<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>አፍሪካ - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/3169</link>
        <description>አፍሪካ, Africa </description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>አፍሪካ - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/3169</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Sat, 25 Apr 2026 04:21:06 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zk$gqemtjq" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>የባለ ሥልጣናት መፈታት ለደቡብ ሱዳን ውጥረት መርገብ ቁልፍ ጉዳይ ነው ተባለ</title>
            <description>የደቡብ ሱዳን መንግሥት በሀገሪቱ የተፈጠረውን ውጥረት ተከትሎ የታሰሩ ባለሥልጣናትን እንዲፈታ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አባል ሀገራት መሪዎች ጥሪ አቅርበዋል።
የኢጋድ አባል ሀገራት ይኼንኑ የደቡብ ሱዳን ግጭት አስመልክተው ረቡዕ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም በበይነ መረብ ባደረጉት ስብሰባ የደቡብ ሱዳን መሪዎች ውጥረቱን ለማርገብ ውይይት እንዲጀምሩም ጠይቀዋል።
በደቡብ ሱዳን የጁባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር የኾኑት ፕሮፌሰር መልሃ ራውት ውጥረቱ የባለሥልጣናቱ መፈታት ውጥረቱን ለመርገብ መወሰድ ካለባቸው ቁልፍ ርምጃዎች አንዱ መኾኑን ገልጸዋል።
በአገሪቱ የቀጠለው የፀጥታ ችግር ዋነኛ ምክንያት ግን እ.አ.አ. በ2018 የተፈረመው የሰላም ስምምነት አተገባበር መጓተት መኾኑን ጠቅሰዋል።


