<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>የዕለቱ አብይ ዜና - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/5027</link>
        <description>የዕለቱ አብይ ዜና amharic.voanews.com</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>የዕለቱ አብይ ዜና - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/5027</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2021 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Thu, 13 May 2021 13:30:57 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zjipqmeyjpq_" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>“እውነተኛ ሰላም እንዲመጣ ከተፈለገ ፣ሰላምን ያወኩ ተጠያቂ መሆን አለባቸው “አምባሳደር ታየ አጽቀ ስላሴ</title>
            <description>የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክርቤት ለህዝብ ደህንነትና ህልውና አስፈላጊ የሆኑ ተቋማት ጥበቃ ሊደረገግላቸው በሚችልበት ጉዳይ ላይ ባደረገው ስብሰባ ላይ ንግግር ያደረጉት በመንግስታቱ ድርጅቱ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር የሆኑት ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ ታጣቂ ሀይሎች ሆን ብለው ለህዝብ መሰረታዊ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ላይ ጉዳት እንደሚያደርሱ በመግለፅ ተጠያቂ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።


የታጠቁ ሀይሎች ሆን ብለው በእርሻዎች፣ የውሀ ማስተላለፊያ ቱቦዎችና የጤና ተቋማት ላይ ቦምብ በመጣል እንደሚያጠቁና ህዝብ መሰረታዊ መገልገያውን እንዲያጣ እንደሚያደርጉ የገለፁት አምባሳደር ግሪን ፊልድ በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ያለውን ግጭት እንደማሳያ አቅርበዋል።


&quot;በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያልው ውጊያ የህዝብ መገናኛ አውታሮች እንዲቋረጡ፣ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ሽቦዎች እንዲወድቁ፣ ሆስፒታሎች እንዲዘረፉና ከጥቅም ውጪ እንዲሆኑ አድርጓል። የትግራይ ህዝቦች መሰረታዊ ፍላጎታቸውን ለማሟላት ለደህንነታችው አስጊ የሆኑ በተለይ ፆታዊ ጥቃት የሚፈፀምባቸው ረጅም ጉዞዎች እንዲጓዙ ተገደዋል&quot; ያሉት አምባሳደር ግሪንፊልድ በትግራይ ያለው ግጭት በአስቸኳይ እንዲቆምም ጠይቀዋል።


ከአምባሳደሯ ንግግር ጋር በተያያዘ የመንግስታቸውን አቋም የጠየቅናቸው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ታየ አጽቀስላሴ በበኩላቸው ፣ የኢትዮጵያ መንግስት የህዝቦች ሰላማዊ ኑሮ እንዳይታወክ በተቻለው አቅም እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው ፣ “እውነተኛ ሰላም እንዲመጣ ከተፈለገ  ሰላምን ያወኩ ተጠያቂ መሆን አለባቸው” ብለዋል።


ከአምባሳደር ታየ ጋር የተደረገውን አጭር ቆይታ ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5873858.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5873858.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 01 May 2021 01:42:21 +0300</pubDate>
            <category>ኢትዮጵያ</category><category>ጋቢና ቪኦኤ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ሀብታሙ ስዩም, ስመኝሽ የቆየ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5873858.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0F609EBA-0E72-437E-884A-858CCFD1F3DF_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የጸረ-ኮቪድ ክትባቶች የቸሩት ተስፋና የገጠሙ አንዳንድ ፈተናዎች</title>
            <description>የጤና አገልግሎት ተቆጣጣሪዎች የብሪታንያ ሰራሹን አስትራዜኔካ ጸረ ኮቪድ ክትባት በተከተቡ አንዳንድ ሰዎች ላይ የታየውን “ያልተለመደ ነው” የተባለ የደም መርጋት አስመልክቶ ሰሞኑን ይፋ ያደረጉትን መረጃ ተከትሎ አንዳንዶች በክትባቱ ላይ የነበራቸው የመተማመን ስሜት በፍጥነት እየቀነሰ መምጣቱ ተዘግቧል።


ክትባቶቹ የቸሩት ተስፋ እና ጥቅም ላይ ከዋሉት በርካታ ክትባቶች በተለይ ሁለቱን .. የእንግሊዙን አስትራዜኔካ እና የዩናይትድ ስቴትሱን ጆንሰን ኤንድ ጆንሰንን ከወሰዱ በርካታ ሚልዮን ሰዎች በጥቂት ሰዎች ላይ የታዩት እነኚህ “ያልተለመዱ” ዓይነት የደም መርጋት ችግሮች ከአንዳንዶች ዘንድ ብርቱ ስጋት ደቅነዋል። በአንጻሩ በእጅጉ የሚያስፈልገውን የክትባት ዘመቻ እንዳይሰተጓጉሉ የሚል አሳሳቢ ሁኔታም ከስተዋል።


በዩናይትድ ስቴትስ እንድ ጊዜ ብቻ የሚከተበውን የጄ ኤንድ ጄ ክትባት ከተከተበው ቁጥሩ ሰባት ሚልዮን የሚጠጋ ሰው ችግሩ የተከሰተው በስድስት ሰዎች ላይ ሲሆን፤ በአውሮፓ ተመሳሳይ ሁኔታ ከታየበት የአስትራዜኔካ ክትባት መጠኑ 25 ሚልዮን የሚደርስ ክትባት የተባለው ችግሩ የገጠማቸው በድምሩ 84 ሰዎች ነው።


የችግሮቹን ምንጭ እና ከክትባቶቹ ጋር ያላቸውን ዝምድና እንዲሁም የደቀኑትን ፈተና .. በመካሄድ ላይ ያሉትን ምርመራዎች ሂደት እና ሌሎች ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች መልከት የሚያደርገውን ቅንብር እነሆ።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/world-vaccine-astrazeneca-us-suspends-johnson-and-johnson-vaccine-4-21-2021/5861599.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/world-vaccine-astrazeneca-us-suspends-johnson-and-johnson-vaccine-4-21-2021/5861599.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 21 Apr 2021 17:44:37 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><category>ኮሮናቫይረስ/ኮቪድ-19</category><author> voadigital@voanews.com (አሉላ ከበደ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/world-vaccine-astrazeneca-us-suspends-johnson-and-johnson-vaccine-4-21-2021/5861599.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/FC4BBF29-1AF5-4D61-9C70-BB853DE9627F_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሆሮጉድሩ ወለጋ 42 ሰላማዊ ሰዎች በታጣቂዎች መገደላቸው ፖሊስ አረጋገጠ</title>
            <description>
	 ማንነትን መሰረት አድርጎ የተፈፀመ ጥቃት መሆኑን ከጥቃቱ የተረፉ ተናግረዋል


በኦሮሚያ ክልል በሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ከቅዳሜ የካቲት 27/2013 ዓ.ም ጀምሮ በተከታታይ ቀናት ማንነትን መሰረት አድርጎ በደረሰባቸው ጥቃት ሕፃናትና ሴቶችን ጨምሮ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ከጥቃቱ የተረፉ ነዋሪዎች ተናገሩ። 


ነዋሪዎቹ “ኦነግ ሸኔ የተባሉ ታጣቂዎች” የአማራ ተወላጅ የሆኑ ነዋሪዎችን እየለዩ ጥቃት ማድረሳቸውን ገልፀዋል። ሕይወታቸው ካለፉ ሰዎች በተጨማሪ ቆስለው ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ በርካቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።


ከጥቃቱ የተረፉ ነዋሪዎችም ቢሆኑ በአሁኑ ሰዓት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች አሉበት ወደተባሉበት ቀበሌዎች በእግራቸው እየሸሹ መሆኑን ገልፀው፤ “መንግሥት ሕይወታችንን ይታደግልን” ሲሉ ጠይቀዋል።


በሌላ በኩል የኦሮሚያ ክልል  ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር እና የኮምኒኬሽን እና ሚዲያ ኃላፊ ጌታቸው ኢታና ፤ ጥቃቱ መድረሱን ገልፀው እስካሁን ባላቸው መረጃ 42 ሰዎች በኦነግ ሸኔ መገደላቸውንአረጋግጧል።


ጃልመሮ በሚል ቅፅል ስም የሚታወቀው የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት የምዕራብ ኦሮሚያ አዛዥ ኩምሳ ድሪባ፤እርሱ የሚመራው ጦር ማንነትን፣ ዘርን እና ኃይማኖትን መሠረት አድርጎ ጥቃት እንደማይፈፅም ገልፆየአማራ እና የኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይሎች ናቸው ብሏል።


