<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>ዩናይትድ ስቴትስ - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/3177</link>
        <description>americana</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>ዩናይትድ ስቴትስ - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/3177</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2021 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Sat, 15 May 2021 12:06:43 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zirjrejtjr" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>ራሽያ ስለ አሜሪካው የጋዝ ማስተላለፊያ ጥቃት አስተባበለች</title>
            <description>ራሽያ ከፊል የዩናይትድ ስቴትስ ምስራቃዊ ግዛትን የሚሸፍነውን የኮሎንያል የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመርን፣ በማሽመደመድ ፈጽማዋለች የተባለውን የሳይበር ጥቃት ክስ አስተባብላለች፡፡ የባይደን አስተዳደር የተፈጠረውን የነዳጅ እጥረት ለመለካለከል እምርጃዎችን እየወሰደ ሲሆን፣ አሸከርካሪዎችም በነዳጅ ዋጋ ላይ የተደረገውን ጭማሪ መመልከት ጀምረዋል፡፡


ባለሥልጣናቱ ይህን ችግር ተከትሎ የተፈጠረውን የነዳጅ እጥረት ለማረጋጋት በሚሞክሩበት በዚህ ወቅት፣ አንዳንድ አሜሪካውያንም በየነዳጅ ማደያው ተጨማሪ ዋጋ መክፈል ጀምረዋል፡፡ ከእነዚህ መካከል አንዷ የሆኑትፓትርሺያ ባምጋርደነር እንዲህ ይላሉ


“ወደ አንድ ሌላ ተጨማሪ ጭንቀት ውስጥ የሚከተን አንድ ትልቅ ነገር ነው፡፡”


ኮለንያል የጋዝ ማስተላለፊያ መስመር፣ ከፊሉን ምስራቃዊ የአሜሪካ ግዛት፣ የነዳጅ አቅርቦት የሚያዳርስ ሲሆን፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በደረሰበት ጥቃት ስራ አቁሟል፡፡


ጥቃቱ የጋዝ ማስተላለፊያውን መስመር የኮምፒውተር ስርዓት ጠልፎ ቆላልፎ በማገት፣ የገንዘብ ክፍያ መጠየቅ ወይም ransomware attack የተባለው ጥቃት፣ የተፈጸመበት መሆኑም ተመልከቷል፡፡ 


እንዲህ ዓይነቶቹ ጥቃቶች ትላልቅ የንግድ ኩባንያዎችንም ሆነ የመንግሥት ተቋማትን፣ የኢንተርኔት መረቦች ጠልፎ በማገት፣ ወይም አገልግሎታቸውን በማሽመድመድ፣ የገንዘብ ክፍያ መጠየቅ እንደሆነ ተገልጿል፡፡




ኤፍ ቢ አይ፣ እንደዚህ ዓይነቶቹን ወንጀል የሚሰሩት መሰረታቸውን በራሽያ ወይም በምስራቅ አውሮፓ ያደረጉና “ዳርክ ሳይድ” ተብለው የሚጠሩ ቡድኖች መሆናቸውን አስታውቋል፡፡


የዋይት ሀውስ የፕሬስ ሴክረተሪ፣ ጄን ሳኪም ደግሞ እንዲህ ብለዋል


“ለማንኛውም ስለጉዳዩ አንድ ውሳኔ ላይ ከመድረሳችን በፊት፣ የመረጃ ተቋሞቻችን መምረመው የሚደርሱበትን ድምዳሜ እንጠባበቅ፡፡”


ዳርክ ሳይድ የተባለው ቡድን “እኛ የምንፈልገው ገንዘብ ብቻ ነው፡፡ ሌላ ስለ መልካምድራዊው ፖለቲካ ጉዳያችን አይደለም” ማለቱም ተመልክቷል፡፡


ትንናት ማክሰኞ፣ ስለጉዳዩ አስተያየታቸውን የሰጡት፣ የራሽያ መንግሥት ቃል አቀባይ፣ ዲምትሪ ፔስኮቭ፣ አገራቸው እጇ እንደሌለበት በመግለጽ


“ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚደርሰብንን ክስ ሁሉ አጥብቀን እንቃወማለን፡፡” ሲሉ አስተባብለዋል፡፡


ባለፈው ሚያዝያ፣ ሶላር ዊንድ በተባለው ትልቁ የቴክኖሎጂ ድርጅት ላይ፣ አድርሳለች በተባለችው ተመሳሳይ የሳይበር ጥቃት፣ የባይደን አስተዳደር፣ ራሺያ ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ መጣሉ ይታወቃል፡፡


የሳይበር ጥቃት ባለሙያዎች ደግሞ፣ ራሽያን ጨምሮ በዓለም ላይ እንዲህ ዓይነቶቹን ጥቃቶች ለማስቆም የሚያስችል፣ ዓለም አቀፍ ስምምነትና ድንጋጌ መኖር አለበት ይላሉ፡፡


በዊልሰን ማዕከል፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ፕሮግራም ድሬክተር የሆኑት ሜግ ኪንግ እንዲህ ብለዋል


“ይህን ጥቃት ሊያስቆም የሚያስችል አስራር ወይም ዘዴ ካልፈጠርን ድረስ ፣ በራሽያና በአካባቢዋ ባሉ አገሮች ውስጥ ያሉ ወንጀለኞች የንግድ ኩባንያዎችን የስራ መዋቅርና መረጃዎች እያገቱ ገንዘብ የሚጠይቁበን መንገድ ከባድ እስካላደረግ ነው ድረስ፣ የንግድ ድርጅቶች መረጃዎቻቸውን ቅጂ ለመጠባበቂያነት እንዲያስቀምጡ እስካልረዳናቸው ድረስ በመሠረተ ልማቶች ሥራ ላይ የተሰማሩ ሁሉ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ እስከ ምን ድረስ ሊሄድ እንደሚችል እንዲያዩ እስካላደረግን ድረስ ይህ ነገር ይቀጥላል፡፡”


ጥቃቱ የተፈጸመበት የኮሎንያል የጋዝ ማስተላለፊያ መስመር ባለቤት፣ አገልግሎቱን መልሶ ለመጀመር እየሠራ መሆኑን አስታውቋል፡፡


የባይደን አስተዳደርም ይህን ተከትሎ የተፈጠረውን የነዳጅ እጥረት ለማሟላት እርምጃዎችን እየወሰደ ነው፡፡


ከእነዚህ ውስጥ አነስተኛ ጥራት ያላቸውን የጋዝ ዓይነቶች ቀላቀሎ አገግሎት ላይ ለማዋል፣ እንዲሁም የባቡር መስመሮች ነዳጅ ወደ ተቋረጠባቸውና፣ ጥረቱ በጣም ወደ ተከሰተባቸው አካቢዎች እንዲያጓጉዙ በማድረግ እየሠራ መሆኑን አመልክቷል፡፡


የዩናይትድ ስቴት የኃይል ሚኒስትር ጀኒፈር ግራንሆልም እንዲህ ይላሉ


“የጋዝ እጥረት ስላለን አይደለም ይህ ነገር የተከሰተው፡፡ የአቅርቦት መስመራችን ስለተሰናከለ ነው፡፡ ስለዚህ ነገሮች በቅርቡ ወደነበሩበት ይመለሳሉ፡፡”


አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ፣ አስተዳደሩ በዩናይትድ ስቴትስ ወደቦች መካከል ያለው የነዳጅ ማጓጓዝ አገልግሎት፣ አሜሪካ ስሪትና፣ ንብረትነታቸው የአሜሪካውያን በሆኑ ድርጅቶችና መርከቦች ብቻ እንዲከናወን የሚያዘውን የፌደራል መንግሥቱን ህግ፣ የሚያላላበት ሁኔታም ካለ እየተዘጋጀ መሆኑ ተመልክቷል፡፡


የቪኦኤ የዋይት ሀውስ ዘጋቢ ፓትሲ ውዳክስዋራ ከላከቸው ዘገባ የተወሰደ፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-pipeline-cyber-hack-5-12-2021/5887998.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-pipeline-cyber-hack-5-12-2021/5887998.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 May 2021 19:51:42 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/us-pipeline-cyber-hack-5-12-2021/5887998.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/1340F9D0-52DD-4CB9-B7FC-D63B64751163_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የአሜሪካ ሴነተሮች ጉብኘት በሱዳን</title>
            <description>በዚህ ሳምንት ሱዳንን የጎበኙት የዩናይትድ ስቴትስ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት አባላት ልዑካን፣ የሱዳን የሽግግር መንግሥት ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለሚያደርገው ሽግግርና አገሪቱም ከእዳ ነጻ የምትሆንበትን መንገድ እንደሚደግፉ ገልጸዋል፡፡ የምክር ቤት አባላቱ ሱዳን ከኢትዮጵ ጋራ በድንበርና በአባይ ግድብ ዙሪያ ባላት ውዝግቦችም ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡


ትናንት ሀሙስ ጧት በተጠ ናቀቀው፣ ያላፉት ሶስት ቀናት፣ የሱዳንን ጉብኝታቸው ሴነተር ክርስቶፈር ኩንስ እና ሴንተር ክሪስ ሆለን፣ የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱላ ሃምዶክና የሱዳን የሽግግር ልዕልና ምክር ቤት መሪ ጀኔራል አብደል ፈታ ቡርሃንን ጨምሮ፣ ከገንዘብ፣ ከውሃና ከመስኖ ሚኒስትሮች ጋር ተገናኝተዋል፡፡


ውይይቱ ያተኮረው ሱዳን ወደ ዴሞክራሲ በምታደርገው ሽግግር፣ ስላለባት ውዝፍ እዳ ስረዛ እንዲሁም ከአገሯባቿ ኢትዮጵያ ጋር ባሏት የድንበር እና ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ በምትገነባው ግዙፉ ግድብ ዙሪያ ላይ ነበር፡፡




የሱዳን የገንዘብ ሚኒስትር ጅብሪል ኢብራሂም የምክር ቤቱ አባላት ስለተጫወቱት ገንቢ ሚና እንደሚከተለው አመስግነዋል፡፡


&quot;ሁለቱ ሴነተሮች ከኢትዮጵያ ጋር ያላውን የድንበር ውዝግብ ለመፍታት ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ፡፡ ጉብኘቱ የተደረገበት ወቅት እጅግ በጣም ወሳኝ ጊዜ ነው፡፡ ለመጨው የፓሪስ ጉባኤም ሆነ ሱዳን ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ማዕክል ካለባት የውዝፍ እዳ ነጻ እንድትሆን በማድረግ በኩል ሁለቱ የምክር ቤት አባላት የሚሰጡት ድጋፍ እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡&quot;


ሴነተሮቹ በምስራቅ ሱዳን ባሉት የመጠለያ ካምፖች ውስጥ የሚገኙትን ኢትዮጵያውያን ስደተኞችም ጎብኘተዋል፡፡


ሴነተር ኩንስ ዩናይትድ ስቴትስ ባላፈው ታህሳስ ወር ሱዳንን ትገኝበት ከነበረው ሽብርተኞችን ከሚረዱ አገሮች ዝርዝር ውስጥ፣ የሰረዘቻት መሆኑን ገልጸው ፣ የተረጋጋችውን ሱዳን ተመልሳ ማየት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል፡፡


ስለጉብኝታቸውም ዓላማ የሚከተለውን ብለዋል፦


&quot;እዚህ ያለነው ካርቱምና ሌሎች አካባቢዎችን በመጎብኘት፣ በሱዳን ላለው መነቃቃትና ሽግግር፣ ያለንን ድጋፍ ለመግለጽ ነው፡፡ አሜሪካ በቅርቡ ለሱዳን ለመስጠት የገባችውን የ700 ሚሊዮን ዶላር የልማትና ድጋፍ እርዳታ ለመከታተልና ለሱዳን ህዝብ ሰላም ደህንነትና ብልጽግ ናን ለማስገኘት ምን ማድረግ እንደሚኖርብን ለመስማት ነው፡፡&quot;


ሴነተር ኩንስ ሱዳን ለዓመታት ያጣችውን የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ እርዳታ መልሳ ለማግኘት በቅርቡ ያደረገችውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ አድንቀዋል፡፡ ይህንንም ሲገልጹ እንዲህ ብለዋል


&quot;ሱዳን ወደ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ሥርዓት ተመልሳ ለመግባት በምታደርገው ጥረት ለውጥ እያሳየች ነው፡፡ ድሮ የነበሩባት እዳዎች እንዲሰረዙላትና ዓለም አቀፍ ኢንቨርስተሮችን ለመሳብ ለነበሩባት ችግሮች መፍትሄዎች እየተገኙ ነው፡፡ ይህም ስለወደፊቱ ተስፋ ያሳደረብን በመሆኑ ደስተኞች ነን፡፡ ሚኒስትሮቹም የኢኮኖሚ ፖሊስውን አስመልከቶ ጠንካራ ውሳኔዎችን አስተላልፈዋል፡፡&quot;


ኩንስ፣ ሱዳንና ግብጽ ከአባይ የምናገኘው የውሃ ድርሻ ይቀንስብናል በሚል ያላቸውን ስጋት አስመልከቶ ሲናገሩ፣ ሱዳን ግብጽ እና ኢትዮጵያ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ያላቸውን አለመግባባት በሰላማዊ መንገድ መፍታት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡


ኢትዮጵያ ያለምንም ጥርጥር ግድቡን የመገንባት እና ከግድቡም ውሃ የኤልክትሪክ ኃይል አመንጭታ መጠቀም መብቷ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ሱዳንም እንዲሁ የውሃውን ፍሰትም ይሁን ፍሰቱ የሚያስከትለውን የደህንነት ጉዳይ አስመልከቶ ባሉት የቴክኒክ ጉዳዮች የድርሻዋን ተገቢውን መረጃ ማግኘት ይኖርባታል፡፡ ይህንንም አስመልከቶ ግብጽንም ጨምሮ በሶስቱም አገሮች የሚያስማማ የስምምነት ማዕቀፍ መኖር አለበት፡፡


የምክር ቤት አባላቱ ሱዳንን የጎበኙት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው በቅርቡ የተሾሙት አንጋፋው የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ መልክተኛ ጄፍሪ ፌልትመን ከሚያደርጉት ጉብኘት ቀድመው ነው፡፡


ፌልትመን በአስር ሺ የሚቆጠሩ ስደተኞች ወደ ሱዳን የተሰደዱበትን፣ በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ ጨምሮ ፣ የቀጠናውን ፖለቲካ፣ ደህንነትና ሰአብዊ ጉዳዮች የሚደረገውን ጥረት እንዲያግዙ፣ ባላፈው ወር በባይደን አስተዳደር በልዩ ልኡክነት የተሾሙ መሆኑ ይታወሳል፡፡


ፊልትመን ሱዳን፣ ግብጽ፣ ኢትዮጵያ፣ ኤርትራን በመጎብኘት ላይ መሆናቸው የተነገረ ሲሆን አገራቱን በሚያገናኙ ጉዳዮ ላይ በመነጋገር፣ ቀጠናውን አስመልከቶ ዩናትድ ስቴትስ ያላትን አጠቃላይ ፖሊሲ ያቀናጃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡


(በቪኦኤ ዘጋቢ ናባ ሞሃዲን ከሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም የተጠናቀረ ዘገባ) 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/sudan-us-senators-sudan-ethiopia-5-7-2021/5882479.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/sudan-us-senators-sudan-ethiopia-5-7-2021/5882479.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 07 May 2021 22:22:23 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/sudan-us-senators-sudan-ethiopia-5-7-2021/5882479.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/356b8f2a-1f35-49a2-a136-a008ede02840_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በትራምፕ ላይ የተወሰነው ውሳኔ የመሪዎች ፌስቡክ አጠቃቀም ህግ እንዲሻሻል ሊያደርግ ይችላል</title>
            <description>በቅርቡ በፌስቡክና በቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ላይ የተወሰነው ውሳኔ ሌሎች የዓለም መሪዎችም የማህበራዊ ትስስር ገፆችን ለመጠቀም፣ በሂደት እየወጡ ባሉ ህጎች መመራት እንዳለባቸው የሚያመላክት ሆኗል። </description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5880927.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5880927.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 06 May 2021 21:46:23 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ስመኝሽ የቆየ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5880927.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/04DE7027-5421-4148-A1B5-C9F831144494_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአሜሪካ ለጥቁሮች የሲኒማ ጥበብ የውይይት መድረክ የከፈቱ ወጣቶች</title>
            <description>ወጣት መቅደስ ኃይሌ በቴክሳስ የሂውስተን ከተማ ነዋሪ ናት፡፡ እንደ አብዛኛው ሰው ሁሉ እሷም እንዲሁ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ የተነሳ ከአንድ ዓመት በላይ ለሆነ ጊዜ በቤት ውስጥ ተገድበው ከቆዩ ወጣቶች መካከል ናት፡፡ ይህን አስጨናቂ ጊዜ አስደሳችና ውጤታማ ለማድረግ ክሎይ ግሬይ ከተባለች አፍሪካዊት አሜሪካዊት ጓደኛዋ ጋር በመሆን በድረ ገጽ ላይ የሚካሄድ MNC MOVIE CLUB የውይይት መድረክ ፈጥረዋል፡፡


ውይይቱ በአሜሪካ ውስጥ በጥቁር አሜሪካውያን እየተሰሩ የሚወጡ አዳዲስ ፊልሞችን በቡድን ሆኖ ማየትና መገምገም ነው፡፡ታዋቂ የፊልም ባለሙያዎችም ይጋበዛሉ፡፡


ይህ በአጭር ጊዜ ውስጥ በርካታ ተከታዮችን የፈጠረላቸው ከመሆኑም በላይ፣ በኦስካር ሽልማት አሸናፊ የሆኑ የፊልም ባለሙያዎችን ሳይቀር በውይይታቸው ላይ እንዲገኙ አድርጎላቸዋል፡፡


ለምሳሌ ቤሪ ጀንኪንስ በአሜሪካ እጅግ ተደናቂና ታዋቂ ከሆኑ የኦስካር ፊልም አሸናፊዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ሙን ላይትን ጨምሮ በርካታ ፊልሞችን መርቶ ጽፎ አዘጋጅቶ ለሽልማት ከበቁ ጥቂት ጥቁር አሜሪካውያን መካከል አንዱ ነው፡፡ ባንዳንዱም ዘርፍ አሸነፎ ሲሸለም የመጀመሪያው ነው፡፡ የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር አንዱ ጥቅሙ ማስተሳሰር ነውና የነ መቅደስ መረብ ታዋቂ ሰዎችንም ወደ ነሱ የውውይት መድረክ መጎተት ጀምሯል፡፡


እንደ ሂውስተን ክሮኒክል ባሉ ጋዜጠኞችም ላይ የመገናኛ ብዙሃን ሽፋን ያስገኘላቸው መሆኑን መቅደስ ኃይሌ ተፈራ ትናገራለች፡፡ የዛሬው “የኢትዮጵያውያን በአሜሪካ” እንግዳ በማድረግ አነጋግረናታል፡፡


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-mekdes-haile-mnc-movie-club-5-6-2021/5880821.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-mekdes-haile-mnc-movie-club-5-6-2021/5880821.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 06 May 2021 20:41:36 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-mekdes-haile-mnc-movie-club-5-6-2021/5880821.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01098835-D990-4EED-8813-5F99F2CA0470_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢራኑ የኒክሉየር ድርድርና የአሜሪካ ማዕቀብ </title>
            <description>ዩናይትድ ስቴትስ ከኢራን ጋር ወደሚደረገው የኒኩዩለሩ ስምምነት ንግግር በመመለሷ ስምምነቱን ውጤታማ ሆኖ በተሟላ መንገድ ተግባራዊ የሚደረግበትን መንገድ የመሻቱ ድርድር ቀጥሏል፡፡ ታዛቢዎች እንደሚሉት ኢራን በምትኩ ካሽመደመዳት የአሜሪካው ማዕቀብ ጨርሶ መገላገል የምትፈግል እንኳ ቢሆን፣ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው የኒኩለየር መስፋፋት በቸልታ ሊታይ የሚገባው ሳይሆን መፈታት ያለበት ጉዳይ ነው፡፡


ይሁን እንጂ የቪኦኤ ዘጋቢ ዴል ጋቭላክ ከአማን እንደዘገበው ከሆነ፣ በክልሉ በስፋት ተሰራጭተው የሚገኙት በኢራን የሚደገፉ የሺያ ሚሊሺያዎች እና ሚሳኤሎች ጉዳይም እልባት ማግኘት ያለበት መሆኑን ተንታኞች ያሳስባሉ፡፡


ዴቪድ ሼንከር በዋሽንግተን ቅርብ ምስራቅ ፖሊሲ ተቋም ተመራማሪ ሲሆኑ በትራምፕ አስተዳደር ደግሞ የመካከለኛው ምስራቅ ፖሊሲ አማካሪ ነበሩ፡፡ እሳቸውና ሌሎቹ ታዛቢዎች እንደሚሉት ኢራን ከተጣሉባት ማዕቀቦች ለመገላገል እጅግ በጣም ትፈልጋለች፡፡ ወደ ኒዩክለር ስምምነቱ ከመመለስ በፊትም በቅድሚያ ሁሉም ማዕቀቦች እንዲነሱም ትጠይቃለች፡፡


ይሁን እንጂ ሼንከር፣ ድርድሩንም ሆነ የኢራንን እኩይ ባህርይና፣ በወኪሎችዋም አማካይነት፣ በክልሉ ከምታካሂደው ያልተገባ ድርጊት እንድትቆጠብ ለማድረግ፣ ዩናይትድ ስቴትስ፣ ይህን አጋጣሚ መጠቀም አለባት ይላሉ፡፡ እንዲህ ይላሉ


“ከማዕቀቦቹ በቂ የሆነው ክፍል ቢነሳ ለኢራናውያኑ በሌሎቹ ዋና ዋና ጉዳዮች እንዲነጋገሩ የማያስችላቸው ምንም ምክንያት አይኖርም፡፡ እነሱም ሚሣኤሎችንና መከካለኛውን ምስራቅ በማተራመስ ላይ የሚገኙትን በኢራን የሚደገፉ የሺያ ሚሊሺያዎችን የሚመለከቱ ናቸው፡፡ ከኢራቅ አንስቶ እስከየመን ከዚያም እስከ ሶሪያ ሊባኖስ ድረስ ኢራን የምታደርገው ነገር፣ ድርድሩን አስመልክቶ አሸናፊ ሆና ለመውጣት፣ በባይደን አስተዳደር ላይ የሚደረገው ግፊት እንዲጨምር ዘመቻ ማካሄድ ነው፡፡






ሼንከር አያይዘው፣ በቅርቡ ኢራቅ ውስጥ፣ በአሜሪካ ወታደራዊ የጦር ሰፈር ላይ፣ የተቃጥቃውንም ሙከራ እና፣ እንዲሁም የመን ውስጥ በሚገኙ የሁቲ አማጻያን አማካይነት፣ ወደ ሳኡዴ አረብያ የሚደረገወን የድሮን ጥቃት ጠቅሰዋል፡፡


ምንም እንኳ፣ የባይደን አስተዳደር ሁቲዎችን ከተፈረጁበት የሽብረተኝነት ቡድን ዝርዝር ውስጥ፣ ነጻ ቢያወጣቸውም፣ የኢራን ፈጣን ጀልባዎች በባህረ ሰላጤ ያሉትን የአሜሪካ ባህር ኃይል መርከቦች መተናኮላቸውን ቀጥለዋል፡፡


 ይሁን እንጂ፣ የዓለም አቀፉ ፋይናንሽናል ታይምስ ኤዲተር፣ ዴቪድ ጋርድነር፣ በአንድ የኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ ዓለም አቀፍ ተቋም መድረክ ላይ እንደተናገሩት፣ እሳቸው እየተመለከቱ ያሉት፣ በማእቀቡ የተሽመደመደችውን ደካማዋን ኢራንን ነው፡፡


በክልሉ እንደልቧ ማወክ አለመቻልዋንና፣ በአለፈው ዓመትም የወታደራዊ ስትራቴጅስት መኮንኗ፣ ጀኔራል ቃስም ሶሌማኒ፣ በአሜሪካ የአየር ኃይል ጥቃት የተገደሉባት መሆኑን ነው፡፡


ዴቪድ እንደሚሉት፣ ኢራቅ፣ ሶሪያና ሊባኖስ የወደቁ መንግሥታት እንጂ አቅም ያላቸው ኃይለኞች አይደሉም፡፡ ኢራን፣ ከሶሌማኒ ሞት በኋላ ሁኔታዎችን ለማስተካከል እየታገለች ነው፡፡ በሚሊሺ ና በሚሳኤሎች ብቻ ትክክለኛውን አቅምና ኃይለኝነት መገንባት አይቻልም፡፡ ስለዚህ ማዕቀቦቹ እንዲነሱ መጣጣር እጅግ በጣም አስፈላጊ ናቸው፡፡


ስለተገደሉት የኢራን ጀኔራልም ዴቪድ እንዲህ ብለዋል


“የሶሌማኒ መገደል የተለያዩ ቡድኖችን ወደ አንድነት ለማጣምት ትልቅ እንቅፋት ፈጥሯል፡፡ ወታደራዊ ጀኔራል የነበሩት ሶሌማኒን የሚተካ አንድም ሰው አልተገኘም፡፡ እሳቸው አረብኛ ይናገራሉ፡፡ ከኩርዶች ጋር ብቻ ሳይሆን ከሱኒዎቹ የአረብ መሪዎችም ጋር የግ ንኙነት ድልድልይ ፈጥረው ነበር፡፡ የሳቸው ድንገተኛ ሞት በመዋቀሩ ደካማ መሆኑን አመልክቷል፡፡”


ይህም ሆኖ ግን፣ የለንደኑ ዓለም አቀፍ የስትራቴጂክ ጥናት ተቋም እንደሚለው፣ የቅርብ ጊዜ የሳታላይት ምስሎች እንደሚሳዩት፣ በደቡባዊ የኢራን ግዛት ውስጥ የተተከሉት ሰባት አዳዲስ ሚሳኤሎች፣ ለሳኡዲ አረብያና ባህሬን ውስጥ ለሚገኙ ወታደራዊ የአየር ኃይል ማረፊያዎች፣ ትልቅ አደጋ ደቅነዋል፡፡


ሌሎች በኢራን የሚደገፉ ሚሊሻዎችም፣ ኢራቅና ሶሪያን በሚያገናኙ ስትራቴጂክ አካባቢዎች፣ የእስላማዊ መንግሥት ታጣቂዎችን ሽንፈት ተከትለው ለመጠናከር እየሞከሩ ነው፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/iran-us-sanction-5-6-2021/5880761.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/iran-us-sanction-5-6-2021/5880761.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 06 May 2021 19:59:21 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/iran-us-sanction-5-6-2021/5880761.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/15CFADCF-E3E0-4177-8328-2A15FE0D8B8B_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቡድን 7 አባል አገራት ቻይና ሩሲያ ማይነማርና ሶሪያን ተነጋገሩ</title>
            <description>የቡድን ሰባቱ የበለጸጉ አገሮች የውጭ ጉዳይ ምኒስትሮች ዛሬ ማክሰኞ ለንደን ላይ ተሰብስበዋል፡፡ በቻይና እና በሩሲያ፣ በማይናማሩ መንፈንቀለ መንግስት፣ በሶሪያው ግጭትና በአፍጋኒስታን ስላለው ወቅታዊ ሁኔታን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ እንደሚነጋገሩ ይጠበቃል፡፡


“ስብሰባውን የሚመሩት የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶሚንክ ራብ ሲሆኑ፣ ስብሰባው የዴሞክራሲን የነጻትና ሰብአዊ መብት ጉዳዮችን አደጋ ላይ ሊጥሉ በሚችሉ አካባቢያዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ይነጋገራል” ሲል የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡


የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራብ ከዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን ጋር አስቀድመው ትናንት ሰኞ የተነጋገሩ ሲሆን፣ የቡድን 7 አባል አገሮች፣ ለማይናማር ህዝብ የሰአብአዊ እርዳታ በሚጨመርበትና፣ የጦር መሳሪያ ማዕቀብ በሚደረግበት፣ እንዲሁም ከማያናማር ወታደራዊ ጁንታ ጋር ግንኙነት ባላቸው ግለሰቦችና ተቋማት ላይ ማዕቀብ ስለሚጣልበት ሁኔታ ግፊት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡


ይህን አስመልከቶ የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶምኒክ ራብ እንዲህ ብለዋል


“በማይናማር ጥቃቱ እንዲያበቃ እንፈልጋለን፡፡ ወታደራዊ አገዛዙ ወደ ተመረጠ ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር እንዲመለስና ሥልጣን በህዝብ ወደ ተመረጡ ተወካዮች እንዲመለስ እንሻለን፡፡ እኛ ኢላማ በምናደጋቸው እዚህ በምንጥለው ማዕቀብ ብቻ አንወሰንም፡፡ የእንግሊዝ የንግድ ድርጅቶች የማይናማር ሠራዊት ከሚቆጣጠሯቸው የንግድ ድርጅቶች ጋር ሁሉ የሚያደርጓቸውን ግንኙነቶች በሙሉ እንዲያቋርጡ እርምጃ የሚወሰድበትን መንገድ ነው የምንመለከተው፡፡ በዚያም በኩል ግፊት ለማድረግ እንሞክራለን፡፡”


የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊነክን፣ “ዩናይትድ ስቴትስ ከሰሜን ኮሪያ ጋርየዲፕሎማሲ ግንኙነት በማድረግ፣ የኮሪያን ባህረሰላጤን ከኒዩክለር ነጻ የማድረግ ግቧን ለማሳከት፣ ሰሜን ኮሪያን አስመልክቶ ለረጅም ወራት የነበራትን ፖሊሲ እንደገና ትቃኛለች፡፡” ብለዋል፡፡




አሜሪካ በሰሜን ኮሪያ ያለውን የሰአብዊ መብት ጉዳዮች የሚከታተል ልዩ ልኡክ እንደምታቋቁምም ብሊንከን ተናግረዋል፡፡


የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አንተኒ ብሊንከን እንዲህ ብለዋል


“አሁን ያለን ፖሊሲ በሚገባ የተቃኘ፣ ከሰሜን ኮሪያ ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማድረግ ክፍት የሆነና የዩናይትድ ስቴትስን፣ የአጋሮቻችንና በአካባቢው ያሰማራናቸውን ኃይሎቻችንን ደህንነት በጠበቀ መልኩ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል አቀራረብ ነው፡፡


እሱን እያደረግንም ከአጋሮቻችንና ወዳጆቻችን፣ የደቡብ ኮሪያ ሪፐብሊክን ጨምሮ፣ ከጃፓናን በሂደት ከሚመጡ ሌሎች አገሮችም ጋር በቅንጅትና በመመካከር እንሰራለን፡፡”


የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ ስበሰባ የተካሄደው በመጭው ሰኔ እዚያው እንግሊዝ ውስጥ ይደረጋል ለተለባለው የቡድን 7 አባል አገራት መሪዎች መሆኑም ሁኔታዎችን ለማመቻቸት መሆኑም ተመልክቷል፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/blinken-europe-5-4-2021/5878025.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/blinken-europe-5-4-2021/5878025.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 04 May 2021 21:44:10 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/blinken-europe-5-4-2021/5878025.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/DAACC9C6-F191-4E9D-BBA4-DA2A2339BB8E_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ባይደን በ100 ቀናት ለአፍሪካ ያደረጓቸው ጥቂት ትላልቅ ነገሮች </title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ የመጀመሪያውን 100 ቀናቸውን የፈጁት ሙሉ ኃይላቸው በአሜሪካው ውስጥ በተከሰተው የኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ላይ በማዋል ነው፡፡ እልህ አስጨራሽ በነበረው በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ግን በአፍሪካ ውስጥ ተቀባይነትን ያገኙ ጥቂት ነገሮችን አድርገዋል፡፡


ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ወደ ሥልጣን በመጡበት የመጀመሪያው ቀናቸው ዩናይትድ ስቴትስ ከዓለም የጤና ድርጅት ለመውጣት የነበራትን እቅድ እንድታቆም አድርገዋል፡፡


ባይደን ከሳቸው በፊት የነበረው አስተዳደር ከዓለም አቀፉ የጤና ተቋም ለመውጣት የወሰነውን አወዛጋቢ ውሳኔ መቀልበሳቸው ዓለም አቀፋዊ ድጋፍ አስገኝቶላቸዋል፡፡


በተለይ የአፍሪካ የጤና ኃላፊዎች ውሳኔውን በጤናው ረገድ በዓለም ፍትሃዊ ስርዓት እንዲኖር ያደርጋል ብለውታል፡፡


ባይደንም ለድሆቹ አገሮች የክትባት ስርጭቱ እንዲዳደረስ፣ ለኮቫክስ ክትባት ስርጭት የ2ቢሊዮን ዶላር ተጨማሪ እርዳታ ጠይቀዋል፡፡


ሥልጣን በያዙ 90ኛ ቀናቸው ላይ፣ እኤአ ሚያዝያ 20 ያስተላለፉት መልዕክትም፣ ከውቂያኖሱ ባሻገር ባለው የዓለም ክፍል አስተጋብቷል፡፡ 


በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዳለ ህይወቱ ባለፈው ፣ የሚኒያፖልሱ ነዋሪ፣ ጆርጅ ፍሎይድ ግድያ ተከሶ የነበረው የፖሊስ መኮንን ላይ፣ የጥፋተኝነት ውሳኔ በተላለፍበት ወቅት ፕሬዚዳንት ባይደን ሲናገሩ እንዲህ ብለው ነበር


“ይህን አጋጣሚ ሥራችንን አከናውነን ጨርሰናል ብለን እንዲሁ ልንተወው አይገባም፡፡ በደንብ ልንመለከተው ይገባናል፡፡ ልብም እንድንለው ያስፈልገናል፡፡ እነዚያን 7 ደቂቃ ከ29 ሰኮንዶች እንደተመለከትናቸው አድርገን ልናየው ይገባናል፡፡ መስማትም ይኖርብናል፡፡ “መተፈንስ አልቻልኩም መተንፈስ አልቻልኩም!” እነዚያ የጆርጅ ፍሎይድ የመጨረሻ ቃላት ነበሩ፡፡ እነዚያ ቃላት ከሱ ጋር አብረውት እንዲሞቱ ማድረግ አንችልም፡፡ እነዚያን ቃላት መስማታችንን መቀጠል አለብን፡፡




ፍሎይድ በሂውስተን ተወልዶ፣ በሚኒያፖልስ የተገደለ ጥቁር አፍሪካ አሜሪካዊ ነው፡፡ ፍሎይድን ለህልፍት አብቅቷል በተባለው የቀድሞ የፖሊስ መኮንን ደሪክ ሻቭን ላይ ፣ የጥፋተኝነት ውሳኔ ሲተላለፍበት፣ መላው አፍሪካ ሂደቱን የተከታተለው በጭንቀት ውስጥ ሆኖ ነበር፡፡


ባለፈው ዓመት በሻቭን ጉልበት ሥር ሆኖ እስትፋንሱ እስክታልፍ በተራዘመ ጭንቅ የታፈነው ፍሎይድ፣ የሚወዳቸው ሁሉ እንዲያስጥሉት እየተማጸነ ሲጮህ ታይቷል፡፡


ያ ትዕይንት ተቃውሞን የቀሰቀሰ ሲሆን በዩናይትድ ስቴትስ የፖሊስ አሠራር ደንብ እንዲሻሻልም የጠየቀ ነበር፡፡


በደቡብ አፍሪካ የብዝህነት አስልጣኝ የጾታና ዘር ጉዳዮች ተራማሪ የሆኑት፣ እንደ አሳንዳ ጓሸኜ የመሳስሉት አፍሪካዊ ተንታኞች፣ የዘር መድልዎ ችግር መኖሩን አምኖ በመቀበል፣ ባይደን ለአሜሪካ ህዝብ ያሰሙትን ንግግር ደግፈውታል፡፡


ደቡብ አፍሪካም ብትሆን፣ ለመቶ ዓመታት ተንሰራፍቶ ከቆየው የቅኝ ገዥነት፣ ጨካኝና ዘረኛው የአፓርታይድ መንግሥት በኋላ፣ አሁን ድረስ ካለባት የዘር መድልዎ ችግሮች ለመላቀቅ እየታገለች ያለች አገር ናት፡፡


አሳንዳ ጨምረው እንደተናገሩት፣ ምክትል ፕሬዚዳንቷ ከማላ ኸሪስ ተሰሚነት እንዳላቸው ጥቁር ሴት በመሆናቸው፣ ባይደን የዘር መድልዎን ለመታገል ለሚያደርጉት ጥረት ክብደት እንዲኖረው ያደርጉታል ይላሉ፡፡ ይሁን እንጂ ከአስተዳደሩም ሆነ ከአሜሪካ ተቋማት ብዙ ነገር እንደሚጠብቁ ተናግረዋል፡፡


“ከማላ ኸሪስን እናደንቃለን፡፡ እሳቸውን ማደናቃችንም ጥሩ ነገር ይመስለኛል፡፡ ይሁን እንጂ ግን መዋቅራዊ ዘረኝነት በተዘረጋበት መዋቅር ውስጥ ያለው ባለቀለም ሰው ለውጥ ማምጣት የሚችልበት እድል እጅግ እጅግ አነስተኛ ነው፡፡


ስለዚህ ሥርዓቱን እና አድሏዊነትን ባለበት እንዲቆይ የሚያደርገውን መዋቅር እስካልታገልነው ድረስ በዩናይትድ ስቴትስም ሆነ በመላው ዓለም ለውጥ የምናይ አይመስለኝም፡፡ ስለዚህ አዎ እውነትነ ነው ለአሜሪካና ለባይደን ጥሩ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ግን ሊያመጡት ስለሚችሉት መዋቅራዊ ለውጥ መናገር ትችላላችሁ? “


መሰረቱን በጆሀንስበርግ ያደረገው የተንታኙ ብሩክስ ስፔክተር ባይደን ተችዎች፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የአፍሪካን ፖሊሲ አስመልከቶ ያደረጉት ስር ነቀል ወይም ትልቅ ለውጥ የለም ብለው ይተቹ እንደነበሩት ሁሉ፣ ባይደንም መተቸታቸው በራሱ አንድ ተፈላጊ ለውጥ ነው ይላሉ፡፡


“በዩናይትድ ስቴትስ የንግድ ልውውጥ ማእቀፍ ውስጥ ያለውን የአፍሪካን የእድገት አማራጭ ድንጋጌ (አጎዋ) ማጠናከር አስፈላጊ ነው፡፡”


“በየጊዜው ድንገት እየተቆራረጡና እየተለዋወጡ ከሚደረጉ የፖሊሲ ለውጦች ይልቅ መሬት ይዘው በዝግታ በረጋና ዘላቂ በሆነ መንገድ ነገሮችን ማከናወን ተመራጭ ነው፡፡ በአህጉሪቱ የኢኮኖሚ ለውጥ እንዲመጣ ድጋፍን መስጠት ከፈለግ ከፈልክ በአህጒሪቱ የኢኮኖሚ እድገት የሚያጠናክር ፖሊስን ማውጣት ነው፡፡”


ለበርካታ ዓመታት የአሜሪካን ዲፕሎማት ሆነው በውጭው ዓለም ያገለገሉት ስፔክተር “ባይደን በአፍሪካ ላይ የሚያሳድሩት ተጽእኖ በጊዜ ሂደት የሚታይ ይሆናል፡፡”


“የፕሬዚዳንቶች ታሪክና አበርክቶ የሚገነባው በዓመታት ሥራቸው እንጂ በቀናት አይደለም፡፡ 100 ቀናት እንኳ ቢሆኑትም ማለት ነው፡፡” ብለዋል፡፡


(የቪኦኤ ዘጋቢ አኒታ ፖል ከጆሀንስበርግ ከላከችልን ዘገባ የተወሰደ)

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/biden-100days-africa-4-30-2021/5873354.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/biden-100days-africa-4-30-2021/5873354.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 30 Apr 2021 17:50:07 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>አፍሪካ</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/biden-100days-africa-4-30-2021/5873354.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9190bd53-57b4-4724-9aec-cf771b6e0237_cx0_cy2_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ባይደን 100ኛ የሥልጣን ቀናቸውን አስመልክቶ ንግግር ሊያደርጉ ነው</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን፣ በፕሬዚዳንትነት የቆዩበትን የመጀመሪያዎቹን 100 ቀናት አስመልክቶ በዚህ ሳምንት ለምክር ቤት አባላት ንግግር ያሰማሉ፡፡ በቅርቡ ከህዝብ በተሰበሰበ አስተያየት መለከያ መሰረት፣ ትንሽ በለጥ ያለ ቁጥር ያላቸው፣ አብዛኞቹ አሜሪካውያን የሥራ አፈጻጸማቸውን ደግፈዋል፡፡ የዴሞክራትና የሪፐብሊካኖቹ መሪዎች ፕሬዚዳንቱ በዚህ ንግግራቸው እንዲያነሷቸው የሚፈልጓቸው ብዙ ነገሮች እንዳሉም ተመልክቷል፡፡


ፕሬዚዳንት ባይደን 100ኛ የሥራ ቀናቸውን አስመልከቶ፣ ለሁለቱም ምክር ቤት አባላት በጋራ በሚያሰሙት ንግግራቸው፣ ባሳለፏቸው 100 ቀናት ውስጥ ያከናወኗቸውን አብይ ሥራዎችና፣ በመጪዎቹ ወራት ሊያከናውኗቸው ያቀዷቸውን አጀንዳዎቻቸውን ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡


በቅርቡ የዋሽንግተን ፖስት እና የኤቢሲ የዜና ማሰራጫዎች አማካይነት፣ ከህዝብ የተሰበሰበው አስተያየት እንደሚያመለክተው፣ 52 ከመቶ የሚሆኑ አሜሪካውያን፣ የፕሬዚዳንቱን የሥራ አፈጻጸም ደግፈዋል፡፡ በትንሽ ቁጥር በለጠ ያለው ይህ አሃዝ፣ በቅርብ ጊዜ ከነበሩ የቀድሞ ፕሬዚዳንቶች ሁሉ ዝቅ ያለ ሲሆን፣ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከነበሩበት ተመሳሳይ ጊዜ አንጻር ግን የበለጠ ሆኖ ታይቷል፡፡


በጥቁሩ ጆርጅ ፍሎይድ ግድያ ተወንጅለው፣ ጥፋተኛ የተባሉት የቀደሞ ፖሊስ መኮንን፣ የሰሞኑ ዜና ከሆኑ በኋላ፣ ባይደን በዚህ ንግግራቸው፣ ያነሱታል ተብሎ የሚጠበቀው፣ በጆርጅ ፍሎይድ ስም የተሰመየው የፖሊሶችን አሰራር ደንብ ማሻሻያዎችን ይሆናል ተብሎም ተገምቷል፡፡


የዴሞክራቶቹ የፖሊስ አሰራር ማሻሻያ ረቂቅ፣ በፍሎይድ ስም የተሰየመ ሲሆን፣ የተወካዮቹን ምክር ቤት አልፎ፣ ወደ ህግ መወሰኛው ምክር ቤት አምርቷል፡፡




የተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑትና የካሊፍሮኒያዋ ዴሞክራት፣ ካረን ባስ፣ ረቂቁን አስመልከቶ እንዲህ ይላሉ


“በአሁኑ ወቀት በአስቸኳይ አንድ ነገር መደረግ ያለበት መሆኑን በመግለጽ ጉዳዩን አንስተው እንደገና ነፍስ ይዘሩበታል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እኛም ጉዳዩን አንስተን ወደፊት እንደገፋበት፣ ማበረታች የሚሆነን ይመስለኛል፡፡”


ይሁን እንጂ፣ የሪፐብሊካን መሪዎች፣ ባይደን በንግግራቸው እንዲያነሱ የሚፈልጉት፣ በዩናይትድ ስቴትስ እና ሜክስኮ ድንበር ያለውንና እነሱ “ቀውስ” ብለው የሚጠሩትን የስደተኞች ጉዳይ ነው፡፡ ቀደም ሲል በተጠቀሰው የህዝብ አስተያየት መለከያ፣ 53 ከመቶ የሚሆኑት አሜሪካውያን፣ ባይደን የስደተኞችን ሁኔታ የያዙበትን መንገድ አልተቀበሉትም፡፡


የፍሎሪዳው ሪፐብሊካን ሴነተር ሪክ ስካት እንዲህ ብለዋል


“የድንበሩን ደህንነት ማስጠበቅ አለብን፡፡ ከዚያ በኋላ፣ ይህን አገር በህጋዊ መንገድ ህልማቸውን ለመፈጸም የመጡ ሰዎች፣ እኛ ልንኖር የምንፈልገውን ህልም መኖር የሚችሉበትን መንገድ ማፈላለግ እንችላለን፡፡”


የባይደን አስተዳደር የስደተኞቹን ፍሰት፣ ከምንጫቸው ለመግታት፣ በማዕከላዊ አሜሪካ ሁኔታዎች የሚሻሻሉበትን መንገድ የሚያስችሉ ፖሊስዎችን ለማውጣት እያሰበ ነው፡፡


የአስተዳደሩንም ጥረት እንዲያግዙ ልዩ ኃላፊነት የተጣለባቸው ምክትል ፕሬዚዳንት ካማላ ኸሪስ በሚቀጥለው ሰኔ ወደ አካባቢዎቹ ያመራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡


(የቪኦኤ ዘጋቢ ሚሸል ኲይን ከላከችው ዘገባ የተወሰደ፡፡)

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-ahead-4-26-2021/5867068.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-ahead-4-26-2021/5867068.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 26 Apr 2021 17:03:04 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-ahead-4-26-2021/5867068.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/fc15d21f-f588-4c1c-b673-6bbd9274f227_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዴሞክራቶች በየግዛቶቹ የወጡትን የመራጮች መብት ገደብ እየታገሉ ነው</title>
            <description>በደቡብ ዩናይትድ ስቴትስ ጆርጅያ ክፍለ ግዛት በፖስታ ቤት በኩል የሚላከውን የድምጽ አሰጣጥ ለመገደብ፣ የመራጮችን ማንንነት አጥብቆ ለማጣራት የወጣው አዲሱ ህግና፣ በቁጥር አነስተኛ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች የመምረጥ መብት፣ በአገር አቀፍ ደረጃ ክርክር አስነስቷል፡፡


