<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>ዩናይትድ ስቴትስ - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/3177</link>
        <description>americana</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>ዩናይትድ ስቴትስ - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/3177</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Sat, 25 Apr 2026 04:32:06 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zirjrejtjr" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>ምክትል ፕሬዚዳንት ከማላ ኻሪስ ከሺ ጂፒንግ ጋር ተነጋገሩ</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዚዳንት ከማላ ኻሪስ ከቻይናው መሪ ሺ ጂፒንግ ጋር በባንኮክ በተካሄደው የእስያ ፓስፊክ ኢኮኖሚ ትብብር ፎረም ወደ ዝግ ስብሰባ ከመግባታቸው በፊት ለአንድ አፍታ ቆይታ አድርገው መነጋገራቸው ተነገረ፡፡


“ምክትል ፕሬዚዳንቷ፣ ባለፈው ሰኞ ህዳር 5 ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን፣ ከፕሬዚዳንት ሺ ጂፒንግ ጋር ተገናኝተው በተነጋገሩበት ወቅት፣ በሁለቱ አገሮቻችን መካከል ያለውን ውድድር በኃላፊነት ለመምራት የግንኙት መስመሮቻችንን ክፍት ማድረግ ይኖርብናል ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩትን ቁልፍ መልዕክት አስታውሰዋል ሲል” ዋይት ሀውስ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡


የምክትል ፕሬዚዳንቷ መልዕክት ቻይናን ሊያስከፋ ከሚችለው የፊሊፒንሷ ደሴት ፓላዋን የማክሰኞ ጉብኝታቸው ጋር ሊቃረን እንደሚችል ተገምቷል፡፡


ቻይና በደቡብ ቻይና ባህር በምትገኘዋ ፓላዋን ደሴት አካባቢ በዙሪያው ከሚገኙ የማሌዥያ፣ ፊሊፒንስ፣ ታይዋን እና ቬትናም አገሮች ጋር  የይገባኛል ጥያቄ ያላት መሆኑ ተገልጿል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6841659.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6841659.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 19 Nov 2022 20:06:10 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/00d80000-0aff-0242-9405-08daca248138_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቨርጂኒያ ዩኒቨርስቲው ጥቃት ተጎጂ ቤተሰቦችና ተማሪዎች የመታሰቢያ ስርዓት አካሄዱ </title>
            <description>በዩናይትድ ስቴትስ ቨርጂኒያ ግዛት ውስጥ የሚገኘው የቨርጂኒያ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እና የማህበረሰቡ አባላት ባላፈው እሁድ ምሽት በጅምላ አጥቂ የተገደሉትን ሶስት የትምህርት ቤቱ እግር ኳስ ቡድን ተጫዋቾች ህልፈትን ለማሰብ ትናንት ሰኞ የሻማ ማብራት ስርዐት አከናውነዋል፡፡   


 

የጅምላ ተኩስ ጥቃት በማድረስ ሶስት ተማሪዎችን ገድሏል የተባለው አጥቂ ትናንት ሰኞ እስከተያዘበት ድረስ የትምህርት ቤቱ ጊቢ ተዘግቶ እንዲቆይ የተደረገ መሆኑ ተነግሯል፡፡ 




ተማሪዎችና የትምህርት ቤቱ ሰራተኞች በሶስቱ ተማሪዎች ሞት የተሰማቸውን ሀዘን እንዲገልጹ ሁሉም ትምህርትና ተያያዥ እንቅስቃሴዎች ዛሬ ማክሰኞ እንዲቋረጡ መደረጉም ተመልክቷል፡፡ 




ፖሊስ የቀድሞ የእግር ኳሱ ቡድን አባል የነበረው የ22 ዓመቱ ክሪስቶፈር ዳንኤል በግድያው ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር መዋሉን ያስታወቀ ሲሆን የጥቃቱ ምክንያት እስካሁን አልታወቀም፡፡ 


 

ጥቃቱ የተፈጸመው ባላፈው እሁድ ምሽት ዋሽንግተን ይካሄድ የነበረውን ጨዋታ ተመልክተው ወደ ትምህር ቤታቸው ይመለሱ የነበሩ የአሜሪካ እግር ኳስ ቡድን ተጫዋቾችን አሳፍሮ ከማቆሚያው ስፍራ በደረሰው አውቶብስ ላይ በተከፈተ የጅምላ ተኩስ  መሆኑ ተነግሯል፡፡ 


 

በጥቃቱ ሶስት ተማሪዎች ሲገደሉ በጽኑ ቆስሎ ሆስፒታል የሚገኘውን ጨምሮ ሌሎች ሁለት ሰዎች መቁሰላቸው ተመልክቷል፡፡ 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6837171.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6837171.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 15 Nov 2022 20:52:48 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/03220000-0aff-0242-1a36-08dac690e6f0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አሜሪካ፣ ደቡብ ኮሪያና ጃፓን፣ ሰሜን ኮሪያን በጋራ ለመመከት ተስማሙ </title>
            <description>ሰሜን ኮሪያ ሌላ የኑክሌር ሙከራ ለማድረግ በምትዘጋጅበት በዚህ ወቅት ዩናይትድ ስቴትስ፣ ደቡብ ኮሪያና ጃፓን ከሰሜን ኮሪያ በኩል የተደቀነውን አደጋ በጋራ ለመመከት ተስማምተዋል። 


የሶስቱ ሃገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ባላንጣቸው ላይ ለመተባበር የተስማሙት ዛሬ ቶኪዮ ላይ ባደርጉት ምክክር ነው። 


“ሰሜን ኮሪያ ሰባተኛውን የኑክሌር ሙከራ የምታደርግ ከሆነ፣ ጠንከር ያለ ምላሽ አስፈላጊ መሆኑን ተስማምተናል” ብለዋል የደቡብ ኮሪያው ምክትል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቾ ያን-ዶንግ። 


ሰሜን ኮሪያ በዚህ ዓመት በርካታ የኑክሌር ሙከራዎችን አድርጋለች። በዚህ ወር በጃፓን የአየር ላይ ያስወነጨፈችው ባሊስቲክ ሚሳዬል ተጠቃሽ ነው። 

የደቡብ ኮሪያው ፕሬዝደንት ዩን ሶክ ዮል ትናንት ማክሰኞ እንደተናገሩት ፒዮንግያንግ የኑክሌር ሙከራ ለማድረግ ዝግጅቷን አጠናቃለች። ይህም ከእ.አ.አ 2006 ወዲህ ሰባተኛው መሆኑ ነው። 



ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በፊት ጃፓን ደቡብ ኮሪያን ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ጠቅልላ መያዟን ተከትሉ በሁለቱ ሃገራት መካከል ፍቅር ባይኖርም፣ የሰሜን የጋራ ባላጣቸው የጦር መሣሪያ ሙከራ መቀጠል ሁለቱን ወገኖች ያቀራረበ ይመስላል። 


“የኑክሌር ሙከራን ጨምሮ ተጨማሪ ትንኮሳ ባለበት ሁኔታ፣ ቀጠናዊ የመከላከል ብቃታችንን ለማጠናከርና በዲፕሎማሲ ረገድ አብረን ለመሥራት ተስማምተናል” ሲሉ የጃፓኑ ምክትል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ተናግረዋል። 


የአሜሪካው ምክትል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ወንዲ ሸርማን፣ ሰሜን ኮሪያ ተጨማሪ ትንኮሳ ከማድረግ እንድትቆጠብና ዩናይትድ ስቴትስ አሁንም ካለቅድመ ሁኔታ ለመነጋገር እንደምትፈልግ አስታውቀዋል። 


የአሜሪካ፣ ደቡብ ኮሪያና ጃፓን የጦር መርከቦች ባለፈው ወር የባሊስቲክ ሚሳዬል መከላከል በተመለከተ ልምምድ አድርገዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6806499.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6806499.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 26 Oct 2022 20:26:58 +0300</pubDate>
            <category>ዓለምአቀፍ</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/14ba4a78-1de6-426e-82ff-03e347af2afe_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በዩክሬን ጥቅም ላይ ውለዋል የተባሉ የኢራን ድሮኖችን በተመለከተ እስራኤል ለአሜሪካ መረጃ ልትሰጥ ነው </title>
            <description>የእስራኤሉ ፕሬዝደንት አይሳክ ሄርዞግ በሩሲያ ጥቅም ላይ የዋሉትን የኢራን ድሮኖች በተመለከተ ሃገራቸው ያላትን መረጃ ዛሬ የአሜሪካውፕሬዝደንት ጆ ባይደንን ሲያገኙ እንደሚያካፍሏቸው አቅደዋል ተብሏል። 


የሄርዞግ ቢሮ እንዳለው በዩክሬን ጥቅም ላይ የዋሉትንና ባለፈው ዓመት በኢራን የተሞከሩትን ድሮኖች ተመሳሳይነት የሚያሳዩ ፎቶዎች እስራኤል አላት። 


ዩክሬንና የምዕራብ አጋሮቿ ሩሲያ የዩክሬን መዲና ኪቭን ጨምሮ ለመደብደብ የተጠቀመችባቸው ድሮኖች ኢራን ሠር የሆኑ ሻሂድ-213 የተባሉ ድሮኖች መሆናቸውን ሲናገሩ ሰንብተዋል። 


ኢራን ለሩሲያ ድሮኖቹን ማቀበሏን ትክዳለች፤ ሩሲያም ድሮኖቹን በዩክሬን ላይ መጠቀሟን እንዲሁ። 


ትናንት ማክሰኞ ጆ ባይደን ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ ለሩሲያ ልከዋል፤ በተለይም ደርቲ ቦምብ በሚባል የሚታወቀውን መሳሪያ ወይም ሌላ የኑክሌር መሣሪያ ሩስያ በዩክሬን ላይ የምትጠቀም ከሆነ።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6806487.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6806487.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 26 Oct 2022 20:21:48 +0300</pubDate>
            <category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/80470000-c0a8-0242-5d5f-08dab76af726_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሩሲያ ፍርድ ቤት የግራይነርን ይግባኝ ውድቅ አደረገ </title>
            <description>የሩሲያፍርድቤትካናቢስ የተሰኘውን አደገኛ ሱስ አስያዥ ዕጽ ይዛ ተገኝታለች በሚል 9 ዓመት እስራት የተፈረደባት፣ የዩናይትድ ስቴትስ ኮከብ የቅርጫት ኳስ ተጫዋች ብሪትኒ ግራይነር ያቀረበቸውን የይግባኝ ጥያቄ ዛሬ ማክሰኞ በሰጠው ውሳኔ ውድቅ አድርጓል፡፡ 


ግራነይር የተያዘቸው ባላፈው የካቲት በሞስኮ አውሮፕላን ማረፊያ በሩሲያ ክልክል የሆነውን በፈሳሽ መልክ የተዘጋጀውን የካናቢስ እጽ፣ ቬፕ በተባለው ማጨሺያ ውስጥ አድርጋ ተገኝታለች ተብላ እንደነበር ይታወሳል፡፡


አሜሪካውያን መራጮች በዚህ ወር መጨረሻ ለሚደረገው የአጋማሽ ምርጫ እየተዘጋጁ ሲሆን የሁለቱም ፓርቲ እጩዎች የመራጮችን ድምጽ ለማግኘት በቻይና ላይ ጥብቅና ጠንካራ ፖሊሲዎችን እንደሚያወጡ ቃል እየገቡ ነው፡፡ 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6805038.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6805038.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 25 Oct 2022 22:04:37 +0300</pubDate>
            <category>ዓለምአቀፍ</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01630000-0aff-0242-19cb-08da846d93db_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሪፐብሊካን ፓርቲ ጉጉልን ከሰሰ</title>
            <description>ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የሪፐብሊካን ፓርቲ ብሄራዊ ኮሚቴ ከጥቅምቱ የአጋማሽ ጊዜ ምርጫ በፊት የሚደረጉ የምርጫ ዘመቻዎችና የገቢ ማሰባሰቢያ ኢሜል ልውውጦችን እያፈነ ነው፥ ሲል በግዙፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ጉግል ላይ ክስ መስርቷል፡፡


ትናንት ዓርብ ካሊፎርኒያ ውስጥ የተመሰረተው ክስ ንብረትነቱ የጉጉል በሆነው የኤሜል መልዕክት መለዋወጫው ጂሜል አማካይነት ድርጅቱ በሪፐብሊካን ፓርቲ ላይ ፍትሃዊ ያልሆነና አድሏዊ ተጽእኖ ይፈጽማል ብሏል፡፡