ከጥቃቱ የተረፉና ቤተሰቦቻቸው በጥቃቱ እንዳጡ የሚናገሩ ቤተሰቦች ግን የጦር መሳሪያ በሚገባ የታጠቁና የኦነግ ሸኔ መለያ ልብስ የለበሱ ታጣቂዎች እንዳጠቋቸው ገልፀዋል። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን በበኩሉ “ኦነግ ሸኔ ጥቃቱን ከፈፀመ በኋላ ሁሌም የሚያሳብብበት አካል ይፈጥራል” ብሏል።


(ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5810855.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5810855.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 11 Mar 2021 22:22:00 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ጽዮን ግርማ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5810855.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/234DFDD2-D2C9-4583-A9E4-C6EC31C7C439_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>“ሰዎች እያደረጉት ያለው እርብርብ ልብ የሚነካ ነው” - አርቲስት ታማኝ በየነ</title>
            <description>ግሎባል አሊያንስ ከሌሎች የሰብዓዊ መብት ማኅበራትና የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ጋር በመሆን ለትግራይናለመተከል ተጎጂዎች እርዳታ ለማሰባሰብ የሚያደርገው ርብርብ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተለመደ የመጣውንየተቸገሩ ሰዎችን ለመርዳት በማንነት እና በብሔር የመቧደን እንቅስቃሴ የመቀየር አላማ እንዳለው የድርጅቱዴሬክተር አርቲስት ታማኝ በየነ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጿል። 


በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ችግር በቀላሉ በእርዳታ ብቻ እንደማይፈታ የሚናገሩት ታማኝ በየነ፤ እርዳታ ማሰባሰቡ ቢያንስ አንደኛው አንደኛውን“አለሁልህ” የሚል ስሜት መፍጠሪያ ነው ያለ ሲሆን፣ ይህ ሐሳባቸው ተቀባይነት አግኝቶ ፤ሰዎች ከአንድ የታሸገፓስታ ጀምሮ ያላቸውን በማዋጣት ላይ መሆናቸውንም ገልጿል። 


/ቃለ ምልልሱን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያዳምጡ።/






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5777658.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5777658.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 14 Feb 2021 07:59:48 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ስመኝሽ የቆየ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5777658.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/62290ABE-8F09-4B14-8912-61FF04D62FE4_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ትግራይ ክልልን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለመመለስ እየሠራ መሆኑን መንግሥት ገለፀ</title>
            <description>መንግሥት ትግራይ ክልልን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለመመለስ እየሠራ መሆኑን አንድ ዓለም አቀፍ ተቋም ባዘጋጀዋው የጥያቄና መልስ ማብራሪያ ላይ ገለፀ።


ባለፈው ሣምንት ሐሙስ ጥር 20/2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተመራ ቡድን “አትላንቲክ ካውንስል” የተሰኘ የዩናይትድ ስቴትስ የሐሳብ አብላዮችተቋም ባዘጋጀው የበይነ መረብ ውይይት ላይ ትግራይ ክልልን በተመለከተ ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያእንደሰጠ በሚኒስቴሩና በካውንስሉ ድረ ገፅ ላይ ይፋ ተደርጓል።


ለአድን ሰዓት በቆየው በዚህ የጥያቄና መልስ ውይይት ላይ ከአዲሱ ከፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር  አባላትእና እንደራሴዎች መካከል የተገኙ እንደነበሩ  የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ያወጣው መግለጫ ያሳያል። በሌላበኩል በዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍፁም አረጋ ከአሜሪካ ድምፅ ጋር በስልክ በነበራቸው ቆይታ፤“ወደ 30 የሚሆኑ ሰዎች እንደተሳተፉ አይቻለሁ” ብለዋል።


ማብራሪያው ለምን ተዘጋጀ?


አምባሳደር ፍፁም አረጋ መርኃግብሩን ያዘጋጀውና ተጋባዦችን የጠራው አትላንቲክ ካውንስል መሆኑን ይናገራሉ። በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ደግሞ ማብራሪያውን የሰጡት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እናየውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፤ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ የመረጃ ፍሰት ቃል አቀባይ አምባሳደር ሬድዋንሁሴን እና የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ኤጄንስ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ናቸው።


በዕለቱ በስብሰባው ላይ የተገኙት በዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍፁም አረጋ፤ የማብራሪያ መርኃግብሩ የተዘጋጀው የኢትዮጵያ ጉዳይ ለሚያሳስባቸው መረጃ ለመስጠት እንደሆነ ገለፀው፤“በኢትዮጵያ ጉዳይላይ የተለያዩ መረጃዎች እየተሠራጩ ስላሉ የኢትዮጵያ መንግሥትን ትክክለኛ ሐሳብና ስልት እንዲሁምደግሞ በየወቅቱ እየሆኑ ያሉ ነገሮችን ትክክለኛ ግንዛቤ ለመስጠት ነው” ብለዋል።


ትግራይ ክልልን በተመለከተ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ የሚነሱት ጥያቄዎችእና የሚሰነዘሩት ክሶች በዛ ያሉ ናቸው። “ትግራይ ክልል ወረራ የተፈጸመበት ኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትነው” ከሚለው “የአማራ ክልል ልዩ ኃይል እና የኤርትራ ሠራዊት ከኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጋር በመሆን በጋራ ሆነው ጥቃት ፈፅመዋል” የሚለውም ይጠቀሳል። “በጦርነቱ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች መሰረተልማቶች ፈራርሰዋል፣ ዘረፋ ተፈፅሟል” የሚል ክስም ይቀርባል።


ከ4.5 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። ይህንን እርዳታ ለመስጠት የሚፈልጉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ደግሞ እንደልብ ተንቀሳቅሰው እርዳታውን መለገስ አልቻሉም። በዚህም የተነሳ በአሁኑ ሰዓትም የሰብዓዊ ቀውስ ቀውሱ እየተባባሰ ነው። የወደፊቱም በአስጊ ሁኔታ ላይ ይገኛል የሚሉ ስጋቶችም በመንፀባረቅ ላይ ይገኛሉ።


የኤርትራ የወታደር ክፍልም ከኢትዮጵያ መከላከታ ሠራዊት ጋር ተሰልፎ በሰላማዊ ዜጎች ላይ ጥቃት እያደረሰ እንደሆነ በስፋት ይገለፃል። ግድያ፣ዘረፋ፣መደፈር እና ሌሎች ኢ- ሰብዓዊ የሆኑ ጥቃቶች በክልሉ እንደደረሱምዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋማት በሚያወጧቸው ሪፖርቶች እየገለፁ ይገኛሉ። አዲሱ የፕሬዚዳንት ጆባይደን አሰተዳደር በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ አማካኝነት ባለፈው ሳምንት በሰጠው መግለጫም የኤርትራወታደሮች ከትግራይ ክልል በአስቸኳይ እንዲወጡ ጠይቋል።


አምባሳደር ፍጹም አረጋ በአትላንቲክ ካውንስል በነበረው የማብራሪያ ውይይት ላይ እነዚህ እና ሌሎች ጥያቄዎችም በማብራሪያው ወቅት መነሳታቸውን ጠቅሰው። በዕለቱ ለእያንዳንዱ ጥያቄዎች የተሰጡትን ምላሾች ዘርዝረዋል።


“የሕወሓት ጽንፈኛ አመራር ቡድን በሰጠው አመራር መከላከያ ሠራዊታችን ላይ ከፍተኛ የአገር ክህደትጉዳት ጭምር አድርሰዋል። ግድያና የጦር መሳሪያ ዘረፋ እንዲሁም ሌሎች ድርጊቶች በማድረጋቸውመንግሥት ለዛ አፀፋ መልሷል።  እዚህ ላይ ያለውን ብዥታ ጦርነቱን ማን እንደጀመረው በራሳቸው ሚዲያ ጭምር የገለጹት በመሆኑ ሁሉም ሁኔታውን በሚገባ እየተከታተለው ነው” ብለዋል።




 


የመንግሥት ባለሥልጣናቱ ሲያስረዱ የነበረው የሰብዓዊ እርዳታውን በተመለከተ መሆኑን የገለጹትአምባሳደር ፍፁም አረጋ፤ “እስካሁን በ92 የማሰራጫ ጣቢያዎች የእህል አቅርቦት በመንግሥት በኩልእየቀረበ ነው። እና የምግብም፣ የመድኃኒትም በአጠቃላይ የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፎች እየተሰጡ ነው” ካሉ በኋላ እነዚህ ቁሳቁሶች እየተሠራጩ ስላሉበት ሁኔታ በዝርዝር ቀርቧል ብለዋል።