የዴሞክራቲክ ፓርቲ ሕግ አውጭዎች ምንም እንኳ በአሜሪካው የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የማለፍ እድሉ አነስተኛ ቢሆንም፣ በመምረጥ መብት ህጎች ዙሪያ ያሏቸውን አማራጮች እየተመለከቱ ነው፡፡


ከ2020ው ምርጫ ማግስት በኋላ፣ በመላው አገሪቱ፣ ምርጫውን በሚመለከት አዲስ ስጋት ተከስቷል፡፡


በየቦታው ያሉት ዜጎችና፣ አንዳንድ የቢዝነስ ተቋማት ሳይቀሩ፣ ፕሬዚዳንት ባይደን በጠባብ ልዩነት ባሸነፉበት የጆርጅያ ክፍለ ግዛት፣ የወጣው አዲሱ ህግ፣ “አነሰተኛ ቁጥር ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍሎችን ያገለለ ነው” በማለት ይቃወሙታል፡፡


የዴሞክራቱ ህግ አውጭ ሴንተር ዲክ ደርባን እንዲህ ይላሉ


“በጆርጅያ ያሉት ሪፐብሊካን ህግ አውጭዎች በምርጫው ላይ ያላቸውን ችግር የድምጽ አሰጣጡን በማክበድ ሊወጡት የወሰኑ ይመስላል፡፡ ምክንያቱም ባላፉት ምርጫ ድምጽ የሰጡት መራጮች የእነሱ መራጮች አይደሉም፡፡ ይህ አስተሳሰብ ከመሰረቱ አሜሪካዊ አይደለም፡፡”


ዲሞክራቶች እንደሚሉት፣ ባለፈው ዓመት ውስጥ ብቻ፣ የመምረጥ መብትን የሚያከብዱ 360 ህጎች 47 ክፍለ ግዛቶች ውስጥ ወጥተዋል፡፡


ሪፐብሊካኖች ደግሞ፣ ዴሞክራቶች የምርጫውን ደህንነት ለመጠበቅ የሚወሰዱ ርምጃዎችን በሙሉ እየተቃወሙ ነው ሲሉ ይከሷቸዋል፡፡


ሪፐብሊካኑ ሴንተር ቸክ ግራስሊ እንዲህ ብለዋል


“ይህ በጣም ቀላል ነው፡፡ የምርጫውን ተአማኒነት ለማስከበር ህግ ባወጡ ክፍለ ግዛቶቻችን ላይ የተቃጣ የቅርብ ጊዜው ጥቃት ነው፡፡ አገር አቀፍ ዴሞክራቶችና ትላልቅ የቢዝነስ ተቋማት በወጣው የድምጽ አሰጣጥ ህግ የተነሳ ጆርጅያን ለማስፈራራት ወስነዋል፡፡”




በ2020ው ምርጫ አነስተኛ ቁጥር ያላቸውን የማህበረሰብ አባላት በነቂስ እንዲወጡ አድርገዋል የሚባሉት እንደ ስቴሲ አብርሃም ያሉት አክቲቪስቶች ደግሞ “አዲሶቹ ህጎች አዳዲሶቹ የዘር መድልዎ መልኮች ናቸው” ይላሉ፡፡ እንዲህ ይላሉ ስቴሲ


“በርግጥ የዘረኝነት ይዘት ያሉበትም ክፍሎች አሉት፡፡ ምክንያቱም የተወሰኑ የማህበረሰብ ክፍል መራጮችን ባርህይ በመጥቀስ፣ በምርጫው እንዳይሳተፉ ለመገደብ ወይም ጨርሶ ለማጥፋት የተጠቀሙበት የዘር ማጥላላትም አለ፡፡”


ዴሞክራቶቹ በሚቆጣጠሩበት የተወካዮች ምክር ቤት የወጡ የመምረት መብት ህጎች፣ የምርጫውን ደንቦች አገር አቀፍ ደረጃ ያላቸው እንዲሆኑ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ 


ሪፐብሊካኖች ግን፣ ይህ የክፍለ ግዛቶችን ሥልጣን የሚነጥቅ ነው በማለት ይቃወሙታል፡፡


ዲሞክራቶች እጅግ በጠበበ መንገድ አብላጫውን በተቆጣጠሩበት የህግ መወሰኛው ምክር ቤት የዴሞክራቶቹ ህግ የማለፍ እድሉ በጣም አነስተኛ መሆኑም ተመልከቷል፡፡


(የቪኦኤ የምክር ቤቶች ዘጋቢ፣ ካትሪን ጊፕሰን፣ ከላከቸው ዘገባ የተወሰደ)

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-voting-rights-4-21-2021/5862122.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-voting-rights-4-21-2021/5862122.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 22 Apr 2021 00:54:19 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/us-voting-rights-4-21-2021/5862122.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/379d160e-4f82-40e8-a5a9-0b472a7b7c3d_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አሜሪካ ራሽያ ላይ ጠንካራ ማዕቀብ ጣለች</title>
            <description>የባይደን አስተዳደር ትናንት ሀሙስ ባወጣው መግለጫ፣ ሩሲያ፣ በዩናይትድ ስቴትስ ትልቁን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂን የመረጃ መረብ በሚያስተዳድረው፣ የሶላርዊንድስ ድርጅት ላይ፣ የስለላና የጥቃት ዘመቻ በመፍጠር፣ እንዲሁም የ2020 ምርጫ ላይ ተጽእኖ ለማሳደር መሞከሯን ተከትሎ፣ ጠንካራ የኢኮኖሚ ማዕቀብ የተጣለባት መሆኑን አስታውቋል፡፡


ዩናይትድ ስቴትስ ትናንት ባወጣቸው መግለጫ፣ ሩሲያ፣ የሳይበር መረጃ መረብን በመጠላለፍ፣ የምርጫውን ሂደት ጣልቃ ገብታ በማደነቃቀፍና በሌሎች ጎጂ ድርጊቶቿ፣ የበረታ ቅጣት የተጣለባት መሆኑን አስታውቃለች፡፡


ፕሬዚዳንት ባይደን ለራሽያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ባደረጉላቸው የስልክ ልውውጥ፣ ይህንኑ ያሳወቅዋችው መሆኑም ተዘግቧል፡፡


ባይደን፣ በዚህ ዓመት በአውሮፓ በሚደረገው ስብሰባም፣ ፑቲን እንዲገኙ የጋበዝዋቸው መሆኑም ታውቋል፡፡


እንዲህ ብለዋል ባይደን


“በዩናይትድ ስቴትስ ከራሽያ ጋር ለመስራት ፍላጎቱ አላት፡፡ መኖርም ይገባዋል፣ ወደፊትም ይኖረናል፡፡ ራሽያ የዩናይትድ ስቴትስ ጥቅሞች መጉዳት ስትፈልግ ግን ምላሹን እንሰጣለን፡፡ ሁልጊዜም አገራችንን፣ ተቋሞቻችንን ሰዎቻችንንና አጋሮቻችንን ለመከላከል ደግሞ እንቆማለን፡፡”


ዩናይትድ ስቴትስ በ2020ው ፕሬዚዳንታዊው ምርጫ ጣልቃ በመግባት ዶናልድ ትራምፕ እንዲመረጡ ጥረት አድርጋለች ከተባለችው ሞስኮ ጋር በተያያዘ፣ 10 የሩሲያ ዲፕሎማቶችን ከአገሯ ያባረረች ሲሆን፣ 32 የሚደርሱ ተቋማትና ግለሰቦችም ላይ ማዕቀብ ጥላለች፡፡




በተመሳሳይ መግለጫም የባይደን አስተዳደር ከራሽያ ጋር አብሮ ለመስራት እንደሚፈልግ አስታውቋል፡፡


ከአትላንቲክ ባሻገር የአዲስቱ አሜሪካ የደህንነት ፕሮግራም ዳይሬክተር፣ አንድሪያ ኬንዳል፣ አብሮ ስለ መስራቱና ስለ መገፋፋቱ ጉዳይ እንዲህ ይላሉ


“በድጋሚ ይህንን አብሮ የመስራትና የመገፋፋት ፍላጎት የተደባለቀበትን ግንኙነት እንመለከታለን፡፡ በተለይም ለሞስኮ እጅግ አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ማበረታቻ ለመፍጠር ጥረት ሲደረግም እናያለን፡፡ ለምሳሌ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የሚደረግን ዘላቂና ስትራቴጂክ ግንኙነት የሩሲያው ፕሬዚዳንት በጣም ይፈልጉታል፡፡ ለምሳሌ እንደ ኢራንና አፍጋኒስታን ባሉ ንግግሮች ላይ ሩሲያም ከውይይቱ ጠረጴዛ ላይ እንድትጨመር ይፈልጋሉ፡፡ ስለዚህ እነዚያን ሁለቱን አቀራረቦች በማጣመር ግንኙነቱን ጠባቂ የሆኑ ነገሮችን ማስቀመጥ የሚቻል ይመስለኛል፡፡“


ባለፈው ታህሳስ ወር፣ በአሜሪካ ፌደራል ተቋማት እና የንግድ ድርጅቶች ይፋ ለተደረገው፣ የሶላርዊንዱ የሳይበር ጥቃት፣ ዋሽንግተን ለመጀመሪያ ጊዜ፣ ሞስኮን በግልጽ ተጠያቂ አድርጋታለች፡፡


ከዊልሰን ማዕከል ሩሲያ የምትነዛውን የመረጃ ውዥንብር የሚያጠኑት ኒና ጃንኮዊችዝ እንዲህ ይላሉ


“በሶላርዊንድ በደረሰው ጥቃት ገና በደንብ ይፋ ያልተደረጉና ያልተደረሰባቸው ሌላ መግቢያዎች ወይም ለሌላ አደጋ የሚያጋልጡ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ራሺያ እነዚያን ነገሮች የምትጠቀምባቸው ከሆነ፣ በሩሲያ የስለላ ተቋሞች ላይ ምናልባትም በሩሲያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ቤተሰቦቻቸው ላይ፣ ያነጣጠረ ማዕቀብ ሊቀጥል ይችላል፡፡ ያ ደግሞ አሁንም ብዙዎቹ የማዕቀብ ጠበብቶችም የሚገፋፉት ይመስለኛል፡፡”


ያለፉት ማዕቀቦች ሞስኮን ሊያንበረክኩ አልቻሉም፡፡ አሁን ግን ባይደን ፣ ከቀዳሚ የአክስዮን ገበያ ላይ፣ በሩሲያ የመገበያያው ገንዘብ፣ ሩብልን በመጠቀም፣ የሩሲያን ቦንድ የሚገዙ የአሜሪካ የፋይናንስ ተቋማትን ለማግደ፣ ተጨማሪ ግፊት እያደረጉባቸው መሆኑ እየተሰማ ነው፡፡


ዋይት ሀውስ አስፈላጊ ከሆነ፣ በሁለተኛው የአክስዮን ገበያም የሚደረገውን ግብይት ማገድ እንደሚሻ ፍንጮችን ሰጥቷል፡፡


የአሜሪካ ባንኮች ከ2019 አንስቶ ከሩብል ውጭ በሆኑ የአክስዮን ገበያዎች የሩሲያን ቦንድ በመግዛት የንግድ ልውውጦችን እንዳያደርጉ ታግደዋል፡፡


የዋይት ሀውስ የፕሬስ ሴክረታሪ ጄን ሳኪ እንደሚከተለው ያስረዳሉ


“ይህ ማለት፣ 80 ከመቶ የሚሆነው የሩሲያ ሉዓላዊ እዳ፣ በተለይም በሩብል የሚፈጸመው አብዛኛው ግብይት፣ በማዕቀባችን የተካተተ አይደለም፡፡ አሁን ግን ወደዚህም ክፍል እየገባን ነው፡፡ ይሁን እንጂ ግን አሁንም ወደፊት ለመሄድ የሚያስችሉን ብዙ አማራጮች አሉን፡፡ “


በራሽያ የክሬሊምን ሰዎች ግን፣ የተባለውን ክስ በሙሉ ያስተባብላሉ፡፡ የራሽያ የውጭ ጉዳይ ምኒስትር ቃል አቀባይ፣ ማሪያ ዛኮሮቫ እንዲህ ይላሉ


“እንደዚህ ያለው ጠብ አጫሪነት ባህርይ በእርግጠኝነት አጸፋው ይመለስለታል፡፡ ለማዕቀቡ ምላሽ መሰጠቱ የማይቀር ነው፡፡”


ማዕቀቦቹ የመጡት ራሽያ ወታደሮችዋን በዩክሬን ድንበር አቅራቢያ ማከማቸት ስትጀምር ነው፡፡ በአካባቢው፣ በዩክሬን መንግሥትና ራሽያ በምትደግፋቸው ኃይሎች መካከል፣ ላለፉት ሰባት ዓመታት የቀጠሉ፣ ግጭትን የሚያባብሱ ነገሮች፣ አሁንም አሉ፡፡


የእምርጃው ሌላው ምክንያት፣ ራሽያ በአፍጋኒስታን የነበሩ የዩናይትድ ስቴትስና አጋሮችዋን የጦር ሰዎች ለማስገደል፣ ቅጥር ነፍስ ገዳዮችን አሰማርታለች የሚለውም ክስ፣ እንደሚገኝበት ተመልክቷል፡፡


(የዋይት ሐውስ ዘጋቢ ፓትሲ ውዳክስዋራ ካጠናቀረችው ዘገባ የተወሰደ)

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-russia-sanction-4-16-2021/5855885.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-russia-sanction-4-16-2021/5855885.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 16 Apr 2021 19:09:25 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/us-russia-sanction-4-16-2021/5855885.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/95AA246A-3238-4473-A41D-51E85A650CF0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ባይደን “ረጅሙ ጦርነት አብቅቷል” የአሜሪካ ወታደሮች አፍጋኒስታንን በመስከረም ይለቃሉ</title>
            <description>ፕሬዚዳንት ባይደን ዩናይትድ ስቴትስ እኤአ በመጭው መስከረም 11/2021 ፣ 2ሺ500 የሚሆኑ ወታደሮችዋን ከአፍጋኒስታን እንደምታስወጣ በትናንትናው እለት በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡


ይህ ቀነ ገደብ፣ ባለፈው ዓመት የትራምፕ አስተዳደርና የታሊባን መሪዎች ከተስማሙበት ግንቦት 1 ፣ ለወራት ያህል ዘግይቶ የሚፈጸም መሆኑም ተነግሯል፡፡


ከ20 ዓመታት በኋላ፣ ወደ ትሪሊዮን ዶላሮች ካወጣችበት፣ ከ2ሺ300 አሜሪካውያንን ህይወት ካጣችበትና በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የአፍጋን ዜጎች ህይወታቸውን ከተነጠቁበት በኋላ፣ ዩናይትድ ስቴትስ አሁን ይበቃል እያለች ነው፡፡


ምክንያቱንም ባይደን እንዲህ ይገልጹታል


“ወደ ጦርነት የሄደነው ግልጽ ግብ ይዘን ነው፡፡ ግባችንን አሳክተናል፡፡ ቢላደን ሞቷል፡፡ አልኬዳ በኢራቅ እና አፍጋኒስታን ውስጥ ተመናምኗል፡፡ ስለዚህ ይህ የሁልጊዜው ጦርነት መቆሚያው ጊዜ ነው፡፡


