<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>ዓለምአቀፍ - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/3737</link>
        <description>International news, features</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>ዓለምአቀፍ - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/3737</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Wed, 08 Apr 2026 19:11:23 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/ziibql-vomx-tpemgqqo" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>ሚሳይል መስሪያ ግብአት በመጫን የተጠረጠረችው ሁለተኛ የኢራን መርከብ ከቻይና ተነሳች</title>
            <description>ከቻይና የሚሳይል ነዳጅ መስሪያ ቁልፍ ግብአቶችን ጭናለች ተብላ በምዕራባዊያን የዜና ዘገባዎች  የተጠረጠረችው ሁለተኛዋ የኢራን  መርከብ ወደ ኢራን እያመራች መሆኑን የቪኦኤ ልዩ የትንታኔ ዘገባ አመልክቷል፡፡
የመርከብ እንቅስቃሴ ክትትል ድረ-ገጾች እንደሚያሳዩት የኢራን ባንዲራ የሚያውለበልበው ጃይራን የተባለው የጭነት መርከብ፣ ከቻይና ይነሳል ተብሎ ከተጠበቀበት ጊዜ ከአንድ ወር በኋላ ዘግይቶ ባለፈው ሰኞ መነሳቱ ተጠቅሷል፡፡
በጥር እና በየካቲት  ዘ ፋይናንሺያል ታይምስ፣ ዘ ዎል ስትሪት ጆርናል እና ሲ ኤን ኤን ባቀረቧቸው ዘገባዎች፣ ቴህራን  በሚሳይል ነዳጅ ውስጥ ጥቅም ላይ የሚውለውን 1,000 ሜትሪክ ቶን ኬሚካል (ሶዲየም ፐርክሎሬት) ለመጫን ከምትጠቀምባቸው ሁለት መርከቦች መካከል ጃይራን አንዱ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡
ሦስቱ የዜና ማሰራጫዎች ስማቸው ያልተጠቀሱ የምዕራባውያን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/iran-china-missile-scheme-/8010868.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/iran-china-missile-scheme-/8010868.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 19:50:09 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/73570913-c12b-459d-b0a3-828c76588f8a_cx0_cy18_cw0_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አይኤምኤፍ እና ኢትዮጵያ በዋጋ ግሽበት ትንበያ ተለያዩ</title>
            <description>. ትንበያዎቹ &quot;የተለያዩ ብቻ ሳይኾኑ ከእውነታውም የራቁ ናቸው&quot; - ባለሞያ
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ)፣ በቅርቡ ስለ ኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ያወጣው ትንበያ፣ እ.ኤ.አ በ2025፣ 25 ከመቶ መድረሱን ይገልጻል፡፡ የዋጋ ንረቱ አኹን ካለበት ሁለት አኀዝ ወደ ነጠላ አኀዝ ለመውረድ እስከ 2028 ሊቆይ እንደሚችልም አይኤምኤፍ ተንብይዋል፡፡
በአንጻሩ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የዋጋ ግሽበቱ እየወረደ መምጣቱንና አኹን ከ15 እስከ 16 በመቶ ዝቅ ማለቱን ይናገራል፡፡
በለንደን የሚገኙት የፋይናንስ እና የምጣኔ ሀብት ባለሞያ ዶር. አብዱልመናን መሐመድ ሃምዛ ግን፣ የአይኤምኤፍም ኾነ የኢትዮጵያ መንግሥት ቁጥሮች፣ &quot;የተለያዩ ብቻ ሳይኾኑ ከእውነታው የራቁ ናቸው፤&quot; ይላሉ፡፡
ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ አጭር ቆይታ ያደረጉት ዶር. አቡዱልመናን፣ በአይኤምኤፍ እና በኢትዮጵያ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/imf-ethiopia-s-inflation/8010710.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/imf-ethiopia-s-inflation/8010710.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 18:06:32 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5ca8d0af-a26a-49ff-0900-08dd5c8b1668_cx0_cy12_cw0_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሩሲያ የተቆጣጠረቻቸውን የዩክሬን ግዛቶች እንደያዘች መቀጠል ትሻለች</title>
            <description>ሩሲያ በዩክሬን የምታካሒደውን ጦርነት ለማስቆም፣ አሜሪካ የምታደርገው ጥረት በክሬምሊን ላይ ጫናን ፈጥሯል። ይኹንና ሞስኮ አሁንም በቀጠለችው ጥቃት ተጨማሪ የዩክሬን ስፍራዎችን ተቆጣጥራለች፡፡
በሩሲያ የሚገኙ አንዳንድ ባለሥልጣናት ደግሞ፣ በድርድሩ ሩሲያ ምንም ነገር አሳልፋ መስጠትን እንደማትሻ በመናገር ላይ ናቸው።