ትግራይ ውስጥ በአሁኑ ሰዓት እርዳታ የሚያስፈልገው ሰው ቁጥር 4.5 ሚሊዮን እንደሆነ የክልሉ ጊዜያዊአስተዳደር የማኅበራዊ ጉዳይ  ቢሮ ኃላፊ አቶ አብርሃ ደስታ ዳሰሳ ጥናት ማድረጋቸውን ገልፀው ለአሜሪካ ድምፅ መናገራቸው ይታወሳል። በመንግሥትና እና በእርዳታ ሠራተኞች መካከል ከተደረገ ስብሰባ ሾልኮ የወጣ መረጃ በሚል በዚህ ዙሪያ ዘገባ ያስነበበው አሶሼትድ ፕሬስም ፤ በምግብ እጥረት የተነሳ በትግራይክልል ሰዎች ሕይወታቸው ማለፍ ጀምሯል ብሏል። 


ቁጥሩን የተመለከተው ጥያቄ በአትላንቲክ ካውንስሉስብሰባ ላይ ቀርቦ ነበር ያሉት አምባሳደር ፍፁም የመንግስትን ምላሽ ሲያስረዱ፤ “የሕግ ማስከበር እርምጃው ከመጀመሩ በፊት ትግራይ ውስጥ 1.8 ሚሊዮን ሕዝብ በሴፍቲ ኔት ፕሮግራም ታቅፎ እርዳታእያገኘ የሚኖር ሕዝብ ነበር። ግጭት ደግሞ የትራንስፖርት እንቅስቃሴውንም ሆነ ብዙ ነገሩንስለሚያስተጓጉል ወደ 700 ሺሕ የሚሆን ተጨማሪ ሕዝብ ለዚህ ችግር እንደተጋለጠ ነው። ስለዚህበድምሩ 2.5 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ተገቢው እርዳታ ያስፈልገዋል። ለአንድ ወር የሚሆን እርዳታምመንግሥት በእነዚህ የሥርጭት ጣቢያዎች እያደረሰ ነው” ብለዋል።




 


የእርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር ከዚህ በላይ እንደሆነ የሚናገሩ ሰዎች የሚጠቅሱት ቁጥር ግምት እንደሆነምገልፀዋል። “ብዙዎቹ ይህን እየሰጡ ያሉ እዛ ገብተን ለመዘገብ መረጃውን ለመናገር አልቻልንም ይላሉ።በሌላ በኩል ደግሞ ቁጥር ይሰጣሉ። የሚናገሩት የሚጋጭ ነው። መጀመሪያ ይህን ከፍተኛ ቁጥር የተናገሩትድርጅቶች መጀመሪያ ገብተን ለማጣራት አልቻልንም ግን ደግሞ ይህን ያህል ቁጥር ሕዝብ እርዳታያስፈልገዋል” ይላሉ ያሉት አቶ ፍፁም፤ “በእርግጥ ለሕዝቡ በማሰብ ይህንን እያሉ ከሆነ በጣም ጥሩእገዛውን ያድርጉ ሕዝቡን ይደግፉት። በኛ በኩል ግን የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚደረጉ ሁኔታዎችእንዳሉ እናያለን።” ብለዋል።


በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ በአራት የስደተኛ መጠለያ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞች፤በኤርትራ ወታደሮች ተይዘው ወደ ኤርትራ እየተመለሱ መሆኑን የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መስሪያቤት ቃል አቀባይ መረጃ እንዳለው በመግለፅ በጻፈው ደብዳቤ አስታውቋል። አምባሳደር ፍፁም ስደተኞቹስለሚገኙበት ሁኔታም የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በካውንስሉ ስብሰባ ላይ ማብራሪያሰጥተዋል ብለዋል።


“በአጠቃላይ እንግዲህ ኢትዮጵያ  አፋር ውስጥ ሁለት ፣ ትግራይ ውስጥ ደግሞ አራት  በአጠቃላይ ስድስትየስደተኛ ጣቢያዎች እንዳሉ ይታወቃል። ከአራቱ ውስጥ ሁለቱ ወደ ድንበር ሁለቱ ደግሞ ወደ መሃል ሽሬእንደነበሩ ይታወቃል። እነሱም ያሉበት ሁኔታ በሕግ ማስከበር ውስጥ የነበረ ችግር እንደነበረ አሁን ግንበተለይ መካከል አካባቢ ያሉት በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙና የተባበሩት መንግሥታት ደርሶ ተገቢ ድጋፍእስኪሰጣቸው ድረስ በኢትዮጵያ መንግሥት  በኩል በብድር መልክ የሚያዝ የተለያዩ የምግብ አቅርቦቶችእየተደረገ እንደሆነ እነዚህ ሁሉ ለጉብኝት ክፍት መሆናቸው ተገልፆላቸዋል” ሲሉ ሰፋ ያለ ማብራሪያሰጥተዋል።


የኤርትራ ወታደሮች በኢትዮጵያ ውስጥ በትግራይ ክልል መኖራቸው ብቻ ሳይሆን ኖረውም የሰብዓዊመብት ጥሰት እየፈፀሙ በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲወጡ የዩናይትድ ስቴትስ የጆ ባይደን አስተዳደር  በውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቃል አቀባይ በኩል ባለፈው ሳምንት ጠይቋል። ሌሎች ተመሳሳይ ሪፖርቶችምእየተሰሙ ይገኛሉ። አምባሳደር ፍፁም አረጋ ይህ ጥያቄ በአትላንቲክ ካውንስሉ ስብሰባ ላይ አልቀረበምወይ ከቀረበስ የኢትዮጵያ መንግስት ምን ምላሽ ሰጠ? ምላሹስ ምንድነው? ለሚለው ጥያቄ አምባሳደርፍፁም ሲመልሱ፤


“የኤርትራ ወታደሮች ኢትዮጵያ ውስጥ አሉ በሚል በተደጋጋሚ የሚገለፅ ነገር አለ። ይሄን በተመለከተየኤርትራ መንግሥት አልገባሁም ብሎ መግለጫ ሰጥቷል። ሁለተኛ የኢትዮጵያ መንግሥት የኤርትራወታደሮችን ግብዣ እንዳላቀረበ መኖራቸውንም እንዳላረጋገጠ ነው በተደጋጋሚ እየተነገረ ያለው።” ካሉበኋላ አያይዘው ሲመልሱ፤ “አንድ ግልፅ መሆን ያለበት ነገር ምንድነው? ድንበሩን የሚጠብቁ ወታደሮችጥቃት ሲደርስባቸው ድንበሩን የሚጠብቅ ማንም የለም። የኢትዮጵያ ሠራዊት በሕወሓት ጽንፈኛ ቡድንየተያዘውን ቦታ እያስለቀቀ ድንበሩ ድረስ እስኪደርስ ድረስ የኤርትራ ወታደሮች ገብተዋል አልገቡምየሚለውን የኢትዮጵያ መንግሥት ሊያረጋግጥበት የሚችልበት መንገድ ያለ አይመስለኝም። በዛ መካከልየተፈጠረውን ክፍተት የኤርትራ መንግሥት የሰጠውን መግለጫ ከመውሰድ ባለፈ የተለየ ነገር ማለትአስቸጋሪ ነው የሚሆነው።” ብለዋል።


በየቦታው የደረሱ በደሎችና ዘረፋዎች ስለመኖራቸው በአትላንቲክ ካውንስሉም ላይ መቅረቡንያስታወሱት አቶ ፍፁም፤ “ የሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን እየለቀቀ በሄደበት ግዜ ወደ 13 ሺሕ የሚደርሱበከፍተኛ ወንጀል የታሠሩ ሰዎችን ለቆ ስለነበር እነዚህ የተለቀቁ አካላት አንዳንድ ቦታ ታጥቀውምጭምር ከፍተኛ በደል ሊያደርሱ እንደሚችሉ ጥቆማ እየመጣ እንደሆነ ባለሥልጣናቱ ማብራሪያሰጥተዋል” ብለዋል።


