15 ወታደሮች መሞታቸውን ገልጸው፣ አይ ኤስ የሞቱበትን 57 ተዋጊዎች ጥሎ መሸሹን አስታውቀዋል፡፡


ከሳምንት በኋላ አይ ኤስ ወይም አይሲስ ተብሎ የሚጠራው የሽብር ቡድን ተጨማሪ አጥፍቶ ጠፊዎችን እና አዲስ ተዋጊዎችን ይዞ በሸለቆው አካባቢ መልሶ ማጥቃት ጀምሮ እንደነበር ባለሥልጣናቱ ገልጸዋል፡፡


የፑንትላንድ ጦር የሽብር ቡድኑን ሦስት የጦር ሰፈሮችን ከመቆጣጠሩ በፊት፣...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/islamic-state-in-retreat-after-offensive-in-somalia-puntland/8001435.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/islamic-state-in-retreat-after-offensive-in-somalia-puntland/8001435.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 06 Mar 2025 21:41:33 +0300</pubDate>
            <category>አፍሪካ</category><category>ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/98859bb0-302a-4816-87bc-6590accaeeb6_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ግብፅ ለትረምፕ የጋዛ እቅድ ያቀረበችውን አማራጭ አቅድ የአረብ መሪዎች መደገፋቸውን አስታወቀች</title>
            <description>የአረብ መሪዎች፤ ግብጽ በ53 ቢሊየን ዶላር ወጪ ጋዛን መልሶ ለመገንባት ያቀረበችውን ዕቅድ ትላንት ማክሰኞ  አፅድቀዋል። እቅዱ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለግዛቲቱ ካቀረቡት እቅድ በተለየ ፍልስጤማውያን ከአካባቢያቸው እንዳይፈናቀሉ ለማድረግ የሚያስችል ነው።


የግብፅ እቅድ ካይሮ ውስጥ በተካሄደው የመሪዎቹ ጉባዔ የመዝጊያ ስነ ስርዓት ላይ ተቀባይነት ማግኘቱን ፕሬዝደንት አብደል-ፈታህ አል ሲሲ ገልጸዋል።


በግብፅ አስተናጋጅነት በተደረገው ስብሰባ ላይ የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ምክትል ፕሬዝዳንት፣ የካታር አሚር እና የሳዑዲ አረብያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተገኝተዋል።


ትረምፕ  ፍልስጤማውያንን ከጋዛ ውጪ አስፍሮ  ሰርጡን መልሶ ለመገንባት ባለፈው ጥር ወር ላቀረቡት እቅድ አማራጭ ሆኖ የቀረበው የግብፅ እቅድ፣ ፍርስራሹ እስኪወገድ እና የተቀበሩ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/egypt-says-arab-leaders-endorse-counterproposal-to-trump-s-gaza-plan/7998939.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/egypt-says-arab-leaders-endorse-counterproposal-to-trump-s-gaza-plan/7998939.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 05 Mar 2025 21:13:16 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/d049eb7c-7154-4932-8f6a-08dd5b02d8d7_cx0_cy5_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የደቡብ ሱዳን ጦር የምክትል ፕሬዝደንቱን ቤት ከቧል</title>
            <description>ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝደንት ሪክ ማቻር ጋር ጥብቅ ግንኙነት ያለው የታጠቀ ቡድን፤ በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል የሚገኝ የጦር ሠፈር  መውረሩን ተከትሎ፣ የመንግሥቱ ወታደሮች ዛሬ በዋና ከተማዋ ጁባ የሚገኘውን የምክትል ፕሬዝደንቱን መኖሪያ ቤት ከበዋል፡፡ በርካታ አጋሮቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል።


ማቻር፤ ባለፈው ወር የመንግሥት ባለስልጣን የነበሩ በርካታ አጋሮቻቸው  መባረራቸው እ.አ.አ በ2018 በእሳቸው እና በፖለቲካ ተቀናቃኛቸው ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት አደጋ ላይ ይጥላል ብለው ነበር። በሁለቱ ተቀናቃኞች መካከል ለአምስት ዓመታት በተካሄደው የእርስ በእርስ ጦርነት ከ400 ሺህ በላይ ሰዎች ተገድለዋል።