በተለይም በምርጫ ወቅት ተለዋዋጭ ድጋፍ በመስጠት በሚታወቁት ወሳኝ ክፍለ ግዛቶች የሚገኙ መራጮች ላይ የሚደረገውን የገቢ ማሰባሰቢያ እና ወጥታችሁ ምረጡ የሚሉ ጥሪዎችን እንደ ብልሹ መልዕክቶች በመፈረጅ ወደ መጣያው ቅርጫት (ስፓም) ውስጥ በመክተት በፓርቲው የምርጫ ዘመቻ ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ነው ሲል ከሷል፡፡


የሪፐብሊካን ብሄራዊ ኮሚቴ ሌቀመንበር ሮና መክዳንኤል ለአሶሴይትድ ፕሬስ በላኩት መግለጫ “ከእንግዲህ ይበቃል ሪፐብሊካኖች ላይ እያሳየ ላለው ግልጽ አድልዎ ጉጉልን እየከሰሰን ነው” ማለታቸው ተዘግቧል፡፡


ጉግል ክሱን ያስተባበለ ሲሆን ፖለቲካዊ ወገንተኝነትን መሰረት በማድረግ የኢሜል ልውውጦችን አያጣራም ብሏል፡፡


የጉጉል ቃል አቀባይ የጄሜል ስፓሞች የሚያመልከቱት የተጠቃሚዎችን ምርጫና እርምጃ ነው ማለታቸውን የአሶሴይትድ ፕሬስ ዘገባ አመልክቷል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6801140.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6801140.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 22 Oct 2022 20:43:42 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/03990000-0aff-0242-098b-08dab4060a84_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሰሜን ኮሪያ በሌሊት ሚሳዬል ሞኮረች</title>
            <description>ሰሜን ኮሪያ ያታለመደ የምሽት ሚሳዬል ሙከራ ዛሬ አድርጋለች። ሙከራውን ያደረገችው በሠራተኞች  ፓርቲ ምሥረታ ዓመታዊ በዓል ዋዜማ እና የአሜሪካ አውሮፕላን ጫኝ መርከብ  ግብረሃይል የሁለት ሣምንት ወታደራዊ ልምምዱን ባጠናቀቀ ከሰዓታት በኋላ ነው።


አውሮፕላን ጫኝ መርከቡ ወደ ኮሬያ ባህረ ገብ ምድር ተመልሶ ያቀናው ሰሜን ኮሪያ መካከለኛ ርቀት ያለው ሚሳዬል በጃፓን አናት ላይ ማክሰኞ ዕለት ካስወነጨፈች በኋላ ነው።


ዛሬ እሁድ በውድቅት ሌሊት ሁለት የአጭር ርቀት ሚሳዬሎች  ሙንቾን ተብሎ ከሚጠራው ቦታ፣ ወደ “ምሥራቅ ባህር” ወይም የ”ጃፓን ባህር” ተብሎ ወደሚጠራው የውሃ አካል ተወንጭፈዋል ሲል የደቡብ ኮሪያ ሠራዊት አስታውቋል። የጃፓኑ ተቀዳሚ ምክትል መከላከያ ምኒስትር ቶሺሮ ኢኖ ይህንኑ አረጋግጠው፣ የ”ጃፓን የተለየ የኢኮኖሚ ቀጠና” ተብሎ ከሚጠራው ክልል ወጣ ብሎ ባለ የውሃ አካላ ላይ ማረፉን አስታውቀዋል።


የቪኦኤዋ ዩኒስ ኪም ከሶል እንደዘገበችው፣ የዩናይትድ ስቴትስ ኢንዶ ፓሲፊክ  የተባለው ወታደራዊ ዕዝ ሁኔታውን ከገመገመ በኋላ “የሚሳዬል ሙከራው በአሜሪካም ሆነ በአጋሮቿ ላይ የፈጠረው ስጋት የለም፤ ዩናይትድ ስቴትስ ደቡብ ኮሪያንና ጃፓንን እንደምትከላከል በድጋሚ እናረጋግጣለን” ብሏል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6782575.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6782575.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 09 Oct 2022 23:50:59 +0300</pubDate>
            <category>ዓለምአቀፍ</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/03990000-0aff-0242-38f6-08daa96a42b0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዩናይትድ ስቴትስ የነዳጅ ዋጋ እንዳይጨምር እርምጃዎችዋን እያጤነች ነው</title>
            <description>ዩናይትድ ስቴትስ የነዳጅ ዘይት አምራችና ላኪ አገሮች ምርቶቻቸውን ለመቀነስ መወሰናቸውን ተከትሎ በዓለም የነዳጅ ዘይት ዋጋ እንዳይጨምር ለመከላከል ተከታታይ እርምጃዎችን እያጤነች መሆኑ ተገለጸ፡፡  


ሩሲያን ጨምሮ ሌሎች አጋሮቹን ያካተተው የነዳጅ አምራችና ላኪ አገሮች ማህበራት (ኦፔክ) በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ የነዳጅ ዘይት ምርትን ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ በቀን በ2 ሚሊዮን በርሜል እንደሚቀንስ በመግለጹ ገበያው ላይ ስጋት መፍጠሩ ተነግሯል፡፡


የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በቡድኑ ውሳኔ ቅር መሰኘታቸውን ገልጸዋል፡፡


ውሳኔውንም  አርቆ ተመልካችነት የጎደለው “የአጭር ጊዜ እይታ ነው” ብለውታል፡፡


ዋሽንግተን እውቅና ከነፈገችው የቬንዙዌላ አምባገነን ሶሻሊስት መንግሥት ጋር አስተዳደራቸው ሊገናኝ ይችላል የሚሉ ዘገባዎችንም ባይደን “ምን ዓይነት አማራጮች ሊኖረን እንደሚችል እየተመለከትን ነው”ባሉበት ንግግራቸው ያረጋገጡት መምሰሉ ተነግሯል፡፡


ባለሙያዎች የነዳጅ ዘይት ምርቶቻቸውን ወደ ውጭ እንዳይልኩ እንደ ቬንዙዌላና ኢራን በመሳሰሉ አገሮች ላይ የተጣለውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ ማንሳት ተጨማሪ የነዳጅ ምርት ወደ ገበያው እንዲመጣ ያስችላል ይላሉ፡፡


ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ በሚቀጥለው ወር ህዳር በሚደረገው ምርጫ፣ ምክር ቤቶቹን መቆጣጠር ለሚፈልጉት የፕሬዚዳንቱ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ተፎካካሪዎች የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው ጥሩ ዜና ሊሆን እንደማይችል ተመልክቷል፡፡