በሌላ በኩል እሁድ ዕለት ይህንን ውይት መነሻ አድርጎ ዘገባ ያጠናቀረው አሶሼትድ የኢትዮጵያ መንግስትበክልሉ ነገሮች ወደነበሩበት እየተመለሱ ነው በሚል የብሬዚዳንት ጆ ባይደን አስተዳደርስ ሰዎች ባሉበትቢናገርም የዓይን እማኞች ግን ትግራይ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የረሃብ ስጋት እንዳለ ይገልፃሉ።


በትግራይ ክልል ውስጥ ከተከሰተው የሰብዓዊ ቀውስ ጎን ለጎን ተያይዞ የሚነሳው አሁንም ውጊያ መኖሩሲሆን ይህንን በተመለከተ ሰሞኑን ለዓለም የሰላም ፋውንዴሽን ከትግራይ ገጠራማ ቦታ ሆነው  በስልክቃለ ምልልስ እንደሰጡ የተገለፀውን የቀድሞ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣን ሙሉጌታገብረሕይወትን ቃል ጠቅሶ ኤፒ እንደዘገብው፤ በትግራይ ክልል አሁንም ውጊያው መቀጠሉን የኤርትራወታደሮች የአርሶ አደሩን ሰብል ካቃጠሉና ከዘረፉ በኋላ በኤርትራ ድንበር አካባቢ የሚገኙ ገበሬዎችበረሃብ መካከል መሆናቸውን ገልፀዋል።


በቅርቡም ከፍተኛ የሰብዓዊ ቀውስ ሊከተል ይችላል ሲሉ ስጋታቸውን አጋርተዋል። በሌላ በኩል ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ለጋሾች ሙሉ ለሙሉ ትግራይ ክልልእንዲገቡ በሚጠይቀው ማሳሰቢያው አሁንም በትግራይ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ውጊያው እንደቀጠገልጿል።


በሌላ በኩል በክልሉ ያለውን የጤና ሽፋን ሁኔታ በተመለከተ የድንበር የለሽ ሃኪሞች ማኅበር የትግራይክልል የአስቸኳይ ግዜ አስተባባሪ አልበርት ቪናስ ከታኅሣሥ ወር ጀመሮ ወደ ትግራይ ክልል ተጉዘውአዲግራት፣ አክሱም እና ዐድዋን ጎብኝተው ከተመለሱ በኋላ፤ ከሁለት ቀናት በፊት በድርጅቱ ድረ ገፅ ላይባስነበቡት አዲስ ሪፖርት፤ በትግራይ ክልል ገጠራማ አካባቢዎች ምን እየተፈጠረ እንደሆነ ማወቅባለመቻሉ ስጋት እንዳላቸው ነገር ግን ከአካባቢው ሽማግሌዎች መረዳት እንደቻሉት ሁኔታዎች እጅግአስቸጋሪ መሆናቸውን ገልፀዋል።


በአዲግራት ከተማ ከፍተኛ ውጥረት መኖሩን፣በሆስፒታሎች ውስጥ ያለው ሁኔታም እጅግ አስቸጋሪእንደሆነ፣ ምግብ፣ ውሃ እና ገንዘብ እንደሌለ  መመልከታቸውን በሪፖርታቸው አስነብበዋል። በሆስፒታልውስጥ የተኙት አንዳንዶቹ ታካሚዎች አሰቃቂ ጉዳቶች እንደደረሱባቸው አንዳንዶቹ ደግሞ በምግብእጥረት እንደተጎዱ መመልከታቸውን አስረድተዋል።




 


አምነስቲ ኢንተርናሽናል በበኩሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 2.3 ሚሊዮን ሰዎች ደግሞ በትግራይክልል የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ጠቅሶ፤ በግራይ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ጭፍጨፋ መፈፀሙን፣የቦንብ ድብደባ መድረሱን፣ ግድያ እና ዘረፋ እንዲሁም በሴት ልጆች ላይ ጾታዊ ጥቃት መፈፀሙ  ጠቅሶበአሁኑ ሰዓት 450 ሺሕ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል ብሏል። እነዚህን ዜጎች ለማገዝምመንግሥት ሙሉ ለሙሉ በሩን ለረድኤት ድርጅቶች መክፈት አለበት ሲል አሳስቧል።


በተያያዘም ሰሞኑን በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደረጉት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከፍተኛ ኮሚሽነርፊሊፖ ግራንዲ ከጉብኝታቸው በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ የተባበሩት መንግሥታት ተቋማትናመንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በክልሉ እንዲንቀሳቀሱ መፍቀድ እጅግ መሰረታዊ መሆኑን ገልፀው 25 መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ወደ ትግራይ ክልል እንዲገቡ ፍቃድ እንዲሰጣቸው በመጠባበቅ ላይመሆናቸውን ተናግረዋል።


በዚሁ መግለጫቸው ላይ ትግራይ ክልልን በተመለከተ በማኅበራዊ ሚዲያ ብዙ የተለያዩ ነገሮችእንደሚነገሩም ገልፀው ፤ እንደርሳቸው ቦታውን በአካል ተገኝቶ ለተመለከተ ግን ሁኔታው ምን ያህልየተወሳሰበ መሆኑን መገንዘብ እንደሚቻል ጥቆማ ሰጥተዋል። በርካታ የተኩስ ልውውጦች እና ጥሰቶችበሁሉም ወገኖች እንደነበሩና በገለልተኛ አካላት ምርመራ ሊደረግ እንደሚገባም ገልፀዋል። ሁኔታዎችተባብሰው ከቁጥጥር ውጭ ሳይወጡ አስቸኳይ እርዳታ በመስጠት ሰብዓዊ ቀውሱን ማስቆምእንደሚገባም ጠቁመዋል።


(የዘገባውን ሙሉ ክፍል ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ላይ ማዳመጥ ትችላላችሁ)




(ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5774223.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5774223.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 11 Feb 2021 15:27:31 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ጽዮን ግርማ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5774223.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/4317DF2F-41DD-4A4B-A44B-D00772627E30_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሰብዓዊ ረድኤት ሠራተኞች ትግራይ ለመሄድ ፈቃድ እየጠበቁ መሆኑን ዩ.ኤን አስታወቀ</title>
            <description>ሰማኒያ የሚሆኑ የተባበሩት መንግሥታት እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅት ሠራተኞች ወደ ትግራይ ክልል ለመጓዝ የሚያስችላቸውን ፈቃድ ለማግኘት አዲስ አበባ ሆነው ሲጠባበቁ አንድ ወር እንዳለፋቸው ድርጅቱ አስታውቋል። በተጨማሪም በክልሉ ያለው የሰብዓዊ ሁኔታ እየተባባሰ መምጣቱን በዚያ የሚገኙ ባልደረቦቻቸው እየገለፁላቸው መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴፈኒ ዱጃሪክ የአገራትን ሁኔታ በተመለከተ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አስታወቁ። 


ቃል አቀባዩ በዚሁ ማብራሪያቸው ላይ እንደጠቀሱት፤ በደህንነት ስጋት እና በቢሮክራሲ ችግር ምክኒያት ትግራይ ክልል ውስጥ እርዳታ ለሚፈልጉ ሰዎች በበቂ ሁኔታ ተደራሽ መሆን እንዳልተቻለ ገልፀው፤ ወደ ቦታው ገብቶ እርዳታውን ለመለገስ የተሰጠው ፈቃድ ውስን መሆኑን ተናግረዋል። 


በአሁኑ ሰዓት እየተሰጡ ያሉ ድጋፎች አጠቃላይ ከሚያስፈልገው ጋር ሲነፃፃር በቂ አለመሆኑን የገለፁት ቃል አቀባዩ ፤ ምንም እንኳን ድጋፋችንን ለማሳደግ ብንችልም አሁንም ከመቀሌ ወደ ሽሬ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኙ ሁለት የስደተኛ ካምፖች ውስጥ ያሉ ሰዎችን ለመርዳት ውስንነት እንዳለባቸው አስታውቋዋል። 


ይህም ሆኖ በአሁኑ ሰዓት በትግራይ ደቡባዊ ክፍል በሚገኙ ማይ-አይኒ እና አዲ ሃሩሽ በተሰኙ ሁለት የስደተኛ መጠለያ ውስጥ ለሚገኙ 250 ሺሕ ሰዎች ለሁለት ወራት የሚሆናቸውን ምግብ ማከፋፈል መቻሉን ገልፀዋል። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የሕክምና እቃዎችም ተገዝተው መላካቸውን ቃል አቀባዩ ጠቁመዋል። 