እኤአ መስከረ 11 2001 ላይ የአልኬዳ አሸባሪ ቡድን አባላት በዩናይትድ ስቴትስ ላይ ያደረሱትን ጥቃት ተከትሎ ከዛሬ ሁለት አስርት ዓመት በፊት በዚያ የተጠለሉትን አሸባሪዎች ለማደን፣ አፍጋኒስታንን የወረረችው አሜሪካ፣ አሁን በአፍጋኒስታን የቀሩትን 2500 የሚሆኑ ወታደሮችዋን ጨርሳ እንድምታወጣ ባይደን ተናግረዋል፡፡


የትራምፕ አስተዳደር ከታሊባን መሪዎች ጋር የነበረው ስምምነት ወታደሮቹን ለማስወጣት የታሰበው ግንቦት 1 ላይ ሲሆን በአጸፋው አፍጋኒስታንን የተቆጣጠሩት የእስልምና አክራሪዎቹ የታሊባን መሪዎች ከአልኬዳ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት ለማቋረጥ ተስማምተዋል፡፡


ፕሬዚዳንት ባይደን ውጊያውን መቀጠል አስፈላጊነቱ የማይታቸው መሆኑን በመግለጽ አፍጋኒስታንን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለቀው መውጣት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል፡፡ “ያንኑ ዓይነት ጦርነት እያካሄዱ የተለየ ውጤት መጠበቅ አያስፈልግም” ባይ ናቸው፡፡


አንዳንድ የሪፐብሊካን አባላት ታሊባኖች ቀጣናውን መልሰው የሚቆጣጠሩት ሲሆን፣ ይህም የአፍጋኒስታንና የአሜሪካን ግንኙነት ይጎዳል ይላሉ፡፡ ሪፐብሊካኑ ሴነተር ሊንዚ ግራም አንዱ ናቸው፡፡ እንዲህ ብለዋል


“ፕሬዚዳንት ባይደን እንዳለመታደል ሆኖ የመረጡት እጅግ አስቸጋሪ የሆነውን ውሳኔ ነው፡፡ ይህም ለቆ መውጣት ነው፡፡ ምንም ይሁን ምን፡፡”


ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በመቀናጀት የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት ኔቶ ወደ 10 ሺ የሚደርሱ ወታደሮቹን ግንቦት 1 ቀን ከአፍጋኒስታን እንደሚያወጣ በትናንትናው እለት አስታውቋል፡፡ የኔቶ ዋና ጸሀፊ በዚህ መካከል ወታደሮቻችን ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም የታሊባን ጥቃት ከፍተኛ አጸፋ ይጠብቀዋል ብለዋል፡፡




ፕሬዚዳንት ባይደንም እሳቸውና አጋሮቻቸው ወደ 300ሺ የሚደርሱ ተጨማሪ የአፍጋን ወታደሮችን እንደሚያሰልጥኑ፣ በሰብአዊ እርዳታና በዲፕሎማሲው በኩልም እንደሚያግዟቸው ተናግረዋል፡፡


ባይደንን ጦራቸውን ከግንቦት ይልቅ በመስከረም ወር እንደሚያስወጡ የሰጡትን መግለጫ ተከትሎ፣ ታሊባን ባወጣው መግለጫ ፣ ትልቅ ሁከት ሊነሳና የአፍጋን መንግስ ት ሊፈረካከስ ይችላል ሲል አስጠንቅቋል፡፡


የአፍጋኒስታን የሰላም ማዕክል ከታሊባን ጋር ለመደራደር በዚህ ወር መጨረሻ ላይ ቱርክ ውስጥ እንደሚገኙ የተነገረ ቢሆንም፣ የሰላሙ ሁኔታ ግን ከወዲሁ የጨለመ መሆኑን ተነግሯል፡፡


ፕሬዚዳንት ባይደንም መግለጫውን ከሰጡ በኋላ በአርሊንግተን ቨርጂኒያ በሚገኘው ብሄራዊ የጀግኖች መካነ መቃብር ላይ በመገኘት በጦርነቱ የተሰውትን አሜሪካውያን ወታደሮች አስበዋል፡፡


(የዋይት ሀውስ ዘጋቢ ፓትሲ ውዳክስዋራ ካሰናዳችው ዘገባ የተወሰደ፡፡)

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-afaghanistan-biden-4-15-21/5854462.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-afaghanistan-biden-4-15-21/5854462.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 15 Apr 2021 19:47:41 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/us-afaghanistan-biden-4-15-21/5854462.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/F93E58DA-43FD-447F-843D-5C54CDF26C5B_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ህግ አውጭዎቹ የ2 ትሪሊዮን ዶላር እቅዱን ሊነጋገሩበት ነው</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ ህግ አውጭዎች በዚህ ሳምንት ወደ ዋሽንግተን ይመለሳሉ፡፡ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ያቀረቡት የ2 ትሪሊዮን ዶላር መሰረት ልማት በጀትም ቀዳሚ አጀንዳቸው እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡


ፕሪዚዳንት ጆ ባይደን በዚህ ሳምንት ከዴሞክራትና ሪፐብሊካን የጋሪዮሽ ኮሚቴዎች ጋር ተገናኝተው የአገሪቱ መንገዶችና ድልድዮች የሚሻሻሉበት፣ ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት ፈጣን የባቡር መስመሮች በሚዘረጉበትና በሌሎች የመሰረት ልማት ጥቅል እቅዳቸው ላይ ይነጋገራሉ፡፡


ባይደን ይህን ሲያደርጉ የሚገጥማቸው፣ በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ፣ በከኮቪድ 19 የተጎዳውን ኢኮኖሚ ለመታደግ ከጠየቁት የ1.9 ትሪሊዮን ዶላር እርዳታ ጋር ተመሳሳይ ሁኔታ ነው፡፡


ከሪፐብሊካን ፓርቲ አባላት ጋር መሰረት ልማት ሲባል ምን ምን ነገሮችን እንደሚይዝና ገንዘቡ ከየት ከየት መጥቶ እንደሚከፈል መተማመን ይጠበቅባቸዋል? ወይስ የዴሞክራቶቹን ድጋፍ ብቻ አግኘተው ወደፊት መጓዝ ይኖርባቸዋል? የሚለውም አጠያያቂ ነው፡፡


ምክንያቱም 100 አባላት ያሉት የመወሰኛው ምክር ቤት፣ 50 ዴሞክራቶች እና 50 ሪፐብሊካን የተከፈሉበት ሲሆን፣ አብላጫውን ድምጽ ለማግኘት የምክትል ፕሬዚዳንቷ ከማላ ኻሪስን ገላጋይ ድምጽ ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡


እስካሁን ባይደን የመረጡት የሁለቱንም ፓርቲዎች የጋራ ድጋፍ ማግኘቱን ነው፡፡


የዩናይትድ ስቴት የኃይል ምንጭ ሚኒስትር ጄኒፈር ግራንሆልም በኤቢሲ ቴሊቪዥን ላይ የባይደን ምርጫ ምን እንደሆነ እንደሚከተለው አብራርተዋል፡፤


“ እንደሚመስለው ፕሬዝዳንት ባይደን ለመደራደር ዝግጁ ናቸው፡፡ አሁን ያለው እቅድ እንደሚለወጥ ይገነዘባሉ፡፡ ይህ ሁሉንም ነገር ተደራድረህ እምትወስነበት አገር ነው፡፡ ያቀረቡት አንድ ጥቅል ጉዳይም ይሁን ዝርዝር ጉዳይ ከሪፐብሊካን አባላት ጋር መነጋገር ይፈልጋሉ፡፡”


የሪፐብሊካን መሪዎች ከወዲሁ ጥቅል እቅዱ እጅግ ከፍተኛ ገንዘብን የሚጠይቅ ነው በማለት ተቃውሞቸውን ማሰማት ጀምረዋል፡፡ ባይደን እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ የገንዘብ ምንጭ አድርገው ያቀረቡትንም መንገድ አልተቀበሉትም፡፡


ባይደን በትላልቆቹ የንግድ ኩባን ያዎች ላይ አሁን ያለውን የ21 ከመቶ ቀረጥ በመጨመር ወደ 28 ከመቶ ለማሳደግ ያሰቡትንም ተቃውመዋል፡፡


ይህ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከአራት ዓመት በፊት ከንግድ ድርጅቶቹ ላይ ያነሱትን ቀረጥ በከፊል ሊሽር ይችላል፡፡


ሪፐብሊካኖች ከፕሬዚደንት ባይደን ጋር ድርድሩን ማድረግ የሚፈልጉ ሲሆን ኢኮኖሚውን ከኮቪድ ወረርሽኙን ለመታደግ ከተላለፈው የኢኮኖሚው ጥቅል በጀት ወቅት ከነበረው የተሻለ ድርድር ለማድረግ ፍላጎቱ አላቸው፡፡




ከሚሲስፒ ግዛት የሪፐብሊካን አባል ተወካይ የሆኑት ሴነተር ሮጀር ዊከር ለኤቢሲ ቴሌቪዥን የሚከተለውን ብለዋል


“በመሰረት ልማቱ ጥቅል እቅድ ላይ ከሳቸው ጋር መደራደር እንፈልጋለን፡፡ ይህ ትሪሊዮን ዶላር ለኔ እጅግ በጣም ብዙ ነው፡፡ ያን ልነግርህ እፈልጋለሁ፡፡ ድርድር ሲባል ግን ልናድነው ከምንፈልገው እቅድ የተለየ ነገር መሆን አለበት፡፡ “


የአሜሪካ የሲቪል ኢንጂነሪን ማህበረሰብ አባላት በቅርቡ ባወጡት ሪፖርት፣ ለአሜሪካ የመሰረተ ልማት የሰጡት ደረጃ፣ የሲ ማይነስ ደረጃ መሆኑም ተመልከቷል፡፡


የኢንጂነሮቹ ቡድን ለዓመታት ተዘንግተው የቆዩት መንገዶችና ድልድዮች የተበለሻሹ ሲሆን፣ አውሮፕላን ማረፊያዎች የውሃና የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ጥገናን የሚጠይቁ ናቸው ብለዋል፡፡


የቪኦኤ ዘጋቢ ሚሸል ኲዪን ካሰናዳችው ዘገባ የተወሰደ፡፡


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-ahead-4-12-21/5850139.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-ahead-4-12-21/5850139.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 12 Apr 2021 21:00:58 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-ahead-4-12-21/5850139.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/EDDA9324-E46B-4F68-9F31-E87924DF101F_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ባይደን ከሚያዝያ 11 ጀምሮ &quot;ሁሉም አዋቂዎች መከተብ ይችላሉ&quot; አሉ</title>
            <description>ዩናይትድ ስቴትስ በያዝነው የሚያዝያ ወር መገባዳጃ ላይ 200 ሚሊዮን አሜሪካውያንን ለማስከተብ ያስቀመጠቸውን ግብ ለማሳከት ተቃርባለች፡፡ የፕሬዚዳንት ባይደን አስተዳደርም በመላው ዓለም ያለውን የኮቪድ 19 ወረርሽን ለመከላከልና ሌሎች አገሮችን የሚያግዝ አስተባባሪ በመሰየም ተጨማሪዎች እምጃዎችን እየወሰዱ ነው፡፡ 


በዚህ ወር እኤአ ሚያዝያ 19 ወይም በኢትዮጵያ ሚያዝያ 11 ላይ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የሚገኙ አዋቂዎች በሙሉ ከትባቱን መውሰድ እንደሚችሉ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አስታውቀዋል፡፡


ይህ ቀደም ሲል ከተቀመጠው የግንቦት 1 ቀነ ገደብ በሁለት ሳምንት አስቀድሞ የመጣ ነው፡፡ አሁን ስላለው የክትባት ሁኔታ ፕሬዚዳንት ባይደን ይህን ብለዋል


&quot;አሁን በየቀኑ በአማካይ 3 ሚሊዮን ክትባቶችን እየሰጠን ነው፡፡ በሳምንት ከ20 ሚሊዮን በላይ ይሆናል፡፡ ቅዳሜ እለት ብቻ ከ4 ሚሊዮን በላይ ክትባቶችን ሰጥተናል፡፡ ከ62 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ሰዎች 150 ሚሊዮን ክትባቶችን በመሰጥት የመጀመሪያዎቹ አገሮች ነን፡፡&quot;


ክትባቶቹን ለማግኘት ሲባል ከሌሎች አገሮች ከመጣው ግፊት የተነሳ ፕሬዚዳንት ባይደን በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ዓለም አቀፉን የኮቪድ 19ን ለመመከት የሚደረገውን ሥራ እንዲያቀናጁ ጌይል ስሚዝን ሾመዋል፡፡


ስሚዝ የዓለም አቀፍ የጤና ኤክስፐርት ሲሆኑ በትርፍነት የተመረቱ ክትባቶች ለሌላው ዓለም እንዲላኩ የሚሟገቱ ናቸው፡፡ እሳቸውም ስለዚሁ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ


&quot;የአሜሪካ አመራር በጣም ተፈላጊ ነው ይህንንም እንደምናሟላ በጣም እርግጠኛ ነኝ፡፡&quot;


አነስተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸው አገሮች ቻይና ስሪት የሆኑ ክትባቶችንና ከተባባሩት መንግሥታት የጋራ ክትባት መርሃ ግብር ውስጥ ካለው ኮቫክስ የመጡ ክትባቶችን እየወሰዱ ነው፡፡


ባለሙያዎች ደግሞ ዩናይትድ ስቴትስ ትርፍ የሆኑ ክትባቶችን ከመላክም ያለፈ ሥራ መሥራት እንደምትችል ይናገራሉ፡፡ 


በዓለም አቀፉ ስትራቴጂና ጥናቶች የጤና ፖሊሲ ማዕከል ዳይሬክተር የሆኑት ጄ ስቴፈን ሞሪሰን እንዲህ ይላሉ


&quot;የክትባቱ ምርት በታቀደው መሠረት እንዲጨምር ይረዳሉ፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃም፣ አሁን ያለውን፣ ተጠያቂነት በጎደለው መንገድ በድብቅና በቀውስ የተሞላውን የክትባቱን ስርጭት አሰመልከቶ ግልጽነት እንዲኖረው ያደርጋል፡፡&quot;


ባለፈው ማክሰኞ ፕሬዚዳንት ባይደን ቨርጂኒያ ግዛት በሚገኘው ቻፕል ውስጥ የሚገኘውን የክትባት መስጫ ጎብኝተዋል፡፡ አሰተዳደራቸውም ክትባቱን ለመውሰድ የሚያቅማሙትን ለማግባባት ከእምነት እና ማህበረሰባዊ ተቋማት ጋር የተጣመረ ህብረት መስርቷል፡፡


የህዝብ አስተያየት መቀበያ ድምጽ እንዳረጋገጠው ክትባቱን ላለመውሰድ የሚያቅማሙት ወደ 20 ከመቶ ይደርሳሉ፡፡




አሜሪካውያን የጤና መመሪያውን የሚጥሱ አሜሪካውያን እየጨመሩ መሆኑን የተነገረ ሲሆን በዚህ ሳምንት በተጀመረው የኮሌጅ ቅርጫት ኳስ ጨዋታዎቹ ብዙዎቹ ተገኝተዋል፡፡


ከቨንደር ቢልት ዩኒቨርስቲ የህክምና ክፍለ ትምህርት ዊሊያም ሻፍነር እንዲህ ይላሉ


&quot;በየቀኑ በቫይረሱ የተያዙ ከ60 ሺ በላይ አዳዲስ ሰዎችን እየተመዘገቡ ነው፡፡ አዋቂ ወጣቶችም ዋነኞቹ የቫይረሱ አስተላላፊዎች ሆነዋል፡፡ ወደ ስፖርት ማዘውተሪያዎች ይሄዳሉ፡፡ ወደ ምግብ ቤቶችና መጠጥ ቤቶችም እየሄዱ ነው፡፡&quot; 