 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6781404.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6781404.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 08 Oct 2022 14:18:27 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/03990000-0aff-0242-3d01-08daa8cd5199_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አሜሪካ አጋሮቿን ከሰሜን ኮሪያ ጥቃት እንደምትከላከል በድጋሚ አስታወቀች</title>
            <description>ሰሜን ኮሪያ መካከለኛ ርቀት ባሊስቲክ ሚሳዬል ትናንት በጃፓን አናት ላይ ማስፈንጠሯን ዩናይትድ ስቴትስ አውግዛ፣ አጋሮቿ የሆኑትን ደቡብ ኮሪያንና ጃፓንን እንደምትከላከል ቃል ገብታለች። ይህም ሆኖ የባይደን አስተዳደር ከፒዮንግያንግ ጋር ለመነጋገር አሁንም በሩ ክፍት መሆኑን አስታውቋል።


ለሰሜን ኮሪያ ሚሳዬል ተኩስ ምላሽ፣ የአሜሪካና የደቡብ ኮሪያ የአየር ሃይል አውሮፕላኖች ትናንት ማክሰኞ የጋራ ልምምድ ማድረጋቸውን የዋይት ሃውስ ቃል አቀባይ ካሪን ዣን-ፒየር አረጋግጠዋል።


“በጋራ የመከላከል ብቃታችንንና፣ በቅጽበት ተለዋዋጭ የሆነ ጥቃት የማድረስ አቅማችንን ለማሳየት፤ በሁለትዮሽም ሆነ በሶስትዮሽ በምናደርገው ግኑኝነት እንዲሁም ከኮሪያ ሪፐብሊክና ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር በመሆን አስቸኳይና ዘላቂ መፍትሄ የምንሰጥበትን ሁኔታ ማቀናጀታችንን እንቀጥላለን” ብለዋል ዣን-ፒየር።


ሰሜን ኮሪያ ትናንት በጃፓን አናት ላይ ያስወነጨፈችው መካከለኛ ርቀት ባሊስቲክ ሚሳዬል በቅርቡ በወታደራዊ ሰልፍ ላይ ያሳየችውና፣ አዲስ ዓይነት ሊሆን እንደሚችል ታምኗል።


ከሌሎቹ ሚሳዬሎች በበለጠ 4ሺህ 600 ርቀት መጓዝ ሲችል፣ ወደ ሰማይ በመተኮስ ፈንታ፣ ወደ ጎን በጃፓን እናት ላይ አስፈንጥራዋለች ሰሜን ኮሪያ። ከ2017 ወዲህ ወደ ጃፓን አቅጣጫ ሲተኮስ የመጀመሪያው ነው።


የጃፓኑ ጠቅላይ ምኒስትር ፉሚዮ ኪሺዳ “በቅርቡ መልስ እንሰጥበታለን” ሲሉ ዝተዋል።


ታዛቢዎች እንደሚሉት ሰሜን ኮሪያ ሙከራውን ያደረገችው፣ በአሜሪካና በደቡብ ኮሪያ መካከል ከፍተኛ የባህር ላይ የጋራ ልምምድ ለማድረጋቸው መልስ ነው። ሃይልን ለመፈታተሸ ይመስላል፣ ዩ.ኤስ.ኤስ. ሮናልድ ሬገን የተሰኘው የአሜሪካው አውሮፕላን ጫኝ መርከብ ባለፈው ወር ወደ ደቡብ ኮሪያ ተጠግቶ ቆሟል።


የባይደን አስተዳድር አጋሮችን እንደሚከላከል ቢያሳውቅም፣ ከፒዮንግያንግ ጋር ለመነጋገር አሁንም በሩ ክፍት ነው ብሏል።


“ዓላማችን አሁንም የኮሪያን ባህረ-ገብ ምድር ከኑክሌር ነጻ ማድረግ ነው። ለዚህም ተጨባጭ እመርታ ላማሳየት፣ ቀጣይነት ያለውና እውነተኛ የሆነ የዲፕሎማሲ ድርድር ለማድረግ አሁንም ዝግጁ ነን። ከሰሜን ኮሪያ ጋር ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ለመገናኘት ሁሌም ዝግጁ ነን” ሲሉ ተናግረዋል ዣን ፒየር።


በተመድ የአሜሪካ አምባሳደር፣ የጸጥታ ም/ቤቱ ፒዮንግያንግ ጅምላ ጨራሽ መሣሪያ ማምረቷን ለመግታት ስብሰባ እንዲደረግ ጠይቀዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6777603.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6777603.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 06 Oct 2022 01:03:15 +0300</pubDate>
            <category>ዓለምአቀፍ</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><author> voadigital@voanews.com (እንግዱ ወልዴ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/80470000-c0a8-0242-1c89-08daa6b52475_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዩናይትድ ስቴትስ በሩሲያውያን ላይ ተጨማሪ እገዳ ጣለች</title>
            <description>የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን አራት የዩክሬን ግዛቶችን ገንጥለው ከጠቀለሉ በኋላ፣ የባይደን አስተዳዳር ፑቲንን በሚደግፉና፣ በሩሲያ ውስጥም ሆነ ውጭ በሚገኙ ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ ትናንት አዲስ ማዕቀብ ጥሏል።


በአሜሪካ የሚገኝ ንብረትና ገንዘብ ላይ፣ እንዲሁም የቪዛ ማዕቀብ በመቶ በሚቆጠሩ የሩሲያ ድርጅቶች፣ የሃገሪቱ ባለስልጣናትና ቤተሰቦች ላይ ሲጣል፤ ለውጪ ገበያ በሚልኩት ምርት ላይም እገዳ መደረጉን የቪኦኤዋ ፓትሲ ዊዳኩስዋራ ከዋይት ሃውስ ዘግባለች።


ለሩሲያ መሳሪያ የሚያቀርቡና፣ አቅርቦቱን የሚያቀላጥፉ 14 የሚሆኑ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችም በማዕቀቡ ተመተዋል። ይህም የሩሲያን ጦር መልሶ የማገገም ብቃት ይጎዳል ተብሏል።


አራት የዩክሬን ግዛቶች ወደ ሩሲያ በመጠቃለላቸው የፑቲን ደጋፊዎች  ደስታቸውን ለመግልጽ ትናንት በቀዩ አደባባይ ተሰባስበው ታይተዋል።