አያይዘውም ትግራይ እና በአማራ ክልል የሚፈፀሙ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል እና ጥቃቱ ለደረሰባቸው ተጎጂዎችም እገዛ ለማድረግ አጋሮቻቸው እየረዷቸው መሆኑን ገልፀዋል። የሰብዓዊ እርዳታውን ለማድረስ ለእርዳታ ሠራተኞች የኢትዮጵያ መንግሥት ያልተገደበ ፈቃድ እንዲሰጥ ጥያቄ ማቅረባቸውን እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5771022.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5771022.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 09 Feb 2021 10:58:05 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ጽዮን ግርማ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5771022.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/4D7C8E38-BBA0-4E46-9809-CF9DB7177B16_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ቶኒ ብሊንከንና ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተነጋገሩ</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ ስልክ ደውለው አነጋግረዋቸዋል።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/secr-tony-blinken-called-pm-abiy-ahmed-of-ethiopia-02-04-2021/5765790.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/secr-tony-blinken-called-pm-abiy-ahmed-of-ethiopia-02-04-2021/5765790.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 05 Feb 2021 01:45:04 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><comments>https://amharic.voanews.com/a/secr-tony-blinken-called-pm-abiy-ahmed-of-ethiopia-02-04-2021/5765790.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0C2BF1D6-2F93-4EB9-B88F-07B6FDA065CA_cx17_cy0_cw81_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሥልጣናቸው ግፊት የበዛባቸው ትረምፕ ስለ አመጹ ተናገሩ</title>
            <description>ፕሬዘዳንት ትረምፕ ትናንት በቪዲዮ ተቀርጾ በወጣው መልዕክታቸው፣ በዚህ ሳምንት ደጋፊዎቻቸው የተወካዮች ምክርቤት ህንጻን በመውረር፣ ያሳዩት አመጽ፣ ሁከትና ህገወጥነት ያስቆጣቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የአመጹን ድርጊት ተክትሎ፣ &quot;ትረምፕ ከሥልጣን መወገድ አለባቸው&quot; ከሚሉ የዴሞክራቲክና ሪፐርብሊካን ፓርቲ አባላትም ከፍተኛ ግፊት እየደረሰባቸው ነው፡፡


በዚህ ሳምንት፣ በፕሬዚዳንት ትረምፕ ደጋፊዎች ፣ በዩናይትድ ስቴትስ ተወካዮች ምክር ቤት ህንጻ ላይ የተካሄደው ወረራ፣ ከብዙ ሰዎች ጭንቅላት ውስጥ ገና አልወጣም፡፡ ፕሬዚዳንት ትረምፕ አመጹን አስመልክቶ፣ ትናንት ሀሙስ፣ ምሽቱ ላይ፣ በቪዲዮ ምስል ያሰራጩት መግለጫ የወጣው አገሪቱ በዚህ ስሜት ውስጥ እንዳለች ነው፡፡


&quot;እንደ ሁሉም አሜሪካውያን በአመጹ ህወገጥነቱና ሁከቱ በጣም አስቆጥቶኛል፡፡&quot;


ትረምፕ፣ ምክርቤቱ የምርጫውን ውጤት በማረጋገጥ ማጽደቁን ቢቀበሉም፣ ባለው ልማድ መሠረት፣ ለተመራጩ ፕሬዚዳንት የሚላከውን የእንኳን አደረሰህ መልዕክት በንግግራቸው ውስጥ አልጨመሩም፡፡ እንዲህ አሉ


&quot;አሁን የኔ ትኩረት ሰለማዊው የሥልጣን ሽግግር፣ ያለምንም እንከን፣ በተገቢው ስርዓት መካሄዱን ማረጋገጥ ነው፡፡&quot;


ጆ ባይደን፣ ከትረምፕ ንግግር ቀደም ብለው ሀሙስ ጧት ባሰሙት ንግግር፣ ትረምፕን በድጋሚ ገስጸዋቸዋል፡፡


&quot;በተቋሞቻችና ዴሞክራሲያችን ላይ በሁሉም መስክ ጥቃት መፈጸም የጀመሩት፣ ገና ከመነሻው ጀምረው ነው፡፡ ትናንት ያደረጉትም የዚያ የማያማቋረጠው ጥቃት ድምር ውጤት ነው፡፡&quot;


ባይደን ፕሬዚዳንት ትረምፕ አመጹ እንዲቀሰቀስ በማድረጋቸው፣ ከሥልጣን መወገድ ይገባቸዋል የሚለውን ውትወታ አስመልክቶ በንግግራቸው ውስጥ ምንም ያሉት ነገር የለም፡፡ መጭው የእንደራሴዎች ምክር ቤት መሪ ይሆናሉ የተባሉት ቻክ ሹመርና የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ናንሲ ፖሎሲ ግን፣ ፕሬዚዳንቱን በብቃት ጉድለት ከሥራቸው እንዲወገዱ የሚያስችለውንና የተሻሻለውን የህግመንስቱን አንቀጽ 25 በመጥቀስ፣ እየወተወቱ ነው፡፡ እንዲህ ይላሉ ፐሎሲ


&quot;በትናንትናው እለት የተካሄደውን አመጽ በማነሳሳታቸው ከሥልጣናቸው የግድ መወገድ ይገባቸዋል፡፡ ገና 13 ቀን የሚቀራቸው ቢሆንም፣ የትኛውም ቀን፣ በአሜሪካ ዘግናኝ የሆነ ክስተት የሚታይበት ቀን ሊሆን ይችላል፡፡&quot;


የሪፐብሊካን ፓርቲው የተወካዮች ምክር ቤት አባል አዳም ኪንዚንገርም በኩላቸው እንዲህ ብለዋል


&quot;ሁሉም ነገሮች የሚያሳዩት፣ ፕሬዘዳንቱ ከኃላፊነታቸውና ሌላው ቀርቶ የገቡትን ቃለ መሃላ የዘነጉ ብቻ ሳይሆኑ፣ ካለው እውነታ ራሱ እጅግ የራቁ ናቸው፡፡&quot;


የህገመንግስቱ የማሻሻያ አንቀጽ 25፣ ተግባርና ኃላፊነቱን በሚገባ መወጣት ያልቻለን ፕሬዚዳንት፣ በምክትል ፕሬዚዳንቱና በአብዛኞቹ የካቢኔ አባላት ድምጽ ማስወገድ የሚቻልበትን አግባብ ይፈቅዳል፡፡ ከምክትል ፕሬዚዳንቱም ሆነ ከካቢኔ አባላቱ ግን ይህንን እርምጃ በመደገፍ ድምጹን ያሰማ የለም፡፡ ይህን አስመልክቶ ከአሜሪካ ኤንተርፕራይዝ ተቋም ጆን ፎርቲየ እንዲህ ይላሉ


&quot;ከቀሩት ቀናት አንጻር፣ በህግም ሆነ እርምጃውን ተግባራዊ ከማድረጉ አንጻር አንዳንድ መሰናክሎች ሊገጥሙ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ መደረጉን ሊደረግ ይችል ይሆናል፣ ይሁን እንጂ ግን በጣም በጣም አስቸጋሪ ይሆናል፡፡&quot;


በሌላም በኩል፣ የፌደራል አቃቢ ህግ፣ በተካሄደው አመጽ ዙሪያ ምርመራ እንደሚያደርግና፣ ወንጀለኞችም ላይ ከስ እንደሚመስረት አስታውቋል፡፡ ያ ምናልባትም፣ የምክር ቤት አባላት፣ የምርጫውን ውጤት በማጽደቅ የባይደንን አሸናፊነት እንዳያረጋግጡ፣ ደጋፊዎቻቸውን ወደ ምክር ቤቱ ህንጻ እንዲያመሩ በመገፋፋት፣ አመጹን አነሳስተዋል የሚባሉትን ፕሬዚዳንት ትረምፕንም የሚጨምር ሊሆን እንደሚችል ተነግሯል፡፡


ትረምፕ “በምርጫው ልሸነፍ የምችለው ምርጫው ከተጭብረበረ ብቻ ነው” የሚለውን ለወራት ሲናገሩ ቆይተዋል፡፡ በጋርዮሽ ከሚሰራው የፖለሲ ተቋም ጄሰን ጋርመት እንዲህ ይላሉ፤