ዋይት ሐውስ እንደሚለው በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ 40 ከመቶ የሚሆኑን አዋቂዎች ቢያንስ አንደኛውን ዙር ክትባት ወስደዋል፡፡ 20 ከመቶ የሚሆኑ ዜጎችም ሙሉ ለሙሉ ተከትበዋል፡፡


(የዋይትሐውስ ዘጋቢ ፓትሲ ውዳክስዋራ ከላከቸው ዘገባ የተወሰደ፡፡) 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-biden-vaccines-4-7-2021/5844307.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-biden-vaccines-4-7-2021/5844307.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 07 Apr 2021 20:06:41 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>ኮሮናቫይረስ/ኮቪድ-19</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/us-biden-vaccines-4-7-2021/5844307.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/7F45B90E-70F7-4BD5-B83B-729A52B9BB8B_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በፍሎይድ ሞት የተከሰሱት የቀድሞ ፖሊስ “ደንብ ጥሰዋል” ተባለ</title>
            <description>ባለፈው ዓመት በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዳለ ህይወቱ ባለፈው ጥቁር አሜሪካዊ ጆርጅ ፍሎይድ ህልፈት በተከሰሱት የቀድሞ ፖሊስ መኮንን ዴሪክ ሻቭን ላይ ክስ የመሰረቱት አቃቢ ህጎች የክሶቻቸውን ጭብጥና ክርክር ለችሎቱ ማሰማት ከጀመሩ ትናንት ሰኞ ሁለተኛ ሳምንቱ ተቆጥሯል፡፡


የምኒያፖሊሱ የፖሊስ ዋና አዛዥ ትናንት ሰኞ ከህዝብ ለተውጣጡ ዳኞች ወይም ጁሪዎች እንዳስታወቁት የቀድሞ የፖሊስ መኮንን ዴሪክ ሻቭን ጆርጅ ፍሎይድን በቁጥጥር ስር ሲያውሉ የፈጸሙት ነገር “የፖሊስ መምሪያውን አያያዝ ደንብ የተከተለ አይደለም” በማለት ተናግረዋል፡፡


 የፖሊስ አዛዡ የፖሊስ መኮንኑ ለመጀመሪያዎቹ ጥቂት ሰክንዶች ሟችን በቁጥጥር ስር ለማድረግ የተጠቀመበት መንገድ አግባብነት ያለው ነው ካሉ በኋላ፣ “ይሁን እንጂ ሚስተር ፎሎይድ ምንም ተቃውሞ ማሳየት ቀርቶ መንቀሳቀስ እንኳ ባቆሙበት ሰዓት፣ እንደዚያ ያለውን የኃይል መጠን፣ መጠቀሙን መቀጠል፣ በየትኛም መንገድ ቢሆን መመሪያችንም ሥልጠናችንም፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ የሥነምግባርና ሞራላችንም የሚፈቅደው ነገር አይደለም፡፡” ብለዋል፡፡


ሻቭን የተከሰሱት በጆርጅ ፍሎይድ አንገት ላይ ጉልበታቸውን ከ9 ደቂቃዎች በላይ በመጫን፣ ወይም በማነቅ ለፎልይድ ህይወት መጥፋት ምክንያት ሆነዋል ተብለው ነው፡፡


በትናንትው እለት ዳኞቹም ሲያደምጡ የዋሉት አንገትን ስለማነቅና ስለመታፈን ክርክር ነው፡፡ 


የሜኒሶታ ፖሊስ ዋና አዛዥ ሜዳሪያ አረዶንዶ እንዲህ ይላሉ


“በፖሊስ አያያዝ የተጠቀሰው አንገትን የማነቅ ሁኔታ ጥንቃቄ በተሞላበት ከቀላል እስከ መካከለኛ ጫና ማሳደር ድረስ የሚሄድ ነው፡፡ በኤግዚቢት 17 ላይ በማስረጃነት የቀረበውን የጆርጅ ፍሎይድ የፊት አገላለጽ ሁኔታ ስመለከት የተደረገው በየትኛው መንገድ ወይም ቅርጽ ከቀላል እስከ መካከለኛ ድረስ ያለውን ጫና አይመስልም፡፡”


የህክምና ባለሙያዎች የፍሎይድ ልብ ሆስፒታል ከመድረሱ በፊት የቆመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እኤአ ግንቦት 25/ 2020 በሆስፒታሉ አስቸኳይ ህሙማን መቀበያ ክፍል ፍሎይድን የተቀበሉት ዶክተር ለዳኞቹ እንደተናገሩት ፍሎይድን ለህልፈት ያበቃው የኦክስጂን እጥረት ነው፡፡ 






ከሄንፕን ካውንቲ ሜዲካል ሴንተር በዐቃቢ ህጉ ፍሎይድ ህይወቱ ያለፈው “በኦክሲጅን እጥረት ሳቢያ ልቡ ደም መርጨት በማቆሙ ነው ?” ተብለው የተጠየቁት ዶ/ር ብራድፍሮድ እንዲህ ብለዋል


“ያ በጣም ሊሆኑ ከሚችሉ ነገሮች መካከል አንዱ ነው፡፡ ከሌሎቹ ይልቅ በዚያ ሰዐት በነበረኝ መረጃ መሰረት የተሰማኝ ነገር ቢኖር ያ መሆኑ ነው፡፡”


በኦክስጅን ወይም ትንፋሽ እጥረት ምክንያት የሚከሰትን ሞት የምትጠሩበት ሌላ መጠሪያ አላችሁ ተብለው በአቃቢ ህጉ የተጠየቁት ዶ/ር ብራድፎርድ፣ “አስፓያክሲያ” የሚለው ቃል የተለመደው አገላለጽ ነው በማለት መልሰዋል፡፡


የተከላካይ ጠበቆች ግን ፍሎይድ የሞተው ከዚህ ባልተገናኘ ሌላ የጤንነት ጉድለት እንዲሁም ከአደገኛ መድሃኒትና እጽ ጋር የተያያዘ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ ለዚህም ፈንታሊን እና ሜታፈታማይን የተባሉ አደገኛ መድሃኒትና ህጾች በፍሎይድ ሰውነት ውስጥ የነበሩ መሆኑን ይናገራሉ፡፡


የዴሪክ ሻቭን ጠበቃ ኤሪክ ኒልሰን ይህንኑ መሠረት በማድረግ በምስክርነት ለቀረቡት ዶ/ር ብራድሮድ ጥያቄዎችን አቅርበዋል


“ስለዚህ ሃይፓክሲያ የሚባለው፣ በደም ውስጥ በቂ ኦክሲጅን እንዳይዘዋወር፣ ሰውነት ሥራውን በብቃት እንዳይሰራ፣ የሚያደርጉ ምክንያቶች፣ እንደ መታፈን ወይም አስፋይክሴሽን ተደርገው የሚወሰዱ በርካቶች አይደሉም?


ሀኪሙ “አዎ ትክክል” በማለት መለሱ ፡፡


የተከላካዩ ጠበቃ አሁንም ሌላ ጥያቄ አቀረቡ


“ይህን በሰውነት ኦክሲጂን እንዳይኖር የሚያደርጉ የተለያዩ አደገኛ መድሃኒቶችና ህጾችም አሉ አይደለም?”


አሁንም ሀኪሙ “አዎ” አሉ ደግመው፡፡


ባለፈው ዓመት ህይወቱ ያለፈው ጆርጅ ፍሎይድ የፖሊሶችን ስልጠና ዓላማና ድርጊት “የጥቁርም ህይወት ዋጋ አለው” በሚል የተነሳውን ተቃውሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲቀጣጠል ማድረጉ ይታወሳል፡፡


የቪኦኤ ዘጋቢ ኢሻ ሳራዬ ካጠናቀረችው ዘገባ የተወሰደ፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/floyed-officer-trial/5843106.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/floyed-officer-trial/5843106.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 06 Apr 2021 22:56:42 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/floyed-officer-trial/5843106.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/96b911ce-af99-466a-a84f-5f641215b725_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የፕሬዚዳንት ባይደን የ2 ትሪሊዮን ዶላር መሠረት ልማት በጀት </title>
            <description>ፕሬዚደንት ጆ ባይደን የአገሪቱን መንገዶች፣ ድልድዮችና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን ለማዘመን፣ በቅርቡ የ2 ትሪሊዮን ዶላር በጀት ለመመደብ ማቀዳቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ ይሁን እንጂ እቅዱ በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤቶች መሰናክሎች ሊገጥሙት እንደሚችሉ ይጠበቃል፡፡


ፕሬዚዳንት ባይደን የመሰረተ ልማት እቅዱን ያቀረቡት አንድ መሠረተ ልማት ሊኖረው የሚገባውን ሁለተናዊ እቅድ መሠረት አድርገው ነው፡፡ መንገዶችንና ድልዮችን መጠጋገን ብቻ ሳይሆን የብሮድ ባንድ የኢንተርኔት አገልግሎት ቴክኖሎጂን የመገንባትና፣ የአየር ንብረት ለውጡን ተከትለው ያሉ ችግሮችን ለማሻሻል ጭምር ነው፡፡


የትራንስፖርት ሚኒስትሩ ፒት ቡትጂጅ በኤቢሲ ቴሌቪዥን “ዚስ ዊክ” በተባለው ፕሮግራም ላይ ሲናገሩ ይህን ብለዋል


“በእኔ አመለካከት፣ ይህ በህይወት ዘመን አንዴ የሚገጥም ነገር ነው፡፡ በሚቀጥሉት 50 ዓመታት ውስጥ በእንዲህ ያለ ቅንጅት የተገለጸ፣ ሁለቱም ፓርቲዎች የጋራ ፍላጎት የታየበት፣ ይህን አስመልከቶ ያለው ትእግስት በስፋት የተሟጠጠበት፣ ይህንንም ጉዳይ በጣም የሚደግፉና ቁርጠኝነት ያሳዩ ፕሬዚዳንት ያሉበት ጊዜ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ይህ በመሰረተ ልማት ጉዳዮች ላይ ብቻ አይደለም በሌሎች ልንፈጥራቸው ባሰብናቸው የሥራ እድሎችም ጭምር ነው፡፡”


በእቅዱ ውስጥ የተካተተው የሥራ እድል ፈጠራ በአገሪቱ የንጹህ ኃይል አቅርቦትን ለመገንባትና ይህንንም የሚንከባከቡ ባለሙያዎችን ቁጥር ከፍ ለማድረግ የታለመ ነው፡፡


የሪፐብሊካን መሪዎች እቅዱ በጣም ትልቅ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ጥቅል እቅዱ እኤአ በ2030 ዓም ድረስ 500ሺ የኤሌክትሪክ ተሸርካሪዎች፣ የኃይል ምንጭ የሚያገኙባቸውን ኃይል መስጫ ጣቢያዎች ለማቋቋም ነው፡፡ 


ሪፐብሊካኑ ሴነተር ሮይ ብለንት በኤቢሲ ቴሊቪዥን ላይ ይህን ብለዋል


“ሰዎች ስለመሠረተ ልማት ሲያስቡ የሚያስቡት ስለመንገድ፣ ድልድዮች፣ ወደቦች እና የአውሮፕላን ማረፊያዎች ነው፡፡ የመሠረት ልማት እቅድ ሲሉ ያንን አነስተኛ እቅድ ነው የመሰረተ ልማት እቅድ ብለው የሚጠሩት፡፡”


“ለእቅዱ የሚሆነው ወጭ አሸፋፈን ጉዳይ ራሱ አንዱ መነጋገሪያ ነው፡፡ ጥቅል እቅዱ በትላልቅ የንግድ ድርጅቶች ላይ ተጨማሪ ቀረጥ መጣልን በምንጭነት ያነሳል፡፡ ሪፐብሊካኖች ግን ይህን ይቃወማሉ፡፡”






የእቅዱ ረቂቅ በዴሞክራቶች መሪነት ለምክር ቤቱ የቀረበ ሲሆን በሚቀጥሉት ወራት ውስጥ ጸድቆ ለፕሬዚዳንቱ ፊርማ እንዲቀርብ የታለመ መሆኑም ተመልከቷል፡፡ በጥቅል እቅዱ መጽደቅ የዴሞክራቲክ ፓርቲ አባላት ህብረት ይፈተንበታል፡፡ ፕሬዚዳንት ባይደን የሪፐብሊካንን አባላት ድጋፍ የማያገኙ ከሆነ፣ በተለይ እኩል በእኩል ያህል በተከፈለው የህግ መወሰኛው ምክር ቤት ውስጥ የሚገኙትን የሁሉም ዴሞክራቶችን ድምጽ የግድ ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡


የቪኦኤ ዘጋቢ ሚሸል ኩዪን ካሰናዳችው ዘገባ የተወሰደ፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-4-5-16/5841592.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-4-5-16/5841592.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 05 Apr 2021 22:48:46 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-4-5-16/5841592.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/DDD97A8E-546B-48FD-8FEA-93B10BE794B7_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ባይደን ስለ ስደተኞች አፍጋኒስታን ቻይናና ሰሜን ኮሪያ ተናገሩ</title>
            <description>ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ሥልጣን ከያዙ በኋ ላ ለመጀመሪያ ጊዜ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫቸው፣ በዩናይትድ ስቴትስና ሜክሲኮ ድንበር በኩል፣ ቁጥራቸው እየጨመረ የመጣውን ስደተኞችና ፣ አሜሪካ ወታደሮችዋን ከአፍጋኒስታን ለማውጣት ያስቀመጠቸውን፣ እኤአ ግንቦት 1 ቀነ ገደብ የማትጠብቅ መሆኑን ማስታወቋን አስመልከቶ፣ ከጋዜጠኞች ጠንከር ያሉ ጥያቄዎች ቀርበውላቸዋል፡፡ 


ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ የመጀመሪያቸው በሆነው ጋዜጣዊ መግለጫቸው አብይ መነጋገሪያ የነበረው የስደተኞች ጉዳይ ነበር፡፡


ፕሬዚዳንት ባይደን በጉዳዩ ላይ ያላቸው አቋም የተለሳለሰ ነው የሚለውን ምልከታ አልተቀበሉትም፡፡


በሜክሲኮ በኩል ወደ አሜሪካ የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር ግን እየጨመረ መጥቷል፡፡ ስለዚሁ ሁኔታ ሲናገሩ ባይደን እንዲህ ብለዋል


“የሚመጡት እኮ ለዚህ ነው ምክንያቱም ባይደን መልካም ሰው እንደሆነ ያውቃሉዋ!! ያለው እውነት ግን የተለወጠ ነገር የለም፡፡ ብዙ ሰዎች የመምጣታቸውን ያህል በኔ አስተዳደር በድንበር በኩል የመጡት ስደተኞች ቁጥር በ28 ከመቶ ሲጨምር፣ ከኮቪድ ወረርሽኝ በፊት በነበረው የ2019 ዓም የትራምፕ አስተዳደር ጊዜ 31 ከመቶ ነበር የጨመረው፡፡” 


በዚህ ሳምንት መጨረሻ ላይ ባይደን የስደተኞቹ ቁጥር የጨመረበትን ትክክለኛ ምክንያት እንዲከታተሉ ምክትል ፕሬዚዳንት ከማላ ኻሪስን ሰይመዋል፡፡


የውጭ ግንኙነቱን አስመልከቶ ዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮችዋን ከአፍጋኒስታን ለማውጣት ያስቀመጠችውን የ እኤአ ግ ንቦት 1 ቀነ ገደብ ማክበር እንደማትችል አስታውቀዋል፡፡ በምትኩም ያስቀመጡት ወይም የጠቀሱት ቀን የለም፡፡ ብዙ አለመቆየታቸውን በመግለጽ ይህን ብለዋል