ባሳለፍነው ሳምንት በጥድፊያ የተፈጸመውን ህዝበ ውሳኔ ዩክሬንና የምዕራቡ ዓለም ውድቅ አድርገውታል። ግዛቶቹ ወደ ሩሲያ መጠቃለላቸውን በማስመልከት በተደረገ የፊርማ ሥነ ስራት ላይ ፑቲን እንዳሉት፣ አንድ አምስተኛውን የዩክሬን ግዛት በሚያክሉት በአራቱ ክልሉች፤ ማለትም ሉሃንስክ፣ ዶነትስክ፣ ኬርሶን እና ዛፖሪዤዢያ የሚገኙ ሕዝቦች “እስከወዲያኛው ዜጎቻችን ሆነዋል” ብለዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6771904.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6771904.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 02 Oct 2022 01:14:14 +0300</pubDate>
            <category>ዓለምአቀፍ</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><author> voadigital@voanews.com (እንግዱ ወልዴ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/80470000-c0a8-0242-4c11-08daa338a2b3_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሰሜን ኮሪያ ተጨማሪ ሚሳይሎች አስወነጨፈች</title>
            <description>ሰሜን ኮሪያ ዛሬ ቅዳሜ ሁለት ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ወደ ባህር አስወንጭፋለች። የአሜሪካ ባላንጣዋ ሰሜን ኮሪያ በያዝነው ዓመት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሚሳኤል አስወንጭፋለች። በዚህ ሳምንት ብቻ ሰባት መሆኑ ነው።


የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዝደንት ካመላ ሃሪስ ባለፈው ሳምንት ጉብኝት ከማድረጋቸው ጥቂት ቀደም ብሉም እንድ ሚሳኤል ለቃለች ሰሜን ኮሪያ። ካመላ ሃሪስ “ግልጽ ጸብ አጫሪነት ነው” ብለውታል።


በሁለቱ ኮሪያዎች መካከል የሚገኘውንና ከወታደራዊ ሃይል ነጻ የሆነውን ቀጠና በጎበኙበት ወቅት፣ ሰሜን ኮሪያን “ጨካኝ ፈላጭ ቆራጭ” ገልጸዋታል ካመላ ሃሪስ።


ቶኪዮ ላይ ዛሬ የተናገሩት የጃፓን ምክትል የመከላከያ ምኒስትር ቶሺሮ ኢኖ፣ የሰሜን ኮሪያን ድርጊት በጽኑ አውግዘዋል። “የጃፓንን ብቻ ሳይሆን፣ የቀጠናውንና የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ የሚያሰጋ ድርጊት ነው” ብለውታል።


ከያዝነው የፈረንጆት ዓመት ጅምሮ ሰሜን ኮሪያ 38 ባሊስቲክ ሚሴሎችን አስወንጭፋለች።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6771901.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6771901.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 02 Oct 2022 01:12:18 +0300</pubDate>
            <category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (እንግዱ ወልዴ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/013b0000-0aff-0242-bb8a-08daa3491488_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዩናይትድ ስቴትስ በሩሲያውያን ላይ ተጨማሪ እገዳ ጣለች</title>
            <description>የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን አራት የዩክሬን ግዛቶችን ገንጥለው ከጠቀለሉ በኋላ፣ የባይደን አስተዳዳር ፑቲንን በሚደግፉና፣ በሩሲያ ውስጥም ሆነ ውጭ በሚገኙ ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ ትናንት አዲስ ማዕቀብ ጥሏል።


በአሜሪካ የሚገኝ ንብረትና ገንዘብ ላይ፣ እንዲሁም የቪዛ ማዕቀብ በመቶ በሚቆጠሩ የሩሲያ ድርጅቶች፣ የሃገሪቱ ባለስልጣናትና ቤተሰቦች ላይ ሲጣል፤ ለውጪ ገበያ በሚልኩት ምርት ላይም እገዳ መደረጉን የቪኦኤዋ ፓትሲ ዊዳኩስዋራ ከዋይት ሃውስ ዘግባለች።


ለሩሲያ መሳሪያ የሚያቀርቡና፣ አቅርቦቱን የሚያቀላጥፉ 14 የሚሆኑ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችም በማዕቀቡ ተመተዋል። ይህም የሩሲያን ጦር መልሶ የማገገም ብቃት ይጎዳል ተብሏል።


አራት የዩክሬን ግዛቶች ወደ ሩሲያ በመጠቃለላቸው የፑቲን ደጋፊዎች  ደስታቸውን ለመግልጽ ትናንት በቀዩ አደባባይ ተሰባስበው ታይተዋል።


ባሳለፍነው ሳምንት በጥድፊያ የተፈጸመውን ህዝበ ውሳኔ ዩክሬንና የምዕራቡ ዓለም ውድቅ አድርገውታል። ግዛቶቹ ወደ ሩሲያ መጠቃለላቸውን በማስመልከት በተደረገ የፊርማ ሥነ ስራት ላይ ፑቲን እንዳሉት፣ አንድ አምስተኛውን የዩክሬን ግዛት በሚያክሉት በአራቱ ክልሉች፤ ማለትም ሉሃንስክ፣ ዶነትስክ፣ ኬርሶን እና ዛፖሪዤዢያ የሚገኙ ሕዝቦች “እስከወዲያኛው ዜጎቻችን ሆነዋል” ብለዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6771898.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6771898.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 02 Oct 2022 01:04:26 +0300</pubDate>
            <category>ዓለምአቀፍ</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><author> voadigital@voanews.com (እንግዱ ወልዴ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/80470000-c0a8-0242-4c11-08daa338a2b3_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ባይደን ለንግስቲቱ ቀብር ለንደን ገብተዋል</title>
            <description>በመቶ የሚቆጠሩ የዓለም መሪዎች በነገው ዕለት በሚፈጸመው የእንግሊዟ ንግስት ዳግማዊት ኤልሳቤጥ የቀብር ስነ ሥርዓት ላይ ለመገኘነት ለንደን ላይ ተሰባስበዋል።


የአሜሪካው ፕሬዝደንት ጆ ባይደንና ባለቤታቸው ጅል ባይደን ትናንት ቅዳሜ ለንደን መግባታቸው ታውቋል።


የቪኦኤዋ አኒታ ፓወል ከለንደን እንደዘገበቸው፣ በማዕከላዊ ለንደን በርካቶች ሲሰባሰቡ፣ የዓለም መሪዎች ደግሞ ላንካስተር ሃውስ ወደተባለው የውጪ ጉዳይና የጋራ ብልጽግና ቢሮ አምርተው ከሳምንት በፊት በ96 ዓመታቸው ህይወታቸው ላለፈው ዳግማዊት ኤልሳቤጥ ሃዘናቸውን ገልጸዋል።