</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/south-sudan-call-for-de-escalation/8011031.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/south-sudan-call-for-de-escalation/8011031.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 22:43:34 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/334741c0-bd9e-4b26-099c-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአፍሪካ የኅይል አቅርቦት ላይ ያተኮረውና በዋሽንግተን ዲሲ የተካሔደው ጉባኤ</title>
            <description>የአሜሪካ መንግሥት ባለሥልጣናት፣ የአፍሪካ ምኒስትሮች፣ ኢንቨስተሮች፣ የግል ገንዘብ አበዳሪዎች፣ እንዲሁም የአገልግሎትና የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች ዓመታዊ ለሆነውና በአፍሪካ የኅይል አቅርቦት ላይ በሚያተኩረው ጉባኤ ላይ ባለፈው ሳምንት በዋሽንግተን ዲሲ ተገናኝተው ነበር።
“መፃኢው የአሜሪካ እና የአፍሪካ የኅይል ትብብር” በተሰኘ መሪ ቃል በተካሄደው ጉባኤ፣ በአዲሱ የትረምፕ አስተዳደር የአሜሪካ መንግሥትም ሆነ የግል ኩባንያዎች የአፍሪካን የኤሌክትሪክ ኅይል ልማት፣ መሠረተ ልማት እንዲሁም የማዕድን ሃብትን በተመለከተ ያላቸውን ተሳትፎ እንደገና ለማዋቀር፣ የአሜሪካ ባለሥልጣናትና የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች ተወካዮች መክረዋል። 
የቪኦኤው አንተኒ ላብሩቶ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/labruto-us-africa-energy/8011019.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/labruto-us-africa-energy/8011019.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 22:40:33 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/f6e4fa2b-1590-4be5-09b6-08dd5c8b1668_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቆዳ ላይ ቀላል እብጠት መሰል ነገሮች እና የቆዳ ቀለምን የሚለውጡ ምልክቶች ለጤና ያሳስቡ ይኾን?</title>
            <description>በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የቆዳ ቀለምን የሚለውጡ ፣በእንግሊዝኛው አጠራር ‘ሞሎች’ በአንዳንድ ባህሎች ዘንድ እንደ ውበት ምልክት ይታያሉ። በተለይ የጥቁር ዝርያ ባላቸው ሕዝቦች ውስጥ፣ በስፋት የሚታዩና የተለመዱ ናቸው።
በአንጻሩ፣ ለጤና መታወክ ይዳርጉ ይኾን? በሚል ለጭንቀት የሚጋለጡ ወገኖች የሚሰሟቸውን ስጋቶች የሚያነሣው ጁማ ማጃንጋ፣ ለእነዚኽ እና ተያያዥ ጥያቄዎች ምላሽ ፍለጋ፣ ከናይሮቢ ኬንያ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/kenya-moles-and-skin-tags-tv-headline-skin-tags-and-moles-/8010760.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/kenya-moles-and-skin-tags-tv-headline-skin-tags-and-moles-/8010760.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 18:12:12 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/6b63bcf5-b100-4ef6-0fa4-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሶማሊያ ሆቴል ከበው ያጠቁት እና ሌሎች 50 የአልሸባብ ታጣቂዎች ተገደሉ</title>
            <description>በሶማሊያ የጸጥታ ኅይሎች በማዕከላዊ ቤለድዌን ከተማ የሚገኘውን ሆቴል ከበው ያጠቁትን ስድስቱን ታጣቂዎች መግደላቸውንና በኋላም ቢያንስ 50 የአልሸባብ ታጣቂዎች የአየር ጥቃት መገደላቸውን አስታወቁ፡፡
የቤለድዌን ወረዳ ኮሚሽነር ኦማር ኦስማን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በሆቴሉ ላይ የተፈጸመው የከበባ ጥቃት ዛሬ ረቡዕ ጧት ማብቃቱን አረጋግጠዋል።
ኮሚሽነሩ “የጸጥታ ኃይሎቻችን የሀገር ሽማግሌዎችና የጸጥታ ሃላፊዎች እየተገናኙ በሚመክሩበት ሆቴል ላይ ጥቃት ያደረሱ ስድስት ታጣቂዎችን በተሳካ ሁኔታ አስወግደዋል&quot; ብለዋል።
በዩናይትድ ስቴትስ በአሸባሪነት የተፈረጀው አልሸባብ ትላንት ማክሰኞ ለደረሰው የሆቴል ጥቃት ኃላፊነቱን ወስዷል።
በአፍሪካ ኅብረት ወታደሮች የሚደገፉት የመንግሥት ወታደሮች ሆቴሉ ውስጥ በታጣቂዎቹ የተከበቡትን የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወታደራዊ መኮንኖችን እና ሰላማዊ ዜጎችን ለመታደግ ሌት ተቀን ጥረት ማድረጋቸውን ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
ኮሚሽነሩ አክለውም “በ18 ሰዓታት ከበባ ጊዜ ጀግኖች ወታደሮቻችን ሁለት ታጣቂዎችን ገድለዋል፤ ማምለጥ እንደማይችሉ የተረዱት አራቱ ተስፋ ቆርጠው በራሳቸው ላይ ቦምብ አፈንድተው ሞተዋል። የመንግሥት የጸጥታ ኃላፊዎችን እና ሁለት ታዋቂ የሀገር ሽማግሌዎችን ጨምሮ ሌሎች ሰባት ሰዎች ተገድለዋል”ብለዋል፡፡
እኤአ ከነሐሴ 2022 ጀምሮ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼኽ መሐሙድ አልሸባብ ላይ “አጠቃላይ ጦርነት” እንዲካሄድ ጥሪ ካቀረቡ በኋላ፣ በሂርሸበሌ ግዛት፣ ኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ፣ ከሞቃዲሾ በስተሰሜን 300 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ቤለድዌን ከተማ፣ የአካባቢው ማህበረሰብ አልሸባብ ላይ ለሚያካሂደው ቅስቀሳ ማዕከል ሆና ቆይታለች።
ከተማዋ ከሞቃዲሾ በስተቀር ከሌሎቹ የሶማሊያ ከተሞች የበለጠ የሽብር ጥቃት ደርሶባታል። እኤአ ከ2009 ጀምሮ በሆቴሎች፣ ምግብ ቤቶች እና የመንግሥት ካምፖች ላይ በተፈጸሙ የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃቶች በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተገድለዋል። እ.ኤ.አ. በ2009 በተፈጸመው ትልቁ ጥቃት ቢያንስ 25 ሰዎች ሲሞቱ 60 ሰዎች ቆስለዋል።
የሆቴል ከበባው ማብቃቱን ተከትሎ የሶማሊያ የጸጥታ ኅይሎች በተለያዩ የሂርሼበሌ አካባቢዎች በርካታ የአልሻባብ ታጣቂዎች መግደላቸውን የመንግሥቱ የብሔራዊ ደኅንነት እና ጸጥታ ተቋም አመልክቷል፡፡
ተቋሙ ባወጣው መግለጫ &quot;የሶማሊያ የጦር ሠራዊት ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋራ በመተባበር በመካከለኛው ሸበሌ ክፍለ ግዛት ቢያንስ 50 የአልሻባብ ታጣቂዎችን ገድሏል፡፡ ከተገደሉት መካከልም የውጊያ ተሽከርካሪዎች አስተባባሪ የሆነ ከፍተኛ የአልሻባብ መሪ ይገኝበታል&quot; ብሏል፡፡
መግለጫው አክሎም ዳማሻ እና ሻቢሎው የተባሉ አካባቢዎች ላይ ያነጣጠረው የአየር ጥቃት ለሽብር ጥቃት የሚሰማሩ ተሽከርካሪዎች አዘጋጅ የሆነውን ማንሱር ቲማ ዊይን የተባለ ከፍተኛ የቡድኑ መሪ ገድሎታል ሲል አስታውቋል፡፡ የሶማሊያ ወታደራዊ ዕዝ በበኩሉ ባወጣው መግለጫ ደግሞ&quot; በቀጠናው የሚካሄደው ጸረ ሽብርተኛ ጥረት አካል የሆነው ርምጃ የአልሻባብን የውጊያ አቅም በእጅጉ አዳክሞታል&quot; ብሏል፡፡
የሶማሊያው የብሔራዊ ደኅንነት ተቋም አክሎም &quot;ከአልሻባብ ጋራ የተሳሰሩ 12 ብዙኀን መገናኛ አውታሮችን እና ድረ ገጾችን ዘግተናል&quot; ሲል አስታውቋል፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/somalia-al-shabab-attack/8008367.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/somalia-al-shabab-attack/8008367.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 20:58:14 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/1497785a-dcdc-4c61-a007-4467888536cd_cx0_cy6_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የደቡብ ሱዳን መሪዎች በአስቸኳይ ውይይት እንዲጀምሩ ጥሪ ቀረበ</title>
            <description>በደቡብ ሱዳን ግጭት እየተሳተፉ የሚገኙ ሁሉም ወገኖች ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ግጭት እንዲያቆሙና የአገሪቱ መሪዎችም በአስቸኳይ ውይይት እንዲጀምሩ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ጥሪ አቀረበ።
የአባል ሀገራት መሪዎች ይኼንኑ የደቡብ ሱዳን ግጭት አስመልክተው ዛሬ በበይነ መረብ ባደረጉት ስብሰባ መክፈቻ ላይ የተናገሩት የኢጋድ ዋና ጸሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ውይይቱ ከኢጋድ አባል አገራት መሪዎች መካከል በአንዳቸው ሊመቻች እንደሚችል ጠቅሰዋል።
የደቡብ ሱዳን መንግሥት የታሰሩ ባለሥልጣናትን በፍጥነት እንዲፈታም ጥሪ አቅርበዋል ።
ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝደንት ሪክ ማቻር ጋራ ጥብቅ ግንኙነት ያለው የታጠቀ ቡድን፤ በደቡብ ሱዳን አፐር ናይል ግዛት፣ ናስር አካባቢ በሚገኝ የጦር ሠፈር ላይ ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ፣ በርካታ የምክትል ፕሬዝደንቱ አጋሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወሳል።
በደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት እና  በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንቱ ሪክ ማቻር መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት፤ ተከትሎ ዩጋንዳ ልዩ ኃይሏን በዋና ከተማዋ ጁባ ማሰማራቷን የአገሪቱ ጦር አዛዥ ትላንት ማክሰኞ መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓ/ም አስታውቀዋል ።
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ፣ ቅዳሜ የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ/ም ይኼንኑ የደቡብ ሱዳን የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ባወጣው የጉዞ ማስጠንቀቂያ፣ የአስቸኳይ ጊዜ ሠራተኞች ያልኾኑ የመንግሥት ሠራተኞች በሙሉ ከደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ እንዲወጡ አዟል።
የኢጋድ አባል አገራት መሪዎች በዛሬው ስብሰባ ማጠቃለያ፣ በደቡብ ሱዳን የቀጠለውን ውጥረት በተመለከተ የጋራ መግለጫ እንደሚያወጡ ይጠበቃል ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/igad-south-sudan-summit/8008032.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/igad-south-sudan-summit/8008032.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 17:28:42 +0300</pubDate>
            <category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0e6565b8-ed50-4726-066c-08dd5c8b1668_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዩጋንዳ በደቡብ ሱዳን ልዩ ኃይሏን አሰማራች</title>
            <description>በደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር እና በተቀዳሚ ምክትላቸው ሪክ ማቻር መካከል የተፈጠረው አለመግባባት፤ ሀገሪቱን ወደ እርስ በርስ ጦርነት ሊመልሳት ይችላል የሚለው ስጋት እያየለ መሄዱን ተከትሎ፣ ዩጋንዳ ልዩ ኃይሏን በዋና ከተማዋ ጁባ ማሰማራቷን የኡጋንዳ ጦር አዛዥ ትላንት ማክሰኞ አስታወቁ።
ነዳጅ አምራች በኾነችው ደቡቡ ሱዳን የኪር መንግሥት ሁለት ሚኒስትሮችን እና በርካታ ከፍተኛ ወታደራዊ ባለሥልጣናትን ማሰሩን ተከትሎ ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል።
በጁባ የተካሄደው እስር እና በሰሜናዊው ናሲር ከተማ የተቀሰቀሰው ግጭት፣ በኪር እና በማቻር ታማኝ ኃይሎች መካከል የተካሄደውን እና ወደ 400 ሺህ ለሚጠጉ ሰዎች ህልፈት ምክንያት የሆነውን የእርስ በርስ ጦርነት ለማስቆም እ.አ.አ በ2018 የተፈረመውን የሰላም ስምምነት አደጋ ላይ እንደሚጥል ተገልጿል።
የኡጋንዳ የጦር አዛዥ ሙሆዚ ካይኔሩጋባ በኤክስ የማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት &quot;ልዩ ኃይላችን ከሁለት ቀናት በፊት ፀጥታዋን ለማስጠበቅ ጁባ ገብቷል&quot; ብለዋል። በዚሁ መልዕክታቸው አክለውም &quot;የዩጋንዳ ጦር የሚያውቀው አንድ የደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ብቻ ነው ። እሳቸውም ሳልቫ ኪር ናቸው። እሳቸውን በመቃወም የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ በዩጋንዳ ላይ ጦርነት እንደማወጅ ይቆጠራል&quot; ብለዋል።
ሮይተርስ በጉዳዩ ላይ ለማነጋገር የደቡብ ሱዳን ማስታወቂያ ሚኒስትር ቃል አቀባይ እና የጦሩ ቃል አቀባይ የእጅ ስልክ ላይ በመደወል ያደረገ ሙከራ አልተሳካም ።
እ.አ.አ በ2013 በደቡብ ሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ ዩጋንዳ ከማቻር ጋራ የሚዋጋውን የኪር ኃይል ለማጠናከር ወታደሮቿን በጁባ አሰማርታ የነበር ሲኾን፣ እ.አ.አ በ2015 ለቀው ወጥተዋል።
እ.አ.አ በ2016ም በሁለቱ ወገኖች መካከል ጦርነት በመቀስቀሱ የዩጋንዳ ጦር በድጋሚ ለአጭር ጊዜ ተሰማርቶ ነበር።
ኡጋንዳ በሰሜን በኩል በምትዋሰናት ጎርቤቷ በድጋሚ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ከፍተኛ የስደተኞች ማዕበል ሊነሳ እና በሀገሯ አለመረጋጋት ሊፈጥር ይችላል ስትል ትሰጋለች።
ካይኔሩጋባ፣ ዩጋንዳ ጦሯን በጁባ ያሰፈረችው በኪር መንግሥት ተጠይቆ ይሁን ወይም ወታደሮቹ ለምን ያህል ጊዜ በደቡብ ሱዳን እንደሚቆዩ አልተናገሩም።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8007654.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8007654.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 11:40:34 +0300</pubDate>
            <category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/ef05245f-3f0a-42f9-8fb4-08dd5b02d8d7_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በማዕከላዊ ሶማሊያ ታጣቂዎች በለድዌን ከተማ የሚገኝ ሆቴል አጠቁ</title>
            <description>ማዕከላዊ ሶማሊያ በለድዌን ከተማ ውስጥ ታጣቂዎች ዛሬ ማክሰኞ የአገር ሽማግሌዎች እና የመንግሥት ባለሥልጣናት ስብሰባ ላይ የነበሩበትን ሆቴል  ወረዋል። ሆቴሉ አሁንም በታጣቂዎቹ እንደተወረረ መሆኑን ዕማኞች እና ሆቴሉ ውስጥ ያሉት ሰዎች ቤተሰቦች ተናግረዋል።
የበለድዌን ከተማ የፌዴራል መንግሥት ባለሥልጣን የሆኑት ዳሂር አሚን ጄሶው &quot;እስከአሁን ባወቅነው መሠረት ቢያንስ አራት ሰዎች ተገድለዋል&quot; ማለታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል። ፅንፈኛ እስላማዊው ታጣቂ ቡድን አልሻባብ  ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ ሲኾን ከዐስር የሚበልጡ ሰዎች ገድለናል ብሏል።
አሊ ሱሊማን የተባሉ ባለመደብር &quot;መጀመሪያ ኃይለኛ ፍንዳታ ሰማን። ከዚያም ተኩስ ቀጠለ። እንደገና ሌላ ፍንዳታ ተደገመ&quot; ማለታቸውን ሮይተርስ ጠቅሷል።  ታጣቂዎቹ እና የመንግሥቱ  ኃይሎች እየተታኮሱ ያሉበት ካሂራ ሆቴል በከፊል መፈራረሱን ዕማኙ አክለው ገልጸዋል።
ሆቴሉ አቅራቢያ የሚኖሩ ሀሊማ ኑር የተባሉ ሌላ ዕማኝ በበኩላቸው ሆቴሉ በታጣቂዎች እንደተወረረ መኾኑን እና አልፎ አልፎ ተኩስ እንደሚሰማ ተናግረዋል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/gunmen-storm-hotel-in-central-somalia-siege-ongoing/8006661.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/gunmen-storm-hotel-in-central-somalia-siege-ongoing/8006661.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 17:07:09 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/36a514dd-3318-4fea-8863-1e8158b012af_cx0_cy4_cw0_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አሜሪካ የምትሰጠው የውጭ ርዳታ መቀነሱ በአፍሪካ ገዳይ የሆነውን በሽታ ለመዋጋት የሚደረገውን ትግል  እንዳዳከመው ተገለጸ</title>
            <description>ይኽ ወር በአብዛኛው የአፍሪካ አካባቢ የወባ በሽታ የሚጀምርበት ወቅት ነው። በአህጉሩ ደግሞ እንደወባ በከፍተኛ ሁኔታ ገዳይ የሆነ በሽታ የለም፣ በተለይ ደግሞ ለሕፃናት።


የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር 90 ከመቶ የሚደርሰውን የአሜሪካ አለማቀፍ የልማት ድርጅት (ዩኤስኤይድ) የውጭ ርዳታ ውሎች ለማቋረጥ መወሰኑ ታዲያ የወባ በሽታ ስርጭትን በከፍተኛ ሁኔታ ሊጨምር ከፍተኛ ጥፋት ሊያስከትል እንደሚችል የአህጉሩ የሕክምና ባለሞያዎች እያስጠነቀቁ ነው።


በሌላ በኩል፣ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዬ ዛሬ ሰኞ በኤክስ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፣ የትራምፕ አስተዳደር ላለፉት ስድስት ሳምንታት የዩኤስኤይድ አብዛኛውን ፕሮግራም የመዝጋት ሥራ ማጠናቀቁን እና ከመዘጋት የተረፈው 18 ከመቶ የርዳታ እና ልማት ፕሮግራም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ስር እንደሚጠቃለል አስታውቀዋል።


ሩቢዮ በዛሬ የኤክስ መልዕክታቸው ዩኤስ ኤይድ ይመራቸው ከነበሩት 6ሺሕ 200 ፕሮግራሞች ውስጥ 5ሺሕ 200 የሚኾኑት መሰረዛቸውን አስታውቀዋል።


&quot;ፕሮግራሞቹ ለዩናይትድ ስቴትስን ብሔራዊ ጥቅም የማያገለግል (እንደውም አንዳንዴ የሚጎዳ) በቢሊየኖች የሚቆጠር ገንዘብ አባክኗል&quot; ብለዋል። የትኞቹ ፕሮግራሞች እንደተረፉም ኾነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በምን መልኩ እንደሚያስቀጥላቸው ግን ዝርዝር መረጃ አልሰጡም።


በአሶስየትድ ፕረስ የተጠናቀረውን ዘገባ ስመኝሽ የቆየ ወደ አማርኛ መልሳዋለች።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/african-affairs-uganda-malaria-usaid/8005670.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/african-affairs-uganda-malaria-usaid/8005670.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 21:49:19 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/85f2fd33-b60b-4b96-0ab8-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዩናይትድ ስቴትስ የመንግሥት ሠራተኞች ከደቡብ ሱዳን እንዲወጡ አዘዘች</title>
            <description>ዩናይትድ ስቴትስ ደቡብ ሱዳን ውስጥ እየታየ ያለው ውጥረት እየበረታ በመምጣቱ፣ ከአስቸኳይ ጊዜ ሠራተኞች ውጪ ያሉ የመንግሥት ሠራተኞች ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ አዘዘች።  


የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ፣ ዛሬ በአወጣው የአስቸኳይ ጊዜ የጉዞ ማስጠንቀቂያ፣ በደቡብ ሱዳን ጦርነቱ መቀጠሉንና፣ ሕዝብ በቀላሉ ሊያገኛቸው የሚችላቸው የጦር መሳሪያዎች መኖራቸውን በማመላከት፣ የአስቸኳይ ጊዜ ሠራተኞች ያልኾኑ የመንግሥት ሠራተኞች በሙሉ ከደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ እንዲወጡ አዟል።


ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝደንት ሪክ ማቻር ጋራ ጥብቅ ግንኙነት ያለው የታጠቀ ቡድን ማክሰኞ ዕለት በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል የሚገኝ የጦር ሰፈር ላይ ወረራ ማካሄዱን ተከትሎ፣ ለማቻር ታማኝ የነበሩት የጦሩ ምክትል አዛዥ ጀነራል ጋብሪኤል ዱፕ ላም እና ሁለት ሚኒስትሮች ለእስር ተዳርገዋል።


ማቻር፤ ባለፈው ወር በርካታ አጋሮቻቸው ከመንግስት ሹመት መባረራቸው እ.አ.አ በ2018 በእሳቸው እና በፖለቲካ ተቀናቃኛቸው ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት አደጋ ላይ ይጥላል ብለው ነበር። በሁለቱ ተቀናቃኞች መካከል ለአምስት ዓመት ዘልቆ በነበረው የእርስ በእርስ ጦርነት ከ400 ሺሕ በላይ ሰዎች ተገድለዋል።


ለማቻር ታማኝ የነበሩት የጦሩ ምክትል አዛዥ ጀነራል ጋብሪኤል ዱፕ ላም በሰሜን በተከሰተው ግጭት ጋር በተያያዘ ማክሰኞ እለት በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን በተመሳሳይ የማቻር አጋር እና የፔትሮሊየም ሚኒስትር የሆኑት ፑት ካንግ ቾል ከጠባቂዎቻቸው እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር ረቡዕ ዕለት በቁጥጥር ስር ውለዋል። ለእስር የተዳረጉበት ምክንያት ግን እስካሁን አልተገለጸም።


የምዕራብ ሀገራት ልዑካን መሪዎቹ ውጥረቱን እንዲያረግቡ ባለፈው ሳምንት አሳስበው ነበር።


ደቡብ ሱዳን እ.አ.አ በ2018 የተደረሰውን ስምምነት እስካሁን ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ያላደረገች ሲሆን ባለፈው ዓመት ሊካሄድ የነበረው ምርጫም በገንዘብ እጦት ምክንያት ለሁለት ዓመት ተራዝሟል።


አርብ ዕለት ሲቪሎችን በማስወጣት ተልዕኮ ላይ ተሰማርቶ የነበረ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሄሊኮፕተር፣ ላይ የተፈፀመ ጥቃት የጸጥታ ሁኔታውን የበለጠ ያወሳሰበው ሲኾን፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች የደቡብ ሱዳን ቢሮ ፣ ድርጊቱ እንደ ጦር ወንጀል የሚቆጠር መኾኑን ተናግረዋል። በደቡብ ሱዳን ሰሜኑ ክፍል እና በመዲናይቱ ጁባ ያለው ውጥረት በሀገሪቱ የተደረገውን የሰላም ስምምነት ሊያደናቅፈው ይችላል ሲል ስጋቱን ገልጿል። 


ደቡብ ሱዳን ውስጥ ለዓመታት የዘለቀውን የሰላም ስምምነት ሊያደናቅፉ የሚችሉ ኹኔታቸው እየተከሰቱ መኾኑን የሚያሳዩ ምልክቶችን እያዩ መኾኑን  ፣ የገለጹት ኮሚሽኑ ሊቀመንበር ያስሚን ሱካ፣ &quot;መሪዎቹ መለያየትን እና ግጭትን ከማባባስ ይልቅ በሰላም ሂደቱ ላይ በአስቸኳይ አተኩረው፣ የደቡብ ሱዳን ዜጎችን ሰብአዊ መብት ማስከበር እና ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርዐት መሸጋገርን ማረጋገጥ አለባቸው&quot; ብለዋል። 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8004349.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8004349.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 09 Mar 2025 20:32:08 +0300</pubDate>
            <category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/ef05245f-3f0a-42f9-8fb4-08dd5b02d8d7_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በየመንና ጅቡቲ ጀልባዎች ሰጥመው ፍልሰተኞች መሞታቸውንና በርካቶች የደረሱበት አለመታወቁን ተመድ አስታወቀ </title>
            <description>የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፍልሰተኞች ኤጀንሲ እንደገለፀው በየመንና ጅቡቲ የባህር ዳርቻ አራት የፍልሰተኞች ጀልባዎች ሰጥመው ሁለት ሰዎች ሲሞቱ 186 የሚሆኑት ደግሞ የደረሱበት አልታወቀም።


የዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) ቃል አቀባይ ታሚም ኤሊየን እንዳሉት ሁለት ጀልባዎች በየመን ባህር ላይ የሰጠሙት ሀሙስ ምሽት ሲሆን የጠፉት 181 ፍልሰተኞችና አምስት የየመን የጀልባው ሰራተኞች መሆናቸውን ለአሶሼትድ ፕሬስ ተናግረዋል። ሁለት የጀልባው ሰራተኞችን ማትረፍ ተችሏል ብለዋል፡፡


ሌሎች ሁለት ጀልባዎች ደግሞ በትንሿ አፍሪካዊቷ ሀገር ጅቡቲ በተመሳሳይ ሰዓት ላይ ሰጥመዋል ሲሉ ተናግረዋል። የሁለት ፍልሰተኞች አስከሬን የተገኘ ሲሆን በጀልባው ውስጥ የነበሩ ሌሎች ሰዎችንም ማትረፍ መቻሉን ገልጸዋል፡፡


በደቡብ ምእራብ የመን ታይዝ ግዛት በዱባብ ወረዳ የተገለበጠችው ሶስተኛዋ ጀልባ 31 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችና ሶስት የመናውያን ሰራተኞችን አሳፍራ እንደነበረ ተናግረዋል፡፡


አራተኛዋ ጀልባ የሰጠመችው ደግሞ በዚሁ አካባቢ አቅራቢያ ወደሚገኘው የአቢያን ግዛት አህዋር ወረዳ ሲሆን 150 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችንና አራት ሰራተኞችን አሳፋራ የነበረች ናት፡፡