ለማቻር ታማኝ የነበሩት የጦሩ ምክትል አዛዥ ጀነራል ጋብሪኤል ዱፕ ላም በሰሜኑ ግዛት ከተከሰተው ግጭት ጋር በተያያዘ ትላንት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7998843.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7998843.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 05 Mar 2025 20:10:19 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/dfc62e3d-c828-4bb7-9666-e8e36aa0584e_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኮንጎ ግጭት ምክንያት ጀርመን ለሩዋንዳ የምትሰጠውን አዲስ ርዳታ አቆመች</title>
            <description>ጀርመን ለሩዋንዳ የምትሰጠውን አዲስ የልማት ርዳታ ማቆሟን እና ቃል የገባቻቸውን ድጋፎችም እየገመገመች መኾኑን ዛሬ ማክሰኞ አስታውቃለች።


ጀርመን ይህን ርምጃ የወሰደችው፣ ሩዋንዳ በጎረቤቷ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በሚካሄደው ግጭት ውስጥ ላላት ሚና ምላሽ ለመስጠት ነው።


የጀርመን ልማት ምኒስትር ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ በርሊን ውሳኔዋን አስቀድማ ለሩዋንዳ ማሳወቋን እና በምስራቅ ኮንጎ የበላይነት እያገኘ ላለው የኤም 23 አማፂ ቡድን የምትሰጠውን ድጋፍ እንድታቆም ማሳሰቧን አመልክተዋል።


ኮንጎ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባለሞያዎች እና የምዕራብ ኃያላን ሀገሮች ሩዋንዳ አማፂውን ቡድን ትደግፋለች በማለት ይከሷታል።


ክሱን የምትቃወመው ሩዋንዳ በበኩሏ በኮንጎ የቱትሲ ተወላጆችን ለመጨፍጨፍ እና ለሩዋንዳ ስጋት ለመፍጠር ከሚንቀሳቀሱ የሁቱ ተወላጅ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/germany-stops-new-aid-to-rwanda-over-dr-congo-conflict/7998693.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/germany-stops-new-aid-to-rwanda-over-dr-congo-conflict/7998693.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 05 Mar 2025 18:06:50 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/10e8d71f-7f1d-49ee-a311-e3d0ae62ff72_cx0_cy8_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title> ኬንያ ውስጥ በስደተኞች የምግብ ዕደላ ወቅት በተቀሰቀሰ ግጭት ተረጂዎች ተጎዱ</title>
            <description>ሰሜን ኬንያ በሚገኘው ካኩማ የስደተኞች መጠለያ ካምፕ በተቃውሞ እንቅስቃሴ ወቅት ፖሊስ በወሰደው ርምጃ አራት ሰዎች መቁሰላቸው ተገለጸ።


በትላንቱ የምግብ ዕደላ ላይ የተቀሰቀሰው ግጭት ለስደተኛው ከሚሰጠው የምግብ ርዳታ እጥረት ጋራ የተያያዘ መኾኑም ተመልክቷል።


ከኬንያ አጎራባቾች ደቡብ ሱዳን፣ ኢትዮጵያ፣ ቡሩንዲ እና ኮንጎ ግጭቶችን በመሸሽ እና በድርቅ ሳቢያ የሚሰደዱ ወገኖችን በሚያስጠልለው ካምፕ ውስጥ ለሚገኙት በብዙ ሺሕዎች የሚገመቱ ስደተኞች ይሰጥ የነበረው የምግብ አቅርቦት፤ በተፈጠረው የርዳታ ገንዘብ እጥረት የተነሳ የወትሮ አሠራሩ መስተጓጎሉ ተዘግቧል።