“እንዴትና በምን ሁኔታ ውስጥ ሆነን ነው ፣ ቀድሞውኑም እንደዚያ ያለ የአወጣጥ ስምምነት ውስጥ እንዴት ተገባ በሚያሰኝ ሁኔታ በፕሬዚዳንት ትራምፕ የተደረገውን ስምምነት ማስፈጸም የምንችለው? ለማንኛውም ግን ብዙ አንቆይም፡፡


አፍጋኒስታን ውስጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየጨመረ ከመጣው ግጭት አንጻር መግለጫው አንዳንዶቹን ታዛቢዎች አላስደነቀም፡፡ ከ እነዚህ መካከል የዓለም አቀፍ ጉዳዮችና የስትራቴጂ ተቋም ውስጥ፣ የዓለማ አቀፋዊ ግጭቶች ባለሙያው የሆኑት አንተኒ ካርድስማን አንዱ ናቸው ፡፡ እንዲህ ይላሉ

“ያለው ተጨባጭ ሁኔታ የፕሬዚዳንት ባይደን አስተዳደር ሥልጣኑን በተረከበበት ወቅት ጭራሽ የተባባሰውን ግጭት አስወግዶ ውጊያውን በማቆምም ሆነ የሰላም ሂደቱን ገጽታ የሚያመላከት አንዳች ነገር ለማስመዝገብ ያደረግነው ምንም ነገር የለም፡፡” 


የዩናይትድ ስቴትሱ መሪ ባይደን፣ ሰሜን ኮሪያ በቅርቡ በምስራቃዊ የአገሪቷ ግዛት በኩል፣ ሁለት የቅርብ ርቀት ተወንጫፊ የባለስቲክ ሚሳኤሎችን ማስወንጨፏን የተባበሩት መንግሥታት ውሳኔዎች የጣሰ ነው ብለውታል፡፡ አስከትለውም፦


“ይህን ነገር ማባባሱን ከመረጡ ምላሽ ሊኖር ይችላል፡፡ አጸፋውን እንዳመጣጡ እንመልሳለን፡፡ ይሁን እንጂ ግን የተወሰነ መልክ ላለው ዲፕሎማሲም ተዘጋጅቻለሁ፡፡”






ፕሬዚዳንት ባይደን እንዲሁም የቻይናው አቻቸው ዚ ጄፒንግ ዓለም አቀፍ ህግ ጋትን እንዲያከበሩ ከአጋሮቻቸው ጋር ሆነው ግፊት እንደሚያደርጉ ተናግረው ይህን ብለዋል፡፡


“በተለያዩ በርካታ አጋጣሚዎች ግጭት የማንፈልግ መሆኑን ለራሳቸው በግል ነግሬያቸዋለሁ፡፡ ምን እንኳ ጠመዝማዛና አስቸጋሪ ውድድር መኖሩን ብናውቅም ማለት ነው፡፡”


የዓለም አቀፋዊ ግጭቶች ባለሙያው የሆኑት አንተኒ ካርድስማን ቻይናን አስመልክቶ የተለወጠ ነገር መኖሩን ሲገልጹ እንዲህ ብለዋል


“ቻይናን አስመልከቶ ያለው ንግግር ትኩረቱን እየቀየረ የመጣ ይመስለኛል፣ ከንግድና በወታደራዊ ግጭቶች ፍጥጫ በመራቅ ከቻይና ጋር መወዳደር ወደሚያስችል ግንኙነቶች ላይ ያተኮረ ይመስለኛል፡፡”


በጋዜጣው መግለጫው ላይ ለአንድ ሰዓት ያህል የቆዩት ፣ ፕሬዛዳንት ባይደን በመጀመሪያዎቹ የሥልጣን ዘመናቸው 100 ቀናት ውስጥ 200 ሚሊዮን የሚደርሱ የኮቪድ 19 ክትባቶችን በየሰው ክንድ ላይ እንደሚያሳርፉ ተናግረዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ2024 ምክትል ፕሬዚዳንት ከማላ ኻሪስን አስከትለው በድጋሚ እንደሚወዳደሩም ይጠበቃል፡፡


መግለጫውን የተከታተለችው የቪኦኤ የዋይት ሐውስ ዘጋቢ ፓትሲ ውዳክስዋራ ከዘገበችው የተወሰደ፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/us-Biden-press-conference--3-26-2021/5829898.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/us-Biden-press-conference--3-26-2021/5829898.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 26 Mar 2021 20:57:36 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/us-Biden-press-conference--3-26-2021/5829898.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/76706c01-648e-47a7-a960-6f26a2165a24_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኔቶ ስብሰባ አሜሪካ አጋርነቷን ዳግም ስታጠናክር ቻይናና ሩሲያ ዋና አጀንዳ ነበሩ</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን አሜሪካ ከአትላንቲክ ባሻገር ካሉት አገሮች ጋር ያላትን ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር እንደምትፈልግ በመግለጽ፣ አገራቸው ከሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን አገሮች ድርጅት (ኔቶ) ጋር ያላትን ህብረት ዳግም እንደምታድስ፣ ብራስልስ ውስጥ ለሁለት ቀናት በተካሄደውና ትናንት ረቡዕ በተጠናቀቀው ስብሰባ ላይ አረጋግጠዋል፡፡


የቪኦኤ ዘጋቢ ኼንሪ ሪጅዌል ከሥራፍው እንደገዘገበው፣ ስብሰባው በቻይና በኩል እየተባባሰ መጥቷል ያለውን አደጋ ጨምሮ በሌሎች በርካታ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ተነጋጋሯል፡፡ 


ዛሬ ከአትላንቲን ባሻገር ባለው ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ ተገልጧል፡፡ ከአራት ዓመታት በፊት የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን አገሮች ድርጅት ወይም ኔቶን “ጊዜው ያለፈበት” ብለውት ነበር፡፡ 


የዛሬው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊነክን ግን ከቃልኪዳን አባል አገራቱ ጋር ያላቸው ግንኙነት በድጋሚ እንዲታደስ ጥረት ሲያደርጉ ታይተዋል፡፡ 


እንዲህ አሉ ብሊንከን 


የማይናወጠው ቃል ኪዳናችን አብሯችሁ ነው፡፡ አሜሪካ ለኔቶ ሙሉ ለሙሉ ቁርጠኛ የሆነ አቋም አላት፡፡


ብሊንከን የቃል ኪዳን አባል አገሮች ህብረቱን ወይም ኔቶን ስለገጠመው ወታደራዊ ስጋት እንዲህ ብለዋል


“የቤጂንግ ወታደራዊ ፍላጎት በየዓመቱ እያደገ ነው፡፡ ይህም ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ እድገት ጋር የተጣመረ ሲሆን ዛሬ እንደምታውቁት ድሮ የዓለም ግማሽ ክፍል ያህል ሩቅ ይመስሉ የነበሩት አገሮች ዛሬ ሩቅ አይደሉም፡፡ በራሽያ በኩልም እንዲሁ የአባል አገሮቹን ለመፈታተን እና፣ የጋራ ደህንነታችንን የሚያረጋግጠውን መርህ በመተላለፍ ወታደራዊ አቅምን የማሳደግ አዲስ ስትራቴጂ መኖሩን ተመልክተናል፡፡”






የኔቶ ዋና ጸሀፊ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ህብረቱ ላይ የተደቀነውን አደጋ በመግልጽና ከህበረቱም ጎን ለመቆም ያሳያቸውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል፡፡


ራሽያ አለመረጋጋትን የሚፈጥሩ አዳዲስ የኒዩክየር ጦር መሳሪያዎችን ማሰማራቷን ቀጥላለች፡፡ ስለዚህ ስለ ብዙ የጦር መሳሪያዎችም ሆነ እንደ ቻይና ያሉ አገሮችን አስመልከቶ አንድ ስምምነት ማድረግ ይኖርብናል፡፡ 


ከአውሮፓ ህብረት የደህንነት ተቋማት ጥናት ማዕክለ ሲሞና ሶአሬ፣ ቻይና በኔቶ አባል አገራት ላይ፣ አንጻራዊ የሆነ አዲስ ፈተና መደቀኗን ይገልጻሉ፡፡


“ይህ የኔቶ ወደ ህንድና ፓስፊክ አገሮች የመቀንሳቀስ ጉዳይ አይደለም፡፡ ይልቁንም የቻይና በአውሮፓ ውስጥ መኖርና እያሳደረች የመጣችውን ተጽእኖ አሉታዊ ጎን ማወቅና እሱን የመቋቋም ጉዳይ ነው፡፡ ይህ ማለት በእርግጥ፣ ወሳኝ የሆኑ የቴክኖሎጂና የመሠረተ ልማቶችን ዒላማ ያደረገውን የውጭውን ቀጥታ ኢንቨስትመንት በበለጠ የመረዳት ነገር ነው፡፡”


ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አንተኒ ብሊንከን አሁንም ቢሆን የአውሮፓ ህብረት አጋሮች የመከላከያ ወጭያቸውን እንዲጋሩ ይጠይቃሉ፡፡ ብሊንከን ኔቶ አዲስ እየተደቀነ ያለውን አደጋ መልሶ ለመቋቋም ጠንክሮ መውጣት አለበት፡፡ ካሉ በኋላ ይህ ደግሞ የተዛባ መረጃ መርጨትን፣ የሳይበር ጥቃትን፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የኮረና ቫይረስ ወረርሽኝን ይጨምራል ብለዋል፡፡


በአፍጋኒስታን ያለው የኔቶ ተልእኮም ተነስቷል፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ ጦር እኤአ ከግንቦት 1 ቀን ጀምሮ አካባቢውን ለቆ እንዲወጣ ከታሊባን ጋር ስምምነት ተደርጓል፡፡፡ ብሊነክን ይህ ስምምነት እየተጠና መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አስማሚ የሆኑ ንግግሮች የተሰሙ ቢሆንም ውስጣዊ ውጥረቶች በኔቶ ውስጥ መኖራቸውም ተመልክቷል፡፡ ብሊንከ ቱርክ ከራሽያ የገዛችውን ኤስ 400 የመከላከያ መሳሪያ ግዥ እንድታቋርጥ አሳስበዋል፡፡ ቱርክ ግን ስምምነቱ መጠናቀቁን ገልጻለች፡፡


ዩናይትድ ስቴትስ ከራሺያ ጀርመን ድረስ የተዘረጋውንና ኖርደ ስትሪም 2 የተሰኘውን የጋዝ ማስተላለፊያ መስመር፣ በግልጽ የምትቃወም መሆኑን ብሊንከን ተናግረዋል፡፡ 

ቻይና ላይ የተሰነዘሩ በርካታ አሉታዊ ነገሮች ቢኖሩም የአውሮፓ ህብረት ግን ከቤጂንግ ጋር የሚያደርገውን የንግድ ስምምነት እያጠናቀቀ ነው፡፡ ብሊንከን ይህን አስመልከቶ ሲናገሩ


“አጋሮቻችን ከቻያና ጋር ያላቸው ግንኙነት የተወሳሰበ መሆኑንና ሁሌም ፍጹም የተሟላና የተሳካ አለመሆኑ ይገባናል፡፡ ይሁን እንጂ ግን ይህን ፈተና በጋራ እምንወጣበትን መንገድ ማግኘት ይኖርብናል፡፡ ስለዚህ ከአጋሮቻችን ጋር አብረን እየሰራን ቻይና አጋጣሚውን እየተጠቀመች ጫና የምታሳድርባቸውን የቴክኖሎጂና የመሠረተ ልማት ግንባታ ዘርፎች ላይ ያለውን ክፍተት መሙላት ይኖርብናል፡፡


በትናንትናው እለት ከአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር የተገናኙት ብሊከን “ የአውሮፓ ህብረት ለዩናይትድ ስቴትስ ቀዳሚው አጋር ነው” ብለው መናገራቸው ከፍተኛ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ይሁን እንጂ ተንታኞች እንደሚሉት ከአትላንቲክ ባሻገር ካሉ አገሮች ጋር ያለው አዲሱ ወዳጅነት፣ ህብረቱን የሚገጥሙት ዘርፈ ብዙ ፈተናዎች ከፊቱ ተደቅነውበታል፡፡ 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/blinken-nato-wrap-2-25-2021/5828450.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/blinken-nato-wrap-2-25-2021/5828450.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 25 Mar 2021 20:47:23 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/blinken-nato-wrap-2-25-2021/5828450.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0F9D1CC8-627D-4E44-82E6-859CBFC12A5C_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ባይደን “እርዳታው ይኸውላችሁ!” በማለት ሊዘዋወሩ ነው</title>
            <description>ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን፣ ለኢኮኖሚው ማነቃቂያ እንዲውል፣ በተላለፈው የ$1.9 ትሪሊዮን ዶላር ጥቅል በጀት ላይ ከፈረሙ በኋላ፣ በዚህ ሳምንት፣ ውሳኔያቸውን ለማስተዋወቅ ወደ የክፍለ ግዛቶቹ የሚያደርጉትን ጉዞ ሊጀምሩ ነው፡፡ አሜሪካውያንም ከበጀቱ የሚደርሳቸውን ገንዘብ እያገኙ ነው፡፡


በሌላም በኩል በስተደቡብ በኩል ባለው የአሜሪካ ድንበር ቁጥራቸው እየበዛ የመጣው የስደተኞች ቁጥር ዋሽንግተንን እያከራከረ ነው፡፡


ባለፈው ሳምንት ለኢኮኖሚው ማነቃቂያ እንዲውል፣ የተላለፈውን የ$1.9 ትሪሊዮን ዶላር ጥቅል በጀት ለማስተዋወቅ ፣ ጆ ባይደን እና ምክትል ፕሬዚዳንት ከማላ ኻሪስ “እርዳታው ይኸውላችሁ!” የሚል ጉዞ ጀምረዋል፡፡


እምጃው በአስርት ዓመታት ውስጥ ድህነትን ለማስወገድ ከተወሰዱ ውጤታማ እምርጃዎች ሁሉ አንዱ መሆኑ ተነግሮለታል፡፡ ከማነቃቂያ በጀቱ 1ሺ400 ዶላር ያህሉ ለበርካታዎቹ አሜሪካውያን የሚከፈል ሲሆን ቤተሰብ ላላቸው ደግሞ በልጅ 3 ሺ600 ዶላር በታክስ ተመላሽነት ታሳቢ ሆኖ የሚሰጥ ነው፡፡


ለበጀቱ ድጋፉን የሰጠ አንድም የሪፐብሊካን አባል የሌለ ሲሆን በጀቱ ውስጥ የተካተተው ገንዘብ እጅግ ትልቅ እና በአስፈላጊ ነገሮችን በግልጽ ለይቶ ያስቀመጠ አይደለም የሚል ተቃውሞ ከሪፐብሊካን በኩል ይሰማል፡፡


ከዋዮሚንግ ግዛት የህግ መወሰኛው ምክር ቤት አባል የሆኑት ሪፐብሊካኑ ጆን ባራሶ እንዲህ ይላሉ


“ሪፐብሊካኖች፣ ሰዎች ክትባቱን መውሰዳቸውን፣ ልጆች ወደ ትምህር ቤት፣ ሰዎች ወደ ሥራ ገበታቸው መመለሳቸውን ማረጋገጥ ይፈልጋሉ፡፡ ይሁን እንጂ ዴሞክራቶች ይህን ቀውስ ለራሳቸው አጀንዳ መጠቀሚያ ለማድረግ ሲሞክሩ ግን በዝምታ አንመለከታቸውም፡፡”