ባለፉት አስርት አመታት ከአፍሪካ ቀንድ ወደ የመን በሚወስደው በዚህ የፍልሰተኞች የባህር ጉዞ ሰጥመው መሞታቸው የተረጋገጡ 693 ሰዎችን ጨምሮ ቢያንስ 2ሽህ 82 ፍልሰተኞች ደብዛቸው ጠፍቷል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un-says-186-missing-and-at-least-2-dead-after-migrant-boats-capsize-off-yemen-and-djibouti-/8003609.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un-says-186-missing-and-at-least-2-dead-after-migrant-boats-capsize-off-yemen-and-djibouti-/8003609.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 08 Mar 2025 18:01:12 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/47136772-2e26-4d42-85e6-9a1f132ed136_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በብዙ አገሮች የሽብር ጥቃቶች እየበረከቱ በመጡበት አፍሪካ አስከፊ ጥቃቶችን ማስተናገዷ ተዘገበ</title>
            <description>ባለፈው ዓመት በዓለም እጅግ አውዳሚ መሆኑ የተነገረለት የአሸባሪዎች ጥቃት በአፍሪካ ሲፈፀም፤ የዓለም የምጣኔ ሃብት እና የሰላም ተቋም ይፋ ያደረገው የ2025 የዓለም አቀፍ የሽብር ጥቃቶች ጠቋሚ ሪፖርት እንዳመለከተው፤ በአጠቃላይ ከሽብር ጋር ከተዛመዱ ግድያዎች ከገሚስ በላይ የሚሆኑት የተፈጸሙት የዓለም አቀፍ የሽብር ጥቃቶች መናሃሪያ ሆኖ በቆየው የሳሕል ክልል ነው።


በሁለት ሀገራት የደረሱትን 3 አደገኛ የሽብር ጥቃቶች ጨምሮ በዓለም ዙሪያ ከተዘገቡት 20 ያህል እጅግ የከፉ ጥቃቶች ውስጥም 17ቱ የተፈጸሙት በአፍሪካ ነው። ባለፈው ዓመት በሰኔ፣ በሀምሌ እና በነሀሴ ወር በኒጀር እና ቡርኪና ፋሶ የተፈጸሙት ጥቃቶች ለ607 ሰዎች ህይወት መጥፋት ምክኒያት መሆናቸውን አክሎ ዋና መሥሪያ ቤቱን በአውስትራሊያ ያደረገው ይሄው የጥናት ቡድን አረጋግጧል።


በዚሁ ዓመት በሳህል ክልል ከግጭቶች ጋር ተያይዘው የደረሱ ሞቶች ቁጥር ከ25,000 በላይ ሰዎች የጠፋባቸው ድንገቶች ዓመታዊው ጥናታዊ ሪፖርት ይፋ መደረግ ከጀመረ ወዲህ ከተዘገቡት ሁሉ እጅግ ግዙፍ መሆኑ እና ከእነዚህም ውስጥ 3,885 ያህሉ በአሸባሪዎች የተፈጸሙ መሆናቸው ተመልክቷል። በመሰል የአሸባሪዎች ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ሃገራት ቀዳሚዋ ቡርኪና ፋሶ ስትሆን፤ ብርቱ ጉዳት ከደረሰባቸው ጥቂት የአፍሪካ ሀገሮች ማሊ፣ ኒጀር፣ ናይጄሪያ፣ ሶማሊያ እና ካሜሩን እንደሚገኙባቸው ታውቋል።


ቡርኪና ፋሶ በዘገባዎች እንደተገለጸው ክፉኛ የተጎዳች ሀገር ብትሆንም፤ አጠቃላይ የጥቃት እና የሟቾች መጠን የሚያመለክቱ አሃዞች በጠቅላላው በ21 በመቶ እና በ57 ቀንሰዋል። ያም ሆኖ ቡርኪና አሁንም በአለም አቀፍ ደረጃ በአሸባሪዎች በሚደርሱ ጥቃቶች የከፋ አደጋ ከሚደርስባቸው አምስተኛዋ አገር ነች።


በዓመቱ ውስጥ ቢያንስ አንድ የሽብር ጥቃት የደረሰባቸው ሀገራት ቁጥር ከ58 ወደ 66 ከፍ ማለቱንም ሪፖርት አክሎ አስፍሯል። ከዚህም ውስጥ ከእስላማዊው ጽንፈኛ ቡድን አይሲስ ጋር ቁርኝት ያላቸው ቡድኖች በዓለም ዙሪያ በ22 የተለያዩ አገሮች ውስጥ ባደረሷቸው የሽብር ጥቃቶች 1, 805 ሰዎች ተገድለዋል። በሌላ በኩል እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ2024 በሽብርተኞች የተፈጸሙ ጥቃቶች ቁጥር ወደ 7,555 ዝቅ ማለቱ ሲዘገብ፣ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ13 በመቶ ያነሰ መሆኑ ታውቋል።


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/africa-global-terrorism/8002890.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/africa-global-terrorism/8002890.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 Mar 2025 22:55:00 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሃሩን ማሩፍ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/efe6cbcf-315a-498b-024b-08dd5c8b1668_cx42_cy14_cw36_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሩቶና ኦዲንጋ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ</title>
            <description>የኬንያው ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ ከቀድሞው ዋና ተፎካካሪያቸው ከራይላ ኦዲንጋ ጋራ በፖለቲካ ጉዳዮች ትብብር ለማድረግ ስምምነት ተፈራርመዋል።


ሁለቱ ወገኖች እየጨመረ ያለውን የሃገሪቱን ዕዳ እና ሙስናን ጨምሮ ሌሎቹንም ሃገሪቱን የገጠሟትን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ አብረው ለመሥራት ተስማምተዋል።


ሩቶ የግብር ጭማሪ እንደሚያደርጉ ማስታወቃቸውን ተከትሎ በሃገሪቱ በተነሳው ተቃውሞ ቢያንስ 60 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። የነበራቸው የሕዝብ ድጋፍም እያሽቆለቆለ መጥቷል።


ተቃውሞው በመበርታቱም ሩቶ ከተቃዋሚያቸው ከኦዲንጋና ከበርካታ የፓርቲ አባሎቻቸው ጋራ”ሰፊ መሠረት ያለው” መንግሥት ለመመስረት እንዲሠሩ አስገድዷቸዋል። ይህንን ስምምነትም ዛሬ በይፋ በመፈረም ሃገሪቱ የገጠማትን ችግሮች ለመቅረፍ በጋራ እንደሚሠሩ አስታውቀዋል።


ጉምቱ የተቃዋሚ ፖለቲከኛው ራይላ ኦዲንጋ በኬንያ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ አምስት ጊዜ ተሳትፈው ሳይቀናቸው ቀርቷል።


ስምምነቱ በሃገር ውስጥ ያለውን ውጥረት ለማርገብ ያለመ እንደሆነ የ80 ዓመቱ ኦዲንጋ አስታውቀዋል። ሩቶ በበኩላቸው ስምምነቱ “ነፃነትና መልካም አጋጣሚዎች ለሁሉም መድረሳቸውን ማረጋገጫና ወደ ተስፋይቱ ምድር የሚወስድ መንገድም ነው” ብለዋል።


የፖለቲካ ተንታኞች ስምምነቱን &quot;እየተንኮታኮተ ያለው አገዛዝ እንዲያንሰራራ የተደረገ ሙከራ&quot; ሲሉ ገልጸውታል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/kenya-ruto-odinga/8002781.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/kenya-ruto-odinga/8002781.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 Mar 2025 22:07:56 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/953a171d-a1a9-41fc-2e58-08dd5c897904_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፍልሰተኞችን የያዙ አራት ጀልባዎች ሰመጡ</title>
            <description> ካይሮ — ፍልሰተኞችን የያዙ አራት ጀልባዎች በየመንና ጂቡቲ ባህር ዳርቻ ሰምጠው ቢያንስ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ 186 የሚሆኑት የደረሱበት እንደማይታወቅ የዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) አስታውቋል።