በካምፑ ለስደተኞች የሚሰጠውን ምግብ የሚያከፋፍለው የዓለም የምግብ ፕሮግራም ባለፈው ታኅሣሥ ወር ለስደተኞች ከሚሰጠው ምግብ &quot;በገጠመው የአቅርቦት እጥረት የተነሳ ከሚያስፈልገው ከ45 በመቶ በታች እንደነበር...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/refugees-injured-in-clashes-with-kenyan-police-during-food-ration-protests/7997332.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/refugees-injured-in-clashes-with-kenyan-police-during-food-ration-protests/7997332.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 04 Mar 2025 20:05:18 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/b1549a9c-982c-4180-96f4-787e01a4e6f6_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ግዛቷ ውስጥ &quot;20 የሁቱ አማጽያን ተያዙ&quot; የተባለው የሐሰት ወሬ ነው&quot; አለች </title>
            <description>የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጦር ከሩዋንዳው የዘር ማጥፋት ወንጀል ጋራ ግንኙነት ያላቸው 20 ተዋጊዎች ግዛቱ ውስጥ ተይዘዋል መባሉን  አስተባብሏል።  አማጽያኑ ለሩዋንዳ ተላልፈው ሲሰጡ የሚያሳይ ተብሎ የወጣውን  ቪዲዮ “በሐሰት የተቀነባበረ ” ሲል ትላንት እሑድ ባወጣው መግለጫ አጣጥሏል።


መግለጫው የወጣው በምሥራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የሚንቀሳቀሰው የኤም 23 ታጣቂ ቡድን በጎርጎሮሳውያኑ 1994 በሩዋንዳ የቱትሲዎች የዘር ማጥፋት ወንጀል በተሳተፉ የሁቱ ጎሳ አባላት የተቋቋመው የሩዋንዳ ነፃ አውጪ ዲሞክራሲያዊ ኅይል (ኤፍ.ዲ.ኤል.አር) ተዋጊዎችን መያዙን ቅዳሜ ዕለት ማስታወቁን ተከትሎ ነው።


የኮንጐ ጦር ኅይሎች አዛዥ  ባወጡት መግለጫ “ይህ የእኛን ሠራዊት ስም ለማጥፋት የተቀነባበረ፤  የውሸት ድርጊት ነው” ብለዋል።


አክለውም “ሩዋንዳ የዲሞክራቲክ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/dr-congo-says-handover-of-20-alleged-hutu-rebels-was-staged/7995545.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/dr-congo-says-handover-of-20-alleged-hutu-rebels-was-staged/7995545.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 03 Mar 2025 21:31:56 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/29EC2571-6016-4806-AD0B-B6FBCE29D7A6_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአፍሪካ ከአየር ንብረት ጋራ የተያያዙ አደጋዎችን ለመቀነስ የሚረዳ ዝግጁነት ላይ እየተሠራ ነው</title>
            <description>የአፍሪካ ቀንድ ሀገራትን የሚያጋጥሙ ከአየር ንብረት ጋራ የተያያዙ አደጋዎች ከጊዜ ወደጊዜ እየተበራከቱ መጥተዋል፡፡ በመኾኑም የቀጣናውን ሀገራት ያሰባሰበው  ኢጋድ ሀገራቱ  ከሰብአዊ ረድዔት ተቋማት ጋራ በመኾን የአደጋ ዝግጁነት መርሐ ግብሮችን  በማሰናዳት ላይ ይገኛል፡፡ ዓላማውም በስምንቱም የቀጣናው ሀገራት የአደጋ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዐቶች በመዘርጋት  አደጋዎች ቢከሰቱ  የሚደርሱ ጉዳቶችን  ለመቀነስ እንዲቻል መኾኑን ከናይሮቢ በጁማ ማጃንጋ ያደረሰን ዘገባ አውስቷል፡፡


ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/african-affairs-africa-disaster-preparedness/7995462.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/african-affairs-africa-disaster-preparedness/7995462.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 03 Mar 2025 20:50:11 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/512db885-d0d7-470b-0707-08dd4a817621_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>