 &quot;እሚታዩት ምስሎች በጣም አስደንጋጭና አሳዛኝ ናቸው፡፡ እና እኔ እንደሚመስለኝ፣ እንዳለመታደል ሆኖ፣ ፕሬዚዳንቱ ለዴሞክራሲ ካላቸው ንቀት አንጻር፣ ውጤቱ ይህ ሊሆን እንደሚችል ሲጠበቅ የቆየ ይመስለኛል፡፡


አፈጉባኤዋ ናንሲ ፐሎሲ፣ ምክትል ፕሬዚዳንት ማይክ ፔንስ የህግ መንግስቱን ማሻሻያ አንቀጽ 25 በመጥቀስ ምንም እንቅስቃሴ የማያደርጉ ከሆነ፣ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንቱን ከሥልጣናቸው ለማንሳት፣ የሚያስችለውን የፖለቲካ ውሳኔ ይሰጣል ብለዋል፡፡ ትረምፕ እኤአ በ2019 መገባደጃው ላይ፣ ከሥልጣናቸው እንዲነሱ በተወካዮች ምክር ቤት የፖለቲካ ውሳኔ የተላለፈባቸው ቢሆንም፣ የህግ መወሰኛው ምክር ቤት፣ እኤአ የካቲት 2020 ሳይደግፈው በመቅረቱ ውሳኔው ውድቅ መሆኑ ይታወሳል፡፡ ዘገባው በቪኦኤ የዋይት ሀውስ ዘጋቢ የፓትሲ ውዳክስዋራ ነው፡፡


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/trump-congress-capitol-1-8-2021/5730223.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/trump-congress-capitol-1-8-2021/5730223.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 08 Jan 2021 20:10:16 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><category>የዩናይትድ ስቴትስ ምርጫ - 2020</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/trump-congress-capitol-1-8-2021/5730223.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/8f4d71b6-918a-4f98-b16d-9a4cbf909ea4_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የባይደን አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሂደትና በምክር ቤቱ ህንጻ የተካሄደው አመጽ</title>
            <description>የዩናይድ ስቴትስ ምክር ቤት ባለፈው ህዳር የተካሄደው የአሜሪካው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አሸናፊ ዴሞክራቱ ጆ ባይደን መሆናቸውን ማረጋገጫ ሰጥቷል፡፡


ምክር ቤቱ ማረጋገጫውን የሰጠው በትናንትናው እለት የተሰናባቹ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ደጋፊዎች፣ የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤትን በመውረር፣ ህገ አውጭዎቹ  የምክር ቤት አባላት ስብሰባቸውን በማቋረጥ፣ ህንጻው ለቀው እንዲወጡ ካስገደዷቸው በኋላ፣ ህገ መንግስታዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ባደረጉት የድጋሚ ስብሰባ ነው፡፡


ተቋርጦ የነበረውን ስብሰባ የመሩት ምክትል ፕሬዚዳንት ፔንስ፣ የየክፍለ ግዛቶቹ ተወካዮች ለባይደን 306 እንዲሁም ለትራምፕ 232 ድምጽ የሰጡ መሆናቸው መረጋገጡን ይፋ አድርገዋል፡፡


የምክር ቤቱ አባላት ከትናንት ምሽት ጀምሮ እስከ ዛሬው ሀሙስ አጥቢያ ድረስ የክፍለ ግዛቶቹን ተወካዮችን ድምጽ ቁጥር ለማረጋገጥ ጥድፊያ ላይ ነበሩ፡፡


የፕሬዚዳንት ትራምፕ ደጋፊዎች የምክር ቤቱን ህንጻ ከወረሩ ሰዓታት በኋላ ሁለቱም የዴሞክራቲክና የሪፐብሊካን ፓርቲ ህግ አውጭዎች የተመራጩን ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን አሸናፊነት ለማረጋገጥ ቁርጠኞች እንደነበሩም ተናግረዋል፡፡


በትላንትናው እለት በሺዎች የሚቆጠሩ የትራምፕ ደጋፊዎች ከህግ አሰከባሪዎች ጋር ግብግብ በመፍጠር የተወካዮቹን ምክር ቤቶች ወረዋል፡፡ ይሁን እንጂ በዚያው ምሽት፣ በጥድፊያ ወደ ምክር ቤቱ የተመለሱ ህግ አውጭዎች፣ ቀደም ሲል ያቋረጡትን ስብሰባ በመቀጠል የፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውድድር አሸነፊ የሆነውን ለመወሰን፣ በየክፍለ ግዛቱ ተወካዮች የተሰጠውን ድምጽ በመቁጠር አጽድቀዋል፡፡ የህግ መወሰኛው ምክር ቤት መሪ ሚች መካኔል


“ለፕሬዘደንታዊው ምርጫ አሸናፊ ማረጋገጫውን እንሳጠለን” ብለዋል፡፡


ምክትል ፕሬዚዳንት ማይክ ፔንስ በህግ መወሰኛው ምክር ቤት ፕሬዘደንትነታቸው ባላቸው ሥልጣን በአመጹ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ስብሰባ ከሰዓታት በኋላ ሲያስጀምሩ


“ዛሬ በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ታሪክ የጨለማው ቀን ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ፖሊሶች፣ የፌደራል፣ የክፍለ ግዛቶችና የአካባቢው ህግ አስከባሪዎች ምስጋና ይግባቸውና እነሱ ባደረጉት ፈጣን ጥረት አመጹ በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡” ብለዋል፡፡


ከመቶ በላይ የሚሆኑ የሪፐብሊካን ፓርቲ የተወካዮች ምክር ቤት አባላት እና 14 የህግ መወሰኛው ምክር ቤት አባላት ከመነሻው ያሰቡት የተለየ ነገር ነበር፡፡ የምርጫውን ውጤት፣ በተለይም ባይደን አሸንፈዋቸዋል ባሏቸው 6 አሻሚ በተባሉ ክፍለ ግዛቶች ያለውን የማረጋገጫ ሂደቱን ማስተጓጎል ነበር፡፡ የምክር ቤቱ አባል ጃሽ ሀውሌይ በእለቱ ከታየው አመጽ ይልቅ


“ ስለምርጫችን ትክክለኝነትና ፍትሀዊነት፣ ባለፈው ህዳር ወር ስለሆነው ነገር ቅሬታ ላላችሁ ወገኖች ሁሉ ቅሬታን የማቅረቢያው ትክክለኛው መንገድ ይኽ ነው፡፡” ብለዋል፡፡


ይሁን እንጂ ትላንት ረቡዕ የተነሳው አመጽ፣ በርካታዎቹ ህግ አውጭ የምክር ቤት አባላት፣ ቀደም ሲል የነበራቸውን ተቃውሞ እንዲተው አድርጓቸዋል፡፡ተከታዩን የተናገሩት ሴነተር ኬሊ ከእነዚህ አንዷ ነበሩ፡፤


“ዛሬ በግልጽ የታየው ክስተት ውሳኔዬን እንደገና እንድመረምረው አድርጎኛል፡፡ የምርጫውን ውጤት የሚያረጋግጠውን ሂደት ለመቃወም አሁን ልቦናዬ አይፈቅድልኝም፡፡”


ተመራጩ ፕሬዚዳንት ጆ ባይ ደን አመጹን ያወገዙ ሲሆን ከደለዌር ክፍለ ግዛት ዊሊምግተን ሆነው ባሰሙትን ንግግር፣ ለፕሬዚዳንት ትራምፕ ጠንካራ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡


“ፕሬዚዳንት ትራምፕ፣ ህገ መንግሥቱን ለመጠበቅ የገቡትን ቃለ መሃል በማክበር፣ አሁኑኑ በአገር አቀፍ ደረጃ ወደሚሰራጭ ቴሌቪዥን ወጥተው ይህን የአመጽ ወረራ እንዲያስቆሙ ጥሪዬን አቀርባላችኋለሁ!”