አደጋው የደረሰው ትላንት ሐሙስ ምሽት ሲኾን፣ በባህረ ሰላጤው ሀገራት ሥራ ለማግኘትና ከግጭት ለመሸሽ ኢትዮጵያን በሚጠቀሙበት የጉዞ መሥመር ላይ እንደኾነም የአጃንስ ፍራንስ ፕረስ ዘገባ አመልክቷል።


በየመን ዳርቻ ከሰመጡት ጀልባዎች በአንደኛው ላይ 150 ኢትዮጵያውያንና አራት የጀልባው ሠራተኞች ተሳፍረው የነበረ ሲሆን፣ በሌላኛው ጀልባ ላይ ደግሞ 31 ኢትዮጵያውያንና ሦስት የመናውያን የጀልባው ሠራተኞች ተሳፍረው እንደነበር ታውቋል።


አሶስዬትድ ፕረስ በበኩሉ በየመን ዳርቻ የሰመጡት ሁለት ጀልባዎች ሠራተኞች ከአደጋው ሲድኑ፣ 181 ፍልሰተኞችና አራት የመናዊ የጀልባዎቹ ሠራተኞች የደረሱበት እንዳልታወቀ ዘግቧል።


በጅቡቲ ባህር ዳርቻ ሁለት ጀልባዎች በተመሳሳይ ሰዓት መስመጣቸውንና፣ የሁለት ፍልሰተኞች አስከሬን ሲገኝ የተቀሩትን መታደጋቸውን የአይ ኦ ኤም ቃል አቀባይ ታሚም ኢሌይን አስታውቀዋል።


በጅቡቲ ባህር ዳርቻ የደረሰው አደጋ ምክንያት ከፍተኛ ኃይል ያለው ነፋስ በመከሰቱ እንደኾነም ተጠቁሟል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/yemen-migrants/8002549.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/yemen-migrants/8002549.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 Mar 2025 19:43:21 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP, ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a8ecce85-8152-47be-2e13-08dd5c897904_cx0_cy7_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሶማሊያ ፑንትላንድ እስላማዊ መንግሥት እያፈገፈገ ነው </title>
            <description>ዋሽንግተን  — ሶማሊያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የእስላማዊ መንግሥት ቡድን ታጣቂዎች፣ ከፑንትላንድ ጦር ጋር ለሁለት ወራት ካደረጉት ተከታታይ ውጊያ በኋላ፣ እንዲያፈገፍጉ ማድረጉን የክልሉ ባለሥልጣናት ተናግረዋል።


ባለፈው ሳምንት የፑንትላንድ ጦር  በቡክ ካሌድ የቡድኑን አሚር አብዱልቃድር ሙሚን ዋና መሥሪያ ቤት በቁጥጥር ስር አውሏል።


የአካባቢው ባለሥልጣናት በኩራ መንደር አቅራቢያ በተካሄደ ውጊያ 15 ወታደሮች መሞታቸውን ገልጸው፣ አይ ኤስ የሞቱበትን 57 ተዋጊዎች ጥሎ መሸሹን አስታውቀዋል፡፡


ከሳምንት በኋላ አይ ኤስ ወይም አይሲስ ተብሎ የሚጠራው የሽብር ቡድን ተጨማሪ አጥፍቶ ጠፊዎችን እና አዲስ ተዋጊዎችን ይዞ በሸለቆው አካባቢ መልሶ ማጥቃት ጀምሮ እንደነበር ባለሥልጣናቱ ገልጸዋል፡፡


የፑንትላንድ ጦር የሽብር ቡድኑን ሦስት የጦር ሰፈሮችን ከመቆጣጠሩ በፊት፣ በውጊያው ወደ 100 የሚጠጉ ሰዎች የሞቱ ሲሆን 28 ወታደሮችን እና ከ70 በላይ ታጣቂዎችን መገደላቸው ተዘግቧል።


እንደ ባለሥልጣናቱ ገለጻ የፑንትላንድ ወታደሮች ከቱርማሳሌ እስከ ዳሳን ያለውን 40 ኪሎ ሜትር ስልታዊ ኮሪደር በማጽዳት ዋሻዎችን እና ትናንሽ መንደሮችን ተቆጣጥረዋል።


የፑንትላንድ ኃይሎች ዋሻዎችንና ትናንሽ መንደሮችን አከታትለው ሲቆጣጠሩ የአይኤስ ተዋጊዎችን ስትራቴጂያዊ ይዞታቸው ከኾኑት የቶጎ ውጫሌ ሸለቆ፣ ከቱርማሳሌ እና ከደሃሳን በ40 ኪሎ ሜትሮች በላይ እንዲያፈገፍጉ ማድረጋቸውን  ባለሥልጣናቱ ገለጸዋል።


የዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚኒስቴር  ስለ አይ ኤስ ማፈግፈግ ሲጠየቅ አስተያየት ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም። ይኹን እንጂ ግን ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ አንድ የዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ባለሥልጣን በሂደት ላይ ስላለው ኦፕሬሽን  ሲናገሩ “ዋሽንግተን ተጨማሪ ርዳታ ለመስጠት መዘጋጀቷን ጠቁመዋል።


&quot;በአፍሪካ ቀንድ አሸባሪ ድርጅቶችን ለመበተን፣ ለማመናመን እና ለማሸነፍ በምናደርገው የጋራ ጥረት አጋሮቻችንን ለመደገፍ ቁርጠኛ ነን&quot; ሲሉ ባለሥልጣኑ ለቪኦኤ ተናግረዋል።


የፑንትላንድ ክልል መሪ ሳይድ አብዱላሂ ዴኒ “ አሸባሪዎች እንቅስቃሴያቸው እና መሠረቶቻቸው  በሙሉ እስኪወገዱ ድረስ” የሽብር ቡድኑን አድነን ለማጥፋት ዝግጁ ነን&quot; ሲሉ ዝተዋል።


የሶማሊያ ባለሥልጣናት ለአሜሪካ ባለሥልጣናት ሲናገሩ  የአይ ኤስ ተዋጊዎች ይዞታቸው ላይ ከመቆየት ይልቅ በሦስት ቡድኖች ተከፋፍለው በተለያዩ አቅጣጫዎች ሸሽተዋል&quot; ብለዋል። 


የሶማሊያ የጸጥታ ባለሞያዎች ግን ግፊቱ ተጠናክሮ ካልቀጠለ በስተቀር ቡድኑ እንደገና በመሰባሰብ የሽምቅ ውጊያ ሊጀምር እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/islamic-state-in-retreat-after-offensive-in-somalia-puntland/8001435.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/islamic-state-in-retreat-after-offensive-in-somalia-puntland/8001435.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 06 Mar 2025 21:41:33 +0300</pubDate>
            <category>አፍሪካ</category><category>ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/98859bb0-302a-4816-87bc-6590accaeeb6_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ግብፅ ለትረምፕ የጋዛ እቅድ ያቀረበችውን አማራጭ አቅድ የአረብ መሪዎች መደገፋቸውን አስታወቀች</title>
            <description>የአረብ መሪዎች፤ ግብጽ በ53 ቢሊየን ዶላር ወጪ ጋዛን መልሶ ለመገንባት ያቀረበችውን ዕቅድ ትላንት ማክሰኞ  አፅድቀዋል። እቅዱ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለግዛቲቱ ካቀረቡት እቅድ በተለየ ፍልስጤማውያን ከአካባቢያቸው እንዳይፈናቀሉ ለማድረግ የሚያስችል ነው።