ዴሞክራቶቹ በቅርቡ የወጣውን የህዝብ አስተያየት ድምጽ ውጤት ይጠቅሳሉ፡፡ አብዛኞቹ አሜሪካውያን የወጣው የማነቃቂያ በጀት ደግፈውታል፡፡


ለምሳሌ ሲ ኤን ኤን ያወጣው የህዝብ አስተያየት ድምጽ እንደሚያመለከተው 61 ከመቶ የሆኑት አሜሪካውያን የእፎይታ በጀቱን ይደግፉታል፡፡ ዴሞክራቷ የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ናንሲ ፐሎሲ እንዲህ ብለዋል


“ሁሉም ክፍለ ግዛቶችና የማህበረሰቡ አባሎች ከዚህ ተጠቃሚ መሆናቸውን ማረጋገጥ ትችላላችሁ፡፡ መራጮቻቸሁ ይህን አስመልክቶ ቅሬታ ሊያሰሙ አይገባም፡፡”






ይህ በእንዲህ እንዳለ በአሜሪካ በስተደቡብ ባለው ድንበር ቁጥራቸው ድንገት እየጨመረ የመጣው ስደተኞች ጉዳይ ዋሽግተንን አስጨንቆ የያዘ ጉዳይ ሆኗል፡፡


እየተወሳሰበ የመጣው ይህ ችግር ጣት የሚያጠቋቁም እየሆነ ነው፡፡ ሪፐብሊካኖቹ ይህ የሆነው ፕሬዚዳንት ባይደን ቀደም ሲል በፕሬዚዳንት ትራምፕ የተወሰዱ እርምጃዎችን እየቀለበሱ በመምጣታቸው ነው ይላሉ፡፡


ዴሞክራቶችም በበኩላቸው ይህን ሁሉ ችግር የፈጠሩት የፕሬዚዳን ትራምፕ የቀደሙት ፖሊሲዎች ናቸው ይላሉ፡፡


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በድንበሩ አቅራቢያ እየተከማቹ የመጡት የበርካቶቹ ስደተኞች ጉዳይ ግን አነጋጋሪ መሆኑ አልቀረም፡፡


በአሜሪካ ድምጽ ዘጋቢ ሚሸል ኩዪን ከተዘጋጀው ዘገባ የተወሰደ፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-biden-travel-3-16-2021/5816950.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-biden-travel-3-16-2021/5816950.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 16 Mar 2021 21:59:33 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-biden-travel-3-16-2021/5816950.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/52B900AA-4C2E-462F-A489-8147E4B3F9AF_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ባይደን 100 ሚሊዮን ሰዎችን በ60 ቀን ውስጥ ልናስከትብ ነው አሉ</title>
            <description>ፕሬዚዳንት ባይደን ትናንት ሀሙስ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአሜሪካ ህዝብ በቴሌቪዥን ባስተላለፉት አብይ ንግግራቸው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ መላው አገሪቱን ያሽመደመደበትን አንደኛ ዓመቱን በማሰብ አሜሪካውያን ከፊታቸው የተደቀነውንም ፈተና አብረዋቸው እንዲወጡ እርዳታቸውን ጠይቀዋል፡፡ 

የዓለም ጤና ድርጅት የኮቪድ 19 ዓለም አቀፍ ወርረሽኝ መሆኑን ካስታወቀ አንደኛ ዓመቱን ይዟል፡፡ ከዚያን ጊዜ አንስቶ እስካሁን በመላው ዓለም ከ2.6ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሲሞቱ በዩናይትድ ስቴትስ ደግሞ ከ530ሺ ሰዎች በላይ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡

ሁላችንም አንድ ነገር አጥተናል፡፡ የጋራ ስቃይ የጋራ መ ስዋዕትነት፣ በሰዎች ህይወት መጥፋት እና ሁላችንም ህይወታችንን የተቀማንበት ዓመት ነበር፡፡

ፕሬዚዳንት ባይደን ወደ ሥልጣን ከመጡ 50 ቀናት በኋላ ትናንት ሀሙስ ለመጀመሪያ ጊዜ በአገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን በቀጥታ ባስተላለፉት አብይ ንግግራቸው አስተዳደራቸው ወረርሽኙኝ ለማስወገድ ያለውን ዝርዝር እቅድ ይፋ አድርገዋል፡፡ በአንድ መቶ ቀናት ውስጥ 100 ሚሊዮን ሰዎች ለማስከተብ ያስቀመጡት እቅድ ከታሰበው በላይ መሄዱንም ተናግረዋል፡፡

በእርግጥ ለነገሩ በአስተዳደሬ የመጀመሪያዎቹ መቶ ቀናት ውስጥ፣ 100 ሚሊዮን ሰዎችን እናስከትባለን በማለት ያስቀመጥነውን ግብ፣ በ60ዎቹ ቀናት ውስጥ ለመድረስ እየተቃረብን ነው፡፡ የትኛውም አገር ይህንን አላደረገም፡፡ 

ባይደን ሁሉም ክፍለ ግዛቶች ክትባቱን መውሰድ የሚችሉትን ሁሉንም አሜሪካውያን እስከ ግንቦት ወር መጀመሪያ እንዲያስከተቡ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ ይሁን እንጂ በርካታ መሰናክሎችም ተደቅኖባቸዋል፡፡ አንዳንዶቹ አሜሪካውያን ክትባቱን ለመውሰድ እያንገራገሩ ሲሆን እንደ አንዳንድ የክልል መንግሥታትም የፌደራል መንግሥቱን የጤና ደንቦችና ትዕዛዝትን መከተል አይፈልጉም፡፡ ለምሳሌ በቴክሳስ የፊትና የአፍንጫ ጭምብል የማድረጉ አስገዳጅነት እንዲቀር ተደርጓል፡፡ 

የፊትና አፍንጫ መሸፈኛውን ጭንብል ማጥለቅ ህይወት ለማዳን ከሚደረጉ ነገሮች ውስጥ አነስተኛው ነው፡፡ ይህ አንዳንዴ ሊከፋፍለን ይችላል፤ ክፍለ ግዛቶች ከክፍለ ግዛቶች ግን አብረው ተባብረው እንደመስራት እርስበርሳቸው ይናቆራሉ፡፡

ተንታኞች እንደሚሉት በክትባቱ እና በጤና ደንቦች ላይ ፖለቲካዊ ልዩነቶች ጥላቸውን አጥልተዋል፡፡ በተለይ ወረርሽኙ ገና በተከሰበታቸው የመጀመሪያዎቹ ዓመታት ላይ ልዩነቶቹ እጅግ የጎሉ ነበሩ፡፡ 

በቺካጎ ዩኒቨርስቲ፣ የህዝብ ፖሊሲ የሀሪስ ትምህርት ቤት ዲን የሆኑት ካትሪን ቤከር እንዲህ ይላሉ

ሰዎች ስለ ህዝብ ጤና የተምታቱ መልእክቶችን እየሰሙ ነው፡፡ የፖለቲካ ሁኔታው በጣም ጫፍና ጫፍ ሆኗል፡፡ ስለዚህ በህዝቡ ዘንድ ጤናን አስመልከቶ በሳይንስ ላይ ያለው ጥርጣሬ ለህዝብ የሚተላለፉ የጤና መልዕክቶችን ጎድቷቸዋል፡፡ በርግጥ ሰዎች ከሚሰሟቸው የተምታታቱ መል ዕክቶች አንጻር ተንስተው መሆኑ ይገባኛል፡፡ ይሁን እንጂ ይህን ነገር ዘላቂ ጉዳት ከሚያስከትሉ ነገሮች አንዱ ይመስለኛል፡፡ 

ትናንት ጧት ላይ ባይደን የ 1.9 ትሪሊዮን ዶላር የተመደበለትን የኮረና ቫይረስ የእፎይታ ህግ ፈርመዋል፡፡ ኢኮኖሚውንም ለማነቃቃት ጭምር ሲባል በህግ አውጭዎቹ ምክር ቤቶች የወጣው ይህ ህግ ከሪፐብሊካን አባላት የአንዳቸውንም ድጋፍ አላገኘም፡፡ 






በተወካዮቹ ምክር ቤት የሪፐብሊካን መሪ የሆኑት ኬቪን መካርቲ ምክንያቱን እንዲግ በማለት ያስረዳሉ

ይህ ህግ፣ የነፍስ አድን ህግ አይደለም፡፡ ገንዘቡም የእርዳታ ሂሳብ አይደለም፡፡ ይልቁንስ የግራ አክራሪዎች ከወረረሽኙ በፊት ያቀረቡት የወጪ ዝርዝር ነው፡፡

ፕሬዚዳንት ባይደን የኮቪድ 19 የእፎይታ ህግ የሚሰጠውን ጥቅም ለአሜሪካ ህዝብ ለማስረዳት ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች “እርዳታው ይኸውላችሁ” በሚል የጉዞ ፕሮግራም የሚያደርጉ መሆኑም ተዘግቧል፡፡

የዋይት ሀውስ የቪኦኤ ዘጋቢ ፓትሲ ውዳክሱዋራ ካጠናቀረቸው ዘገባ የተወሰደ፡፡




 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/covid-us-tv-biden-3-11-2021/5812083.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/covid-us-tv-biden-3-11-2021/5812083.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 12 Mar 2021 18:24:22 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/covid-us-tv-biden-3-11-2021/5812083.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/f026d968-ba2d-4b92-9e22-a473576845e8_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አሜሪካ በኮቪድ ወረርሽኝ ውስጥ አንድ ዓመት ሆናት</title>
            <description>ዩናይትድ ስቴትስ ለኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ በመጋለጧ ሰዎች ከቤት እንዳይወጡ ስታግድ ዛሬ ልክ አንድ ዓመት ሆኗል፡፡ ይሁን እንጂ አሁን ወደ መደበኛው የህይወት እንቅስቃሴ የመመለሱ ነገር ቀስ በቀስ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ 


የዛሬ አንድ ዓመት አካባቢ በኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ሳቢያ በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የሚገኙ ከተሞች ሁሉ መዘጋጋት ጀመሩ፡፡ ዓለም አቀፉን ወረረሽኝ በሚከታተለው የጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ መረጃ መሠረት ከዚያን ጊዜ አንስቶ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ ወደ 29 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችም ለቫይረሱ ተጋልጠዋል፡፡ 


አሜሪካ ዛሬ በተለየ ሁኔታ ላይ ትገኛለች፡፡


ወረርሽኙ በምጣኔ ሀብቱ ላይ ያደረሰውን ጉዳት ለመቋቋም ፕሬዚዳንት ባይደን የጠየቁት የ $1.9 ትሪሊዮን ዶላር በጀት፣ የአንዱንም ሪፐብሊካን አባል ድጋፍ ሳያገኝ በህግ መወሰኛው ምክር ቤት በማለፍ አሁን ወደ ተወካዮቹ ምክር ቤት አምርቷል፡፡ 






በክትባቱም ረገድ ከፋይዘርና ሞደርና ቀጥሎ ሶስተኛ ሆኖ በተጨማሪነት የወጣው የጆንሰን ኤንድ ጆንሰን ክትባት በስርጭት ላይ ይገኛል፡፡

ይሁን እንጂ እንደ ቴክሳስና ሚሚስፒ የመሳሰሉት የአሜሪካ ክፍለ ግዛቶች የፊትና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብሎችን አስገዳጅነት ለማንሳትና ምግብ ቤቶችን ሙሉ ለሙሉ እንዲከፈቱ ያስተላለፉት ውሳኔ ያለ ጊዜው የፈጠነ መሆኑ ስጋት ፈጥሯል፡፡ ራሳቸውን የመከላከሉ ጉዳዩ ካሁን በኋላ የነዋሪዎች እንጂ የመንግሥት አለመሆኑም ተነግሯል፡፡ 


ይህን አስመልክቶ አንዳንድ የጤና ባለሥልጣናት ስጋታቸውን እየገለጹ ነው፡፡ የብራውን ዩኒቨርስቲ የህዝብ ጤና ክፍለ ትምህርት ዲን የሆኑት ዶር አሺሻ ጃ ከ እነዚህ አንዱ ናቸው፡፡


ወደ ማብቂያው ጊዜ በተቃረብንበት በዚህ ወቅት፣አንድ ሰው ዛሬ በቫይረሱ የተያዘ ሆኖ በሶስትና አራት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ የሚሞት ከሆነ፣ ይህ ሰው ክትባቱን የሚያገኘው የዛሬ ወር ገደማ ነው ማለት ነው፡፡ ለዚህ ነው ጥንቃቄውን ትንሽ ዘለግ ላለ ጊዜ ማቆየት ያለብን፡፡


የክፍለ ግዛቶቹ ገዢዎች የፊትና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎች ላይ ያስቀመጧቸውን አስገዳጅ ደንቦች የሚያነሱባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች አስቀምጠዋል፡፡

በኦሃዮ ከአንድ መቶ ሺ ሰዎች ውስጥ ለቫይረሱ የተጋለጡ ሰዎች 50 ብቻ እስኪሆኑ ድረስ አስገዳጅነቱ የሚቀጥል መሆኑ የተነገረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን ያለው 179 ሰዎች መሆኑን ሪፐብሊካኑ የኦሃዮ ገዥ ማይክ ደዋይን ተናግረዋል፡


ከክትባቱ ጋር አሁን በማጥቃት ላይ ነን፡፡ ያ በጣም ጥሩ ነገር ነው፡፡ ይሁን እንጂ ኦሃዮ ውስጥ መከላከላችንን በፍጹም ማቆም የለብንም፡፡ ይህ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ከሚገባው በላይ እየሠራ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡ 


ሌላው የስጋት ምንጭ ሆነ የተገኘው የትምህር ቤቶች ጉዳይ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ 27 ከመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ትምህርታቸውን የሚከታተሉት በርቀት ብቻ ነው፡፡ በብዙ ክፍል ግዛቶች መምህራንና የትምህር ቤት ሠራተኞች ክትባቱ ተሰጥቷቸው ተማሪዎች በፍጥነት ወደ ትምህር ቤት እንዲመለሱ ለማድረግ ትልቅ ግፊት አለ፡፡


ምንም እንኳ የክለ ግዛቱ ገዢ ማይክ ደዋይን ከዚህ ወር መጀመሪያ አንስቶ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ የሚፈልጉ ቢሆንም፣ በክሊቭላንድ ኦሃዮ የሚገኘው የመምህራን ማህበር አባላት በሰጡት ድምጽ የርቀት ትምህርቱ እንዲቀጥል ወስነዋል፡፡ 


የክፍለ ግዛቱ ገዥ ደዋይን ግን እንዲህ ብለዋል


ወደዚህ ዓመት መጀመሪያ አካባቢ ላይ ኦሃዮ ውስጥ ከሚገኙ ልጆቻችን ግማሽ የሚሆኑት ትምህርታቸውን የሚከተታሉት በርቀት ነበር፣ ዛሬ ግን ከ95 ከመቶ በላይ የሚሆኑት ክፍል ውስጥ ናቸው፡፡ ስለዚህ ዛሬ ስለደረስንበት ነገር በጣም ደስተኞች ነን፡፡


የቪኦኤ ዘጋቢ ሚሽል ኩዪን ካሰናዳችው ዘገባ የተወሰደ፡፡

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-ahead-03-09-2021/5807982.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-ahead-03-09-2021/5807982.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 09 Mar 2021 23:36:58 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዩናይትድ ስቴትስ</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/washington-week-ahead-03-09-2021/5807982.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/756795E9-E4BF-457E-B111-9123917940CF_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>