ባይደንና ባለቤታቸው  በዌስትሚኒስተር አዳራሽ በመገኘት ካለፈው ረቡዕ ጀምሮ በክብር ያረፈውን የንግስቲቱን አስከሬን የተመለከቱ ሲሆን፣ ንጉስ ቻርለስ ሶስተኛ ለእንግዶቻቸው የአቀባበል ስነ ሥርዓት እንደሚያደርጉም የጠበቃል።


የእንግሊዝ ዘውድ፣ በንግስቲቱ የቀብር ስነ ሥር ዓት ላይ እንዲገኙ ለሳውዲ አረቢያው አልጋ ወራሽ ሞሃመድ ቢን ሳልማን ጥሪ በማድረጉ ጭቅጭቅን ፈጥሯል። አልጋ ወራሹ ጋዜጠኛ ጅማል ካሾግጂን ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ አስገድለዋል የሚል ውንጀላ ይቀርብባቸዋል። ዘግይቶ በወጣ ሪፖርት ደግሞ ንጉሱ በቀብር ስነ ሥርዓቱ ላይ እንደማይገኙ ታውቋል።


የእንግሊዝ ዘውድ፣ የሩሲያ፣ ቤላሩስ፣ ሲሪያ፣ አፍጋኒስታን እና ቬንዝዌላን መሪዎች በቀብሩ ላይ እንዲገኙ አልጋበዘም።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6752557.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6752557.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 18 Sep 2022 21:20:45 +0300</pubDate>
            <category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (እንግዱ ወልዴ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/095c0000-0a00-0242-29a4-08da9990370e_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ፐሎሲ አዘርባጃን በአርሜኒያ ላይ የፈጸመችውን ጥቃት አወገዙ</title>
            <description>አርሜኒያን በመጎብኘት ላይ የሚገኙት የአሜሪካው ም/ቤት  አፈ ጉባኤ  ናኒሲ ፐሎሲ በቅርቡ አርሜኒያ ላይ በአዘርባጃን  የተፈጸመውን ጥቃት አውግዘዋል።


ጥቃቱንም “ሕገ ወጥና አደገኛ” ሲሉ ጠርተውታል።


በአርሜኒያ መዲና የረቫን ላይ የተናገሩት ፐሎሲ፣ አሜሪካ የአርሜኒያን ሉአላዊነት እንደምትደግፍና ሃገሪቱ ራሷን ለመከላከል የሚያስፈልጋትን ነገር አሜሪካ ማወቅ ትሻለች ብለዋል።


ፐሎሲ አያይዘውም፣ ጥቃቱ የተጀመረው በአዘርባጃን ወገን መሆኑ መታወቅ አልበት ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።


“አርሜኒያ ላይ በአዘርባጃን የተፈጸመው ጥቃት በዲሞክራሲና በፈላጭ ቆራጭ አገዛዞች መካከል በመላው ዓለም የሚደረገው ትግል አካል ነው” ብለዋል ፐሎሲ።


የአዘርባጃን ሃይሎች ጀርሙክ የተባለውን የሽርሽር ከተማ በሰው አልባ አውሮፕላንና በሞርታር ደብድበዋል ሲል የአርሜኒያ መከላከያ ምኒስቴር ባለፈው ረቡዕ አስታውቆ ነበር።


የአዘርባጃን መከላከያ ሠራዊት በበኩሉ የአርሜንያ ሃይሎች ይዞታዎቼን ደብድበውብኛል በማለት መልሶ ወነጅሏል።


አርሜኒያ 49 ወታደሮቿ እንደተገደሉባት ስታስታውቅ፣ አዘርባጃን ደግሞ 50 ሞተውብኛል ብላለች።


የሶቪየት ሶሻሊስት ሪፐብሊክ አካል የነበሩት ሁለቱ ሃገሮች ናጎርኖ ካራባክ በተባለው ክልል ይገባኛል ጥያቄ ለዓመታት ተዋግተዋል።


በእ.አ.አ. 1994 የአርሜኒያ ሃይሎች ናጎርኖ ካራባክን በቁጥጥር ሥር አውልውት የነበር ቢሆንም፣ ከሁለት ዓመት በፊት በተደረገ የስድስት ቀናት ጦርነት አዘርባጃን ሰፊ አካባቢን ተቆጣጥራለች።


ሩሲያ አስታራቂ ሆና ጣልቃ በመግባት ሁለቱ ወገኖች የሰላም ስምምነት አድርገው እንደነበር ይታወሳል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6752536.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6752536.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 18 Sep 2022 20:57:21 +0300</pubDate>
            <category>ዓለምአቀፍ</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (እንግዱ ወልዴ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/7463787a-e8c2-4591-aa39-7b6bfcdca516_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኦባማ ኤሚ አሸነፉ</title>
            <description>የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ትናንት ማታ የኤሚ ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል::


ኦባማ ሽልማቱን ያሸነፉት “ታላላቆቹ ብሄራዊ ፓርኮቻችን” በሚል ርዕስ በኔትፍሊክስ የተዘጋጀውን ዘጋቢ ፊልም በመተረካቸውና “ምርጥ ተራኪ” በሚል የሽልማት ምድብ አሸናፊ በመሆናቸው ነው።


የቀድሞው ፕሬዝደንት ከዚህ በፊት ሁለት መጽሕፍትን በትረካ በማቅረባቸው ሁለት የግራሚ ሽልማት አሸናፊ ሆነው ነበር።


በአምስት ክፍል የቀረበው ዘጋቢ ፊልም በዓለም ዙሪያ ያሉ ብሄራዊ ፓርኮችን የሚያሳይ ሲሆን፣ የተዘጋጀውም “ሃየር ግራውንድ” በተሰኘው የኦባማና ባለቤታቸው ሚሸል የፊልም ኩባንያ ነው።


ኦባማ የኤሚ ሽልማትን ያሸነፉ ሁለተኛው ፕሬዝደንት ናቸው።


የቀድሞ ፕሬዝደንት ድዋይት አይዘንሀወር በ1956 ልዩ የኤሚ ሽልማት አግኝተው ነበር።


ኦባማ ከዚህ በፊት “The Audacity of Hope” እና “A Promised Land” የተሰኙ መጻሕፍት በድምጽ አቅርበው የ“ምርጥ ተራኪ” ሁለት የግራሚ ሽልማቶችን ወስደዋል።