የግብፅ እቅድ ካይሮ ውስጥ በተካሄደው የመሪዎቹ ጉባዔ የመዝጊያ ስነ ስርዓት ላይ ተቀባይነት ማግኘቱን ፕሬዝደንት አብደል-ፈታህ አል ሲሲ ገልጸዋል።


በግብፅ አስተናጋጅነት በተደረገው ስብሰባ ላይ የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ምክትል ፕሬዝዳንት፣ የካታር አሚር እና የሳዑዲ አረብያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተገኝተዋል።


ትረምፕ  ፍልስጤማውያንን ከጋዛ ውጪ አስፍሮ  ሰርጡን መልሶ ለመገንባት ባለፈው ጥር ወር ላቀረቡት እቅድ አማራጭ ሆኖ የቀረበው የግብፅ እቅድ፣ ፍርስራሹ እስኪወገድ እና የተቀበሩ ፈንጂዎች እስከሚወጡ፣ የጋዛ ነዋሪዎች እዚያው ጋዛ ውስጥ በሰባት የተለያዩ ሥፍራዎች   በጊዜያዊ መኖሪያ ቤቶች እንዲቆዩ ይጠይቃል።


በጉባኤው ላይ የግብጹ ፕሬዝደንት ሲሲ ትረምፕ ጋዛን መልሶ ለመገንባት ስላደረጉት ጥረት አመስግነው ግብፅ ያቀረበችው እቅድ ግዛቱን በጊዜያዊነት የሚመራ የአስተዳደር አካልንም ያካተተ መሆኑን አመልክተዋል።


ዩናይትድ ስቴትስ በአሸባሪነት የፈረጀችው ሐማስ እቅዱን የተቀበለው ሲሆን፣ እስራኤል ግን ነቀፌታ ሰንዝራለች። የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ የአረብ ሀገራት ጉባኤ ያፀደቀው እቅድ ሐማስ እ.አ.አ በጥቅምት 7፣ 2023 ካደረሰው ጥቃት የተከተለውን ተጨባጭ ሁኔታ ከግምት ውስጥ ያስገባ አይደለም ብሏል። 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/egypt-says-arab-leaders-endorse-counterproposal-to-trump-s-gaza-plan/7998939.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/egypt-says-arab-leaders-endorse-counterproposal-to-trump-s-gaza-plan/7998939.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 05 Mar 2025 21:13:16 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/d049eb7c-7154-4932-8f6a-08dd5b02d8d7_cx0_cy5_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የደቡብ ሱዳን ጦር የምክትል ፕሬዝደንቱን ቤት ከቧል</title>
            <description>ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝደንት ሪክ ማቻር ጋር ጥብቅ ግንኙነት ያለው የታጠቀ ቡድን፤ በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል የሚገኝ የጦር ሠፈር  መውረሩን ተከትሎ፣ የመንግሥቱ ወታደሮች ዛሬ በዋና ከተማዋ ጁባ የሚገኘውን የምክትል ፕሬዝደንቱን መኖሪያ ቤት ከበዋል፡፡ በርካታ አጋሮቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል።


ማቻር፤ ባለፈው ወር የመንግሥት ባለስልጣን የነበሩ በርካታ አጋሮቻቸው  መባረራቸው እ.አ.አ በ2018 በእሳቸው እና በፖለቲካ ተቀናቃኛቸው ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት አደጋ ላይ ይጥላል ብለው ነበር። በሁለቱ ተቀናቃኞች መካከል ለአምስት ዓመታት በተካሄደው የእርስ በእርስ ጦርነት ከ400 ሺህ በላይ ሰዎች ተገድለዋል።


ለማቻር ታማኝ የነበሩት የጦሩ ምክትል አዛዥ ጀነራል ጋብሪኤል ዱፕ ላም በሰሜኑ ግዛት ከተከሰተው ግጭት ጋር በተያያዘ ትላንት ማክሰኞ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን በተመሳሳይ የማቻር አጋሩ  የነዳጅ ዘይት ሚኒስትር  ፑት ካንግ ቾል ከጠባቂዎቻቸው እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር ዛሬ ረቡዕ  በቁጥጥር ስር ውለዋል። የታሰሩበት ምክንያት ግን እስካሁን አልተገለጸም።


የምዕራብ ሀገራት ልዑካን መሪዎቹ ውጥረቱን እንዲያረግቡ ባለፈው ሳምንት አሳስበው ነበር።


ደቡብ ሱዳን እ.አ.አ በ2018 የተደረሰውን ስምምነት እስካሁን ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ያላደረገች ሲሆን ባለፈው ዓመት ሊካሄድ የነበረው ምርጫም በገንዘብ እጦት ምክንያት ለሁለት ዓመት ተራዝሟል። 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7998843.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7998843.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 05 Mar 2025 20:10:19 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/dfc62e3d-c828-4bb7-9666-e8e36aa0584e_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኮንጎ ግጭት ምክንያት ጀርመን ለሩዋንዳ የምትሰጠውን አዲስ ርዳታ አቆመች</title>
            <description>ጀርመን ለሩዋንዳ የምትሰጠውን አዲስ የልማት ርዳታ ማቆሟን እና ቃል የገባቻቸውን ድጋፎችም እየገመገመች መኾኑን ዛሬ ማክሰኞ አስታውቃለች።


ጀርመን ይህን ርምጃ የወሰደችው፣ ሩዋንዳ በጎረቤቷ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በሚካሄደው ግጭት ውስጥ ላላት ሚና ምላሽ ለመስጠት ነው።


የጀርመን ልማት ምኒስትር ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ በርሊን ውሳኔዋን አስቀድማ ለሩዋንዳ ማሳወቋን እና በምስራቅ ኮንጎ የበላይነት እያገኘ ላለው የኤም 23 አማፂ ቡድን የምትሰጠውን ድጋፍ እንድታቆም ማሳሰቧን አመልክተዋል።


ኮንጎ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባለሞያዎች እና የምዕራብ ኃያላን ሀገሮች ሩዋንዳ አማፂውን ቡድን ትደግፋለች በማለት ይከሷታል።


ክሱን የምትቃወመው ሩዋንዳ በበኩሏ በኮንጎ የቱትሲ ተወላጆችን ለመጨፍጨፍ እና ለሩዋንዳ ስጋት ለመፍጠር ከሚንቀሳቀሱ የሁቱ ተወላጅ ታጣቂዎች እራሷን እየተከላከለች እንደሆነ ትገልጻለች።


የሩዋንዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያቤት የጀርመን ውሳኔ &quot;የተሳሳተ እና አሉታዊ ውጤት ያለው ነው&quot; ሲል ምላሽ ሰጥቷል።


መስሪያ ቤቱ ባወጣው መግለጫ &quot;በቀጠናው በተደጋጋሚ ለሚከሰቱ አለመረጋጋቶች ታሪካዊ ኃላፊነት የተሸከሙ እንደ ጀርመን ያሉ ሀገራት ለአንድ ወገን ያደላ አስገዳጅ ርምጃዎችን ከመተግበር የተሻለ ማወቅ ነበረባቸው&quot; ብሏል።