ትራምፕ ትዊተር ላይ ባስተላለፉት በቪዲዮ የተቀዳ መልዕክታቸው መረጋጋት እንዲኖር ጥሪ ያስተላለፉ ቢሆንም፣ ምርጫው ተጭበርበሯል የሚለውን መሰረት የለሹን ክሳቸውን፣ እንደሚከተለው ማሳተላለፋቸውን ቀጥለውበታል፡፡


“ከዳር እስከዳር ያሸነፍንበት ምርጫ ነው፡፡ ሁሉም ሰው ያውቀዋል፡፡ በተለይም በሌላ ወገን ያሉት፡፡ ለማንኛውም አሁን ወደ የቤታችሁ መሄድ አለባችሁ፡፡”


ትዊተርና ፌስ ቡክ የተባሉት ማህበራዊ የትስስር ድረገጾች፣ ለመጀመሪያ ጊዜ የፕሬዘዳንት ትራምፕ ድርጊት ፖሊሲያቸውን የሚጥስ መሆኑን በመግለጽ በድረ ገጾቹ የፕሬዚዳንቱን የግል መልዕክት ማስተላለፊያቸውን በመዝጋት አግደዋቸዋል፡፡ ትራምፕ ቀደም ሲል ደጋፊዎቻቸው ወደ ምክር ቤቶቹ እንዲያመሩ


“ከዚህ በኋላ ወደዚያው እንጓዛለን፡፡ እኔም እዚያው ከናንተ ጋር እገኛለሁ፡፡” በማለት አሳስበዋቸዋል፡፡


“ደካማዎቹን የምክር ቤት ሰዎች አስወግዱ” ብሎ ለደጋፊዎቻቸው መናገር ማለት ምን ማለት ነው ይላሉ፤ በቴክሳስ ኤ ኤንድ ኤም (A&amp;M) ዩኒቨርስቲ ስለ ፕሬዚዳንታዊ ንግግሮች የሚያስተምሩት ጀኒፈር መርሲያ


“አመጹን አነሳስተዋል፡፡ በአካል ተገኝተው ባይመሯቸውም በንግግራቸው መርተዋቸዋል፡፡” የሚል አስተያየት ሰጥተዋል፡፡


17 ዴሞክራት የሆኑ የተወካዮች ምክር ቤት አባላት ምክትል ፕሬዚዳንቱ ማይክ ፔንስ የህገ መንግስቱን ማሻሻያ አቀንጽ 25 በመጠቀም ትራምፕን በአስቸኳይ ከሥልጣናቸው እንዲያነሱ ጠይቀዋል፡፡ ትራም የፕሬዚደንትነት ዘመናቸው ሊያበቃ ሁለት ሳምንታት የሚቀረው በመሆኑ የተፈጻሚ መሆኑ ግን አጠራጣሪ ነው፡፡ በቺካጎ ዩኒቨርስቲ የህገ መንግሥት መምህር የሆኑት አዚዝ ኻክ እንዲህ ይላሉ


“እንደ እውነቱ ከሆነ የህገ መንግሥቱ ማሻሻያ አንቀጽ 25 የሚያነሳው ስለ ብቃት ማነስ እና በአካልም ሆነ በጤንነት ምክንያት ማልገል ስላለመቻል ነው እንጂ ስለፕሬዚዳንቱ የሥነልቡና ብቃት አይደለም፡፡”


ይሁ ሁሉ ሁከት ቢኖርም፣ ጆ ባይደን 46ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት በመሆን፣ እኤአ ጥር 20/2021 በዓለ ሲመታቸውን ያከብራሉ፡፡ ይሁን እንጂ ባይደን


“እኔ ስለራሴ ደህንነት ወይም ፕሬዚዳንት የመሆኛዬ ቀን ስለሚከበርበት በዓለ ሲመቴ አይደለም የማስበው፡፡ እሱ አያሳስበኝም፡፡” ብለዋል፡፡


በሌላም በኩል ህግ አውጭዎቹ የምክር ቤት አባላት የትናንቱን ሁከት በመቆጣጠር ከፍተኛ ተጋድሎ ይደረጉትን የፖሊስና ህግ አስከባሪ አካላት አድናቆታቸውን ቢገልጹም ቀድሞውኑም ቢሆን እንዲህ ያለ ነገር እንዴት ሊከሰት እንደቻለ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቀዋል፡፡ በተለይም በአዲሱ ህግ አውጭ ምክር ቤት የምክር ቤቱን ህንጻና አስተዳደር በጀት ኮሚቴ የሚመሩት ሁለቱ ዴሞክራቶች


“ብዙ ቪዲዮች አሉ፣ አንዳንዶቹ ጀግንነትን የሚያሳዩ ቢሆንም አንዳንዶቹ ግን አሳሳቢ ናቸው፡፡” ብለዋል፡፡ “ሙሉ ምርመራ ተደርጎ የምክር ቤቱ ህንጻ በዚያ ፍጥነት እንዴት ሆኖ ሊወረር እንደቻለ የጥበቃውና የደህንነቱ ሁኔታ እንደገና ሊመረመር እንደሚገባውም” አሳስበዋል፡፡


“የፕሬዘዳንቱን መሰረት ቢስ ቅሰቀሳ ሰምተው ቀደም ሲል ለተቃውሞ አመጽ የተዘጋጁ ሰዎች መኖራቸው እየታወቀ ለምን በቂ ዝግጅት አልተደረገም” የሚሉም ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡


ሌላኛዋ የምክር ቤት አባል የሆኑት ኢሃን ኦማር እንዲህ ብለዋል


&quot;ለብሄራዊ ደህንነት ጥበቃ በቢሊዮን ዶላሮች እናወጣለን፡፡ በዛሬው እለት በአገሪቱ ምክር ቤት ላይ ህገ ወጥ ነውጠኞች ያደጉትን ወረራ ግን ማስቆም አልቻልንም፡፡ ይህ ተቀባይነት የለውም!&quot;


ዘገባው በቪኦኤ ዘጋቢ ፓትሲ ውዳክስዋራ እና በቪኦኤ የዜና ክፍል ባልደረቦች ከተጠናቀሩት ዘገባዎች የተወሰዱ ናቸው፡፡


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-electoral-collage-vote/5728916.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-electoral-collage-vote/5728916.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 07 Jan 2021 22:41:30 +0300</pubDate>
            <category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>የዩናይትድ ስቴትስ ምርጫ - 2020</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/us-electoral-collage-vote/5728916.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/FCC8D7AE-9AFD-4F4B-BE15-A0A70FB739A7_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በቤንሻንጉል ጉምዝ ከ100 በላይ ሰላማዊ ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ከጥቃቱ ያመለጡ ገለፁ</title>
            <description>በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ በኩጂ ቀበሌ ውስጥ ከመቶ በላይ ሰላማዊ ሰዎችበታጣቂዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች እየተናገሩ ነው። የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልላዊ መንግሥትም ጥቃቱበሲቪሎቹ ላይ መፈፀሙን አረጋግጧል።


ከዚህ ጥቃት ማምለጣቸው ለአሜሪካ ድምፅ የገለፁልን ነዋሪዎች፤ ጥቃቱን የፈፀሙት የክልሉን ልዩ ኃይልየደንብ ልብስ የለበሱ መሆንቸውን ተናግረዋል። ያነጋገርናቸው ሁለቱ ነዋሪዎች  የተገደሉትን ሰላማዊሰዎች ቁጥር ወደ 100 ያደርሱታል። 


የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የመንግሥት ኮምዩንኬሽንስ ጉዳዮች ቢሮኃላፊ አቶ መለስ በየነም የሟቾች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።


(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)






 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5711021.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5711021.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 23 Dec 2020 22:43:42 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (አስቴር ምስጋናው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5711021.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5A23478B-25C3-4373-9AE5-CAE1C69BBF52_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ በመተከል</title>
            <description>ወደ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዛሬ ሄደው ከዞኑ ነዋሪዎች ጋር የተወያዩት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአካባቢው የህግ የበላይነትን ማስከበር ዋነኛ አጀንዳቸው መሆኑን አስታውቀዋል።


ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር የሰላም ሚኒስትሯና የሃገሪቱ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም አብረው ነበሩ።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ዛሬ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን በመገኘት ከተመረጡ የሀገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ምክትልርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ  ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል። 


ነዋሪዎቹ በክልሉ ውስጥ እየታዩ ያሉ ችግሮችን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳነሱላቸው አቶ ጌታሁንተናግረዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትር  አብይ ከነዋሪዎቹ በተነሱት ሀሳቦች ላይ የተካሄደውን ውይይት ከመሩ በኋላ የሠነዘሯቸውን ሃሣቦችና የሰጧቸውን መመሪያዎች በተመለከተ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እንዲህ ብለዋል።






 