ባለቤታቸው ሚሸል ኦባማ መጽሐፋቸውን በድምጽ አቅርበው፣ ከሁለት ዓመት በፊት የግራሚ ሽልማት መውሰዳቸውን የአሶስዬትድ ፕረስ ዘገባ አስታውሷል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6730642.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6730642.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 04 Sep 2022 20:45:09 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (እንግዱ ወልዴ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/b4f8d650-f1d3-48d5-a017-b04066a3a335_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በስለት በመወጋቱ ከፍተኛ ጥቃት የደረሰበት ሳልማን ሩሽዲ ሆስፒታል ገባ</title>
            <description>ኒው ዮርክ — ሳልማን ሩሽዲ በትላንትናው ዕለት ምእራብ ኒውዮርክ ውስጥ በተዘጋጀ አንድ ሥነ ስርአት ላይ ሊናገር ሲል በተሰነዘረበት ጥቃት ከባድ ጉዳት ከደረሰበት በኋላ በዛሬው ዕለት ሆስፒታል ገባ።


የሩሽዲ ወኪል ሲናገሩ: የ75 ዓመት ዕድሜው ደራሲ “ጉበቱ ተጎድቷል፣ የእጅ ነርቮቹ ተቆርጠዋል፤ እናም ብርሃኑን ሊያሳጣው በሚችል አደጋ ዓይኑ ላይ ጉዳት ደርሶበታል። የሚተነፍሰውም በመሳሪያ እገዛ ነው።” ብሏል።


ሩሽዲ “ሰይጣናዊ ጥቅሶች” በሚል ርዕስ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1980ዎቹ የደረሰው ልቦለድ መድብል የኢራኑን መሪ የግድያ ዛቻ ማስከተሉ ይታወሳል። ሩሽዲ ላይ ጥቃቱን ያደረሰው ሰው ፖሊስ በቁጥጥር ስር ያዋለው የፌርቪው ኒውጀርሲ ነዋሪ የሆነው የ24 ዓመቱ ሃዲ ማታር መሆኑን ታውቋል። የማታር ጠበቃ ግን አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል። ፖሊስ በሩሽዲ ላይ ለደረሰው ጥቃት መንስኤው ምን ስለመሆኑ እስካሁን ግልፅ አይደለም ብሏል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/salman-rushdie-in-hospital-police-seek-motive-in-stabbing/6700811.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/salman-rushdie-in-hospital-police-seek-motive-in-stabbing/6700811.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 14 Aug 2022 04:44:58 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/84c00d53-4f2a-4f81-8477-5cac8def6da8_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በዩናትይትድ ስቴትስ የዝንጅሮ ፈንጣጣ ክትባት በአነስተኛ መጠን ይሰጣል </title>
            <description>የዩናይትድስቴትስ የጤና ባለሥልጣናት የዝንጀሮ ፈንጣጣን (መንኪፖክስ) ክትባት ለማዳረስ የወጣውን እቅድ አጽድቀዋል፡፡  


የዩናይትድ ስቴትስ የምግብና የመድሃኒት አስተዳደር ትናንት ባወጣው መግለጫ በአገሪቱ የተፈጠረውን የክትባቱን እጥረት በማየት ከዚህ በፊት ለእያንዳንዱ ሰው ይሰጥ ከነበረው ክትባት አሁን አንድ አምስተኛው እጅ ብቻ እንዲሰጥ ፈቃድ መስጠቱ ተመልክቷል፡፡ 


ትናንት የወጣው የጤና ባለሥልጣናቱ መግለጫ፣ በአነስተኛ መጠን ተቀንሶ የሚሰጠው ክትባት ከሙሉው ክትባት እኩል ውጤታማ መሆኑን አስታውቋል፡፡  


የዋይት ሀውስ ባለሥልጣናት አዲሱ ፖሊሲ አሁን ያለውን 444ሺ የክትባት መድሃኒት መጠን ወደ 2 ሚሊዮን ጥቃቅን የክትባት መድሃኒቶች እንደሚያበዛቸው ተናግረዋል፡፡  


አንዳንድ የጤና ባለሙያዎች ስለ ውጤታማነቱ በበቂ መረጃ ላይ የተደገፈ ጥናት ባለመደረጉ፣ የክትባቱን መጠን መቀነስ ተቃራኒ ውጤት ሊያመጣ ይችላል ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡ 


እስካሁን ወደ 625ሺ ሙሉ የክትባት መድሃኒቶችን በየክፍለግዛቱ ማሰራጨታቸውንም ባለሥልጣናቱ አመልከተዋል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6695871.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6695871.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 10 Aug 2022 17:10:52 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01a10000-0aff-0242-b76c-08da7a5dfbff_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አሜሪካ ቻይና በታይዋን ዙሪያ የምታደርገው ወታደራዊ ልምምድ አደገኛ ነው አለች</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴስ ምክር ቤት አፈጉባኤ ናንሲ ፐሎሲ በታይዋን ጉብኝት ማድረጋቸው እጅግ ያበሳጫት ቻይና ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በወታደራዊ ግንኙነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና በሌሎች ጉዳዮች የምታደርገውን ውይይት ማቋረጧን አስታውቃለች።


የቻይና ጠቅላይ ሚኒስቴር ዋንግ ዪ ጉዳዩን አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር &quot;የአሜሪካ ምክርቤት አፈጉባኤ፣ ቻይና በተደጋጋሚ ያሰማችውን ተቃውሞ እና ተደጋጋሚ ድርድር ችላ ብለዋል። ጉዞዋ የተመቻቸውም በዩናይትድ ስቴትስ መንግስት ነው&quot; ብለዋል።


የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ የምስሉን ትክክለኛነት ማጣራት ባይችልም፣ የቻይና ቴሌቭዥን ጣቢያ ቤይጂንግ በታይዋን አቅራቢያ ወታደራዊ ልምምድ ስታደርግና ስትተኩስ የሚያሳዩ ምስሎችን አሳይቷል። ከዚህ በፊት ባልታየ መጠን የሚካሄደው ይህ ልምምድም ዓለም አቀፍ ፍርሃት እና ውግዘት እያስከተለ ነው። 


የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አንተኒ ብሊንከን በካምቦዲያ ጉዞ ባደረጉበት ወቅት ከአሜሪካ ድምፅ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ &quot;የቻይና ምላሽ ያልተመጣጠነ እና አደገኛ ነው&quot; ያሉ ሲሆን ጉዞው ምንም አይነት ስሜት ቢፈጥርባት 11 ተወንጫፊ ሚሳይሎችን በታይዋን ዙሪያ መተኮስ፣ መርከቦችን በታይዋን ዙሪያ ማሰማራት ትክክል አለመሆኑንና ከሚሳይሎቹ አምስቱ ጃፓን አቅራቢያ መውደቃቸውን ገልፀዋል። 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6689757.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6689757.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 06 Aug 2022 19:23:11 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/09680000-0a00-0242-56cb-08da76ebe526_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ባይደን ለባህር ኃይል አካዳሚ ምሩቃን ስለ ሩሲያና ቻይና ተናገሩ</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ነጻው ማህበረሰብ ከሩሲያና ከቻይና አደጋ የተደቀነበት በመሆኑ “እናንተ የዲፕሎማሲ ተከላካይና ወኪሎች ናችሁ” ሲሉ ትናንት ዓርብ ለተመረቁት የባህር ኃይል አባላት ተናገሩ፡፡


ሜሪላንድ አናፖልስ በሚገኘው የባህር ኃይል አካዳሚ ተገኝተው 1ሺ ለሚደርሱ ምሩቃን ንግግር ያሰሙት ባይደን የሩሲያን ወረራና የቻይናን የባህር ላይ መስፋፋት አንስተዋል፡፡ 


“ዓለም በመልክአ ምድር (ጂኦግራፊ) ብቻ ሳይሆን፣ በጋራ እሴቶችም የሚተባበር መሆኑን በሩሲያው ወረራ አሳይቷል” ያሉት ባይደን፣ እናንተም “የአውሮፓና የኢንዶ ፓስፊክ አጋሮቻችንን ታግዛላችሁ” ብለዋል፡፡


የቻይና ደቡባዊ ባህርና ከዚያም ባሻገር ያሉትን ዓለም አቀፍ የባህር ላይ መስመሮች ወይም የመጓጓዣ መንገዶች ፣ ለዓለም አቀፉ ስርዐት መከበርም ሆነ ምጣኔ ሀብት ቁልፍ በመሆናቸው እነሱን መጠበቅ ኃላፊነታቸው መሆኑንም ባይደን ለምሩቃኑ ገልጸዋል፡፡


ባይደን በዛሬው እለትም በደለዌር ዩኒቨርስቲ በሚካሄደው የተማሪዎች ምርቃት ስነ ስር ዓት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡ 


ፕሬዘዳንቱ 19 ህጻናት በተገደሉበት የቴክሳሱ የትምህር ቤት ጥቃት፣ ልጆቻቸው የሞቱባቸውን ወላጆች ለማነጋገር ነገ እሁድ ወደ ዩቫልዲ እንደሚያቀኑም ተነግሯል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6593447.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6593447.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 28 May 2022 16:57:19 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/2cbe329e-0554-42d3-a566-90f03b851a90_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአሜሪካ ትልቁ የመሳሪያ ማህበር ጉባኤውን በቴክሳስ አካሄደ</title>
            <description>በአሜሪካ ትልቁ የመሳሪያ ሽያጭ ጠበቃና ተሟጋች የሆነው ብሄራዊ የመሳሪያ ማህበር ትናንት ቴክሳስ ውስጥ ዓመታዊ ጉባኤውን አካሂዷል፡፡ 


19 ህጻናት ከተገደሉበት የቴክሳሱ  ዩቫልዲ ትምህር ቤት 500 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ስፍራ በተካሄደው ጉባኤና የመሳሪያ ሽያጭ ትርኢት ላይ ለመካፈል ከ50ሺ በላይ የማህበሩ አባላት መመዝገባቸውን ማህበሩ አስታውቋል፡፡


ዝግጅቱን ለሌላ ጊዜ እንዲያስተላልፈው ተጠይቆ የነበረው ብሄራዊ የመሳሪያዎች ማህበር ሥራ አስፈጻሚ ዊይን ላፒየር እያንዳንዱ የማህበሩ አባል በጉዳዩ ማዘኑን ገልጸዋል፡፡ 


“እኛ ከዚህ ማህበረሰብና ከመላው አሜሪካውያን ጋር በጸሎት እንገኛለን፣ እኛም ወንድ ልጆች ሴት ልጆችና የምናወዳቸው ልጆች አሉን፡፡ ይህ አሳዛኝ ድርጊት አሁን ብዙዎች እያለፉበት እንዳለው አንጀት የሚነካ የማይገመት ህመም የሚፈጥር ነገር ነው” ብለዋል፡፡  


ግድያውን ተከትሎ ፕሬዘዳንት ባይደን ባሰሙት ንግግር “መሳሪያ ሻጮች ሁለት አስርት ዓመታት ሙሉ ትልቁን ትርፍ የሚያጋብሱበትን የማጥቂያ መሳሪያዎችን ሲያሻሽጡ ኖረዋል ይህን ኢንደስትሪ ማቆም የምንችልበት አቅም ሊኖረን ይገባል” በማለት የመሳሪያ ህግ በአስቸኳይ እንዲወጣ ጠይቀዋል፡፡


በመሳሪያ ማህበሩ ጉባኤ ላይ ንግግራቸው የተሰማው የቀደሞ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ “ይህ ዓይነቱ ንግግር ከፋፋይና አደገኛ ነው ከሁሉም በላይ ደግሞ ስህተት ነው በፖለቲካችን ውስጥ ስፍራ አይኖረውም” ብለዋል፡፡ 


ትራምፕ አያይዘውም “ እንደሁልጊዜውም እንዲህ አሳዛኝ ነገር በተከሰተ ማግስት በግራ ፖለቲከኞች የመሳሪያ ቁጥጥር ፖሊሲ ይደረጋል፣ እስካሁን በግራው ግፊት የወጡ ፖሊሲዎች አሰቃቂውን ነገር እንዳይደርስ በተከላከሉ ነበር&quot; በማለት ተናግረዋል፡፡


የሂውስተን ከተማ የሰላምና ፍትህ ማዕከል ፕሬዚዳንት ቢል ክሮሲየር በሰጡት አስተያየት


“ከተማችንን ለእነዚህ ለመሳሪያ አምራቾችና ለኛ ለመራጮች ሳይሆን ለነሱ ለቆሙ ፖለቲከኞች ክፍት በማድረጋችን የተሰደብኩ ያህል ይሰማኛል” ብለዋል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6593443.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6593443.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 28 May 2022 16:49:21 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><enclosure url="https://gdb.voanews.com/03180000-0aff-0242-998e-08da3f7610cc_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>