የጀርመን ምኒስቴር እንደገለፀው በርሊን፣ እ.አ.አ ከጥቅምት 2022 እስከ 2024 ላለው ጊዜ የ98 ሚሊየን ዶላር ርዳታ ለሩዋንዳ ለመስጠት ቃል ገብታ ነበር። 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/germany-stops-new-aid-to-rwanda-over-dr-congo-conflict/7998693.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/germany-stops-new-aid-to-rwanda-over-dr-congo-conflict/7998693.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 05 Mar 2025 18:06:50 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/10e8d71f-7f1d-49ee-a311-e3d0ae62ff72_cx0_cy8_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title> ኬንያ ውስጥ በስደተኞች የምግብ ዕደላ ወቅት በተቀሰቀሰ ግጭት ተረጂዎች ተጎዱ</title>
            <description>ሰሜን ኬንያ በሚገኘው ካኩማ የስደተኞች መጠለያ ካምፕ በተቃውሞ እንቅስቃሴ ወቅት ፖሊስ በወሰደው ርምጃ አራት ሰዎች መቁሰላቸው ተገለጸ።


በትላንቱ የምግብ ዕደላ ላይ የተቀሰቀሰው ግጭት ለስደተኛው ከሚሰጠው የምግብ ርዳታ እጥረት ጋራ የተያያዘ መኾኑም ተመልክቷል።


ከኬንያ አጎራባቾች ደቡብ ሱዳን፣ ኢትዮጵያ፣ ቡሩንዲ እና ኮንጎ ግጭቶችን በመሸሽ እና በድርቅ ሳቢያ የሚሰደዱ ወገኖችን በሚያስጠልለው ካምፕ ውስጥ ለሚገኙት በብዙ ሺሕዎች የሚገመቱ ስደተኞች ይሰጥ የነበረው የምግብ አቅርቦት፤ በተፈጠረው የርዳታ ገንዘብ እጥረት የተነሳ የወትሮ አሠራሩ መስተጓጎሉ ተዘግቧል።


በካምፑ ለስደተኞች የሚሰጠውን ምግብ የሚያከፋፍለው የዓለም የምግብ ፕሮግራም ባለፈው ታኅሣሥ ወር ለስደተኞች ከሚሰጠው ምግብ &quot;በገጠመው የአቅርቦት እጥረት የተነሳ ከሚያስፈልገው ከ45 በመቶ በታች እንደነበር አመልክቷል።


የዓለም የምግብ ፕሮግራም ከለጋሽ አገሮች መንግሥታት ያገኝ የነበረው መዋጮ እጥረት እንደሚገጥመው ለዓመታት ሲያሳስብ መቆየቱ ይታወቃል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/refugees-injured-in-clashes-with-kenyan-police-during-food-ration-protests/7997332.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/refugees-injured-in-clashes-with-kenyan-police-during-food-ration-protests/7997332.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 04 Mar 2025 20:05:18 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/b1549a9c-982c-4180-96f4-787e01a4e6f6_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ግዛቷ ውስጥ &quot;20 የሁቱ አማጽያን ተያዙ&quot; የተባለው የሐሰት ወሬ ነው&quot; አለች </title>
            <description>የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጦር ከሩዋንዳው የዘር ማጥፋት ወንጀል ጋራ ግንኙነት ያላቸው 20 ተዋጊዎች ግዛቱ ውስጥ ተይዘዋል መባሉን  አስተባብሏል።  አማጽያኑ ለሩዋንዳ ተላልፈው ሲሰጡ የሚያሳይ ተብሎ የወጣውን  ቪዲዮ “በሐሰት የተቀነባበረ ” ሲል ትላንት እሑድ ባወጣው መግለጫ አጣጥሏል።


መግለጫው የወጣው በምሥራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የሚንቀሳቀሰው የኤም 23 ታጣቂ ቡድን በጎርጎሮሳውያኑ 1994 በሩዋንዳ የቱትሲዎች የዘር ማጥፋት ወንጀል በተሳተፉ የሁቱ ጎሳ አባላት የተቋቋመው የሩዋንዳ ነፃ አውጪ ዲሞክራሲያዊ ኅይል (ኤፍ.ዲ.ኤል.አር) ተዋጊዎችን መያዙን ቅዳሜ ዕለት ማስታወቁን ተከትሎ ነው።


የኮንጐ ጦር ኅይሎች አዛዥ  ባወጡት መግለጫ “ይህ የእኛን ሠራዊት ስም ለማጥፋት የተቀነባበረ፤  የውሸት ድርጊት ነው” ብለዋል።


አክለውም “ሩዋንዳ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አንዳንድ ቦታዎችን መውረሯን ምክንያታዊ ለማድረግ የተጠቀመችው ስልት አካል ነው” ሲሉም አክለዋል።  “በውሸት እና በማጭበርበር ጥበብ የተካኑት የሩዋንዳ ባለስልጣናት የድሮ የሩዋንዳ ነፃ አውጪ ዲሞክራሲያዊ ሃይል (ኤፍ.ዲ.ኤል.አር) እሥረኞችን ወስደው አዲስ ወታደራዊ ልብስ በማልበስ በጎማ  ከተማ በቅርቡ  ጎማ ውስጥ የተያዙ ተዋጊዎች አስመስለው  አሳልፈዋቸዋል” ብለዋል።


በምሥራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እየተባባሰ ያለው ግጭት በሩዋንዳ፣ በዩጋንዳ እና ወደሌሎች ጎረቤት ሀገራት ተዛምቶ  ወደ ሰፊ ቀጣናዊ ጦርነት ሊሸጋገር ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።


ሩዋንዳ እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ አስተያየት አልሰጠችም።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/dr-congo-says-handover-of-20-alleged-hutu-rebels-was-staged/7995545.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/dr-congo-says-handover-of-20-alleged-hutu-rebels-was-staged/7995545.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 03 Mar 2025 21:31:56 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/29EC2571-6016-4806-AD0B-B6FBCE29D7A6_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአፍሪካ ከአየር ንብረት ጋራ የተያያዙ አደጋዎችን ለመቀነስ የሚረዳ ዝግጁነት ላይ እየተሠራ ነው</title>
            <description>የአፍሪካ ቀንድ ሀገራትን የሚያጋጥሙ ከአየር ንብረት ጋራ የተያያዙ አደጋዎች ከጊዜ ወደጊዜ እየተበራከቱ መጥተዋል፡፡ በመኾኑም የቀጣናውን ሀገራት ያሰባሰበው  ኢጋድ ሀገራቱ  ከሰብአዊ ረድዔት ተቋማት ጋራ በመኾን የአደጋ ዝግጁነት መርሐ ግብሮችን  በማሰናዳት ላይ ይገኛል፡፡ ዓላማውም በስምንቱም የቀጣናው ሀገራት የአደጋ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዐቶች በመዘርጋት  አደጋዎች ቢከሰቱ  የሚደርሱ ጉዳቶችን  ለመቀነስ እንዲቻል መኾኑን ከናይሮቢ በጁማ ማጃንጋ ያደረሰን ዘገባ አውስቷል፡፡


ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/african-affairs-africa-disaster-preparedness/7995462.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/african-affairs-africa-disaster-preparedness/7995462.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 03 Mar 2025 20:50:11 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/512db885-d0d7-470b-0707-08dd4a817621_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>