 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5709312.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5709312.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 22 Dec 2020 22:54:32 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (አስቴር ምስጋናው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5709312.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/06A0F210-B4D5-4F2D-896D-B8FAD324F360_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>&quot;የኢትዮጵያ መንግሥት ትግራይ ክልል ውስጥ ያካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ ህጋዊ ነው” - ሙሳ ፋኪ ማሃማት</title>
            <description>የኢትዮጵያ መንግሥት ትግራይ ክልል ውስጥ ያካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ “ህጋዊ ነው” ሲሉየአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ተናግረዋል።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/igad-summit-/5708100.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/igad-summit-/5708100.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 22 Dec 2020 01:41:50 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/igad-summit-/5708100.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/CBB70026-13D9-49FE-B21F-CD23A0AF1851_cx0_cy11_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከአቶ ነብዩ ስሁል ሚካኤል ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ</title>
            <description>የትግራይ ብልፅግና ፓርቲን ጨምሮ በአገር እና በክልል ደረጃ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትየተካተቱበት የጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ተቋቁሞ ሥራ መጀመሩን የትግራይ ክልል ብልፅግና ጽ/ቤትኃላፊ አቶ ነብዩ ስሁል ሚካኤል ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5706523.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5706523.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 20 Dec 2020 17:06:00 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ጽዮን ግርማ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5706523.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9938214F-2309-4026-9BF8-ABFF6C0C0828_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአዲስ አባባ በፈነዳ የእጅ ቦንብ ሦስት ሰዎች ሲሞቱ አምስት ቆስለዋል</title>
            <description>በአዲስ አበባ ከተማ ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት ልዩ ቦታው “ስልጤ መስጅድ ጀርባ” እየተባለ በሚጠናው አካባቢ ለልማት በታጠረ ቦታ ላይ በፈነዳ የእጅ ቦንብ፤ ሦስት ሰዎች ሲሞቱ አምስት ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5706505.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5706505.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 20 Dec 2020 16:34:14 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ፀሐይ ዳምጠው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5706505.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/E7402B10-0D2B-4920-B2C1-33044498FB32_cx18_cy0_cw76_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የጉምዝ ታጣቂዎች በአዊ ዞን ጥቃት ማድረሳቸውን አስተዳደሩ ገለፀ</title>
            <description>በአማራ ክልል በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጓንጓ ወረዳ መንግሥት “የጉምዝ ታጣቂዎች ናቸው” ያላቸው በአርሶ አደሮች ላይ ጥቃት  መፈፀማቸውን ገልጿል።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5705787.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5705787.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 19 Dec 2020 15:52:06 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (አስቴር ምስጋናው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5705787.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5B89FB26-102B-4869-89DC-01651D6AC966_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በማይካድራ በጅምላ የተቀበሩ ሰዎች ፀሎተ ፍትሃት ተደረገላቸው</title>
            <description>በማይካድራ በጅምላ የተቀበሩ ሰዎች ፀሎተ ፍትሃት ተደርጎላቸው አስክሬናቸው ቤተክርስቲያ ውስጥ እንዲያርፍ ተደረገ። ሰሞኑን ሰሜን ኢትዮጵያ የሚገኘው የሃዋሳው ዘጋቢያችን ዮናታን ዘብዲዮስ ዛሬ ውሎውን ማይካድራ አድርጎ ነበር። የሟቾች ፀሎተ ፍትሃት ሲደረግም ተከታትሏል።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5705243.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5705243.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 19 Dec 2020 00:23:27 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><category>Ethiopian Refugee Crisis</category><author> voadigital@voanews.com (ዮናታን ዘብዴዎስ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5705243.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/22F01425-7248-4E15-995A-AF3FE4BF2521_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኢትዮጵያ እና በሱዳን የፀጥታ ሃይሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት</title>
            <description>ማክሰኛ ዕለት በኢትዮጵያ እና በሱዳን የፀጥታ ሃይሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት በሁለቱ አገራትከፍተኛ ባለስልጣናት ውይይት እንደሚደረግበት ተገልጿል::</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5704654.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5704654.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 18 Dec 2020 16:09:54 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5704654.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/795F5151-7B87-4D67-9F5F-0B127E87B7E0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የተባበሩት መንግሥታቱ ድርጅት የኤርትራውያን ስደተኞች ጉዳዮች አሳስቦኛል አለ።</title>
            <description>በሰሜን ኢትዮጵያ የትግራይ ክልል በውጊያውምክንያት ካምፖቻቸውን ጥለው የሸሹ ኤርትራውያን ስደተኞች በግድ ወደካምፖቻቸው እንዲመለሱ እየተደረገ መሆኑ አሳስቦኛል ሲል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተናገረ።


የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮምሽነር በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች በአውቶቡስወደ ስደተኛ ጣቢያዎቹ እየተወሰዱ ስለመሆኑ ሪፖርት ደርሶናል ብሏል።


የኢትዮጵያ መንግሥት “የመከላከያ ኃይላችን በትግራይ ክልል የሕወሃት ኃይሎች ላይ ድል ተቀዳጅቷል” ስለሆነም ስደተኞቹ ወደካምፖቻቸው ቢመለሱ የሚያሰጋ ነገር አይኖርም ማለቱን ዜናው ጠቅሱዋል።


የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮምሽነር ፌሊፔ ግራኒዲ ትናንት ዓርብ ባወጡት መግለጫቸው የድርጅቱ የረድዔት እና ሌሎችም ድርጅቶች ወደክልሉ ለመግባት በተከለከሉበት ሁኔታ ስደተኞቹ መመለሳቸው ያሳስበናል ብለዋል።


ዘጠና ስድስት ሺህ ኤርትራውያን ስደተኞች በተጠለሉባቸው የስደተኛ ካምፖች የምግብ ዕጥረት አለ ብለን እናምናለን ያሉት የረድዔት ድርጅቶች በአንዳንዶቹ የትግራይ አካባቢዎች ውጊያ አሁንም እንዳለ የሚገልጹ ሪፖርቶች አሳስበውናል ሲሉም አስታውቀዋል።


የዩ ኤን ኤች ሲ አር ከፍተኛ ኮምሽነር ፌሊፔ ግራንዲ በመግለጫቸው የኢትዮጵያ መንግሥት የመንግሥታቱ ድርጅት የረድዔት መስሪያ ቤቶች እና አጋሮቻቸው “ወድ ክልሉ ደህንንታቸው ተጠብቆ መግባት እንዲችሉ ዋስትና እሰጣለሁ” ማለቱ መልካም የመጀመሪያ ርምጃ ነው፤ ሆኖም የተፈረመው ስምምነት ባስቸኩዋይ ስራ ላይ ውሎ ለስደተኞቹና ለሌሎቹም ተጎጅዎች አጣዳፊ ርዳታ ይዘን መድረስ እንድንችል ሊደረግ ይገባል ሲሉአሳስበዋል

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/un-eritrean-refugee-situation-in-ethiopia-12-12-20/5697245.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/un-eritrean-refugee-situation-in-ethiopia-12-12-20/5697245.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 13 Dec 2020 00:09:55 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (አሉላ ከበደ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/un-eritrean-refugee-situation-in-ethiopia-12-12-20/5697245.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/C0157852-BCD1-4ECC-AEA9-943C54210708_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ክርክር በኢትዮጵያ የዛሬ ሁኔታ ላይ</title>
            <description>ኢትዮጵያ ውስጥ ላለው በፌደራል መንግሥቱና በህወሓት መካከል በተፈጠረው ሁኔታ መወያየና መደራደር ያስፈልጋል ወይስ አያስፈልግም? ለዚህ ግጭት ተጠያቂው ማንነው? ወደ የት እያመራ ነው? መፍትኄስ አለው?</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/debate-on-situation-in-ethiopia-amb-fisseha-asgedom-vs-ato-neamen-zeleke/5680640.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/debate-on-situation-in-ethiopia-amb-fisseha-asgedom-vs-ato-neamen-zeleke/5680640.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 29 Nov 2020 21:11:17 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ሰሎሞን አባተ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/debate-on-situation-in-ethiopia-amb-fisseha-asgedom-vs-ato-neamen-zeleke/5680640.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/FFD2BAB0-879B-42FC-9C5D-0847D15DD0E2_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title> &quot;መንግሥት መቀሌን ተቆጣጥሯል&quot; ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ</title>
            <description>&quot;የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት መቀሌን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል&quot; ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-tigrai-mekele/5679989.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-tigrai-mekele/5679989.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 28 Nov 2020 22:16:59 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-tigrai-mekele/5679989.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/02463FA1-E1C0-41BA-99E9-06E8FF372BF4_cx13_cy0_cw77_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>