የቪኦኤው ጄፍ ከስተር የላከውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/russia-ukraine-concessions/8009965.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/russia-ukraine-concessions/8009965.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:21:08 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/fce71d0f-fae4-482a-0ed0-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኤኮዋስ የፀረ-ሽብር ጦሩ በተጠንቀቅ እንዲቆም አደረገ</title>
            <description>የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ &quot;ኤኮዋስ&quot; የቀጠናው የጦር ኃይል በተጠንቀቅ እንዲጠባበቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል። የጸጥታ ተንታኞች ርምጃውን ያደነቁ ቢሆንም፣ የተቋሙ ሦስት አባል ሀገራት በቅርቡ መውጣታቸው ውጤታማነቱን አጠራጣሪ እንደሚያደርገው ተገልጿል።
የናይጄሪያ መከላከያ ሚኒስትር ሞሃመድ ባዳሩ አቡባካር የኤኮዋስ የጦር ኃይል በተጠንቀቅ ላይ እንደሚሆን ያስታወቁት፣ ትላንት ማክሰኞ በተካሄደው የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት ጥምረት የሆነው ኤኮዋስ 43ኛ መደበኛ የፀጥታ ስብሰባ ወቅት ነው።
5 ሺሕ ወታደሮች እንደሚኖሩት የሚጠበቀው የጦር ኃይል፣ በቀጠናው የሚካሄዱትን ሽብርተኝነት እና ድንበር ዘለል ወንጀሎች ለመከላከል የሚደረግ ቀጠናዊ የፀጥታ እንቅስቃሴ አካል ነው።
አቡበከር በንግግራቸው &quot;ይህ  ኃይል በተጠንቀቅ እንዲቆም ሆኖ ሥራ መጀመሩ፣ የሽብርተኝነትን መስፋፋት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ecowas-regional-bloc-activates-counterterror-force/8009724.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ecowas-regional-bloc-activates-counterterror-force/8009724.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 20:42:16 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9a78e2c0-aa66-46a3-95bd-53dfc7c9bc06_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ትረምፕ ከአውሮፓ በሚገቡ የአልኮል መጠጦች ላይ ከበድ ያለ ታሪፍ እንደሚጥሉ አስታወቁ</title>
            <description>የአውሮፓ ኅብረት ከአሜሪካ በሚገባው ዊስኪ ላይ የ50 በመቶ ታሪፍ መጣሉን ተከትሎ፣ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ከአውሮፓ በሚገባው የወይን ጠጅ፣ ሻምፓኝና ሌሎች የአልኮል መጠጦች ላይ የ200 በመቶ ታሪፍ እንደሚጭኑ አስጠንቅቀዋል።
የ27 ሃገራት ስብስብ የሆነውን የአውሮፓ ኅብረት &quot;በዓለም የከፋው ታክስና ታሪፍ ጣይ&quot; ሲሉ የገለጹት ትረምፕ፣ &quot;እ.አ.አ በ1993 ሲመሠረት ዓላማው &quot;ከአሜሪካ የኢኮኖሚ ጥቅም ለማግኘት ነው&quot; ብለዋል። 
ባለፈው አንድ ወር ከአሜሪካ ከፍተኛ የንግድ ሸሪኮች፣ ማለትም ከሜክሲኮ፣ ካናዳ፣ ቻይናና የአውሮፓ ኅብረት ጋራ የታሪፍ ውዝገብ ውስጥ የገቡት ትረምፕ፣ ታሪፉን መጣሉ አስፈላጊ የሆነው ሃገራቱ ወደ አሜሪካ የሚገባውን አደገኛ  ዕጽ እና መድሃኒት እንዲያስቆሙና እንዲሁም የሸቀጥ አምራቾች በውጪ ያላቸውን ፋብሪካ ዘግተው ወደ አሜሪካ እንዲመጡ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/trump-tariffs/8009704.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/trump-tariffs/8009704.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 20:34:24 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a1531c9d-c3db-422b-0e43-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከታቀደው በላይ የቆዩትን ጠፈርተኞች ለመተካት ሊላክ የነበረው የስፔስ ኤክስ ተልእኮ ዘገየ</title>
            <description>ጠፈር ላይ ከጊዜያቸው በላይ የቆዩ የ ዩናይትድ ስቴትስ የኤሮኖቲክስ እና ጠፈር ምርምር (ናሳ) ጠፈር ተመራማሪዎችን ለመተካት ወደ  ሊላክ የነበረው የስፔስ ኤክስ መንኮራኩር የሮኬት ማስወንጨፊያ እክል ስለገጠመው ወደ ጠፈር ጣቢያው የሚያደርገው በረራ ዘግይቷል፡፡
ቡች ዊልሞር እና ሱኒ ዊሊያምስ የተባሉት ጠፈርተኞች ከዘጠኝ  ወራት  ቆይታ በኋላ ወደ ምድር ከመመለሳቸው በፊት እነሱን የሚተካ የጠፈርተኞች ቡድን ከዓለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ መድረስ ይኖርበታል፡፡
ይሁን እንጂ ከኬኔዲ የጠፈር ማእከል ሊወነጨፍ ተዘጋጅቶ የነበረውን ፋልከን ሮኬት እክል ገጥሞታል፡፡
አሶስየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ሮኬቶቹን ደግፈው ከያዙት መሳሪያዎች መካከል አንዱን የሚቆጣጠረው የማስወንጨፊያ ክፍል (የማስነሻ ፓድ)  ችግር የገጠመው መኾኑን መሀንዲሶች በመናገራቸው ስፔስ ኤክስ (SpaceX) ተልዕኮውን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/https-www-voanews-com-a-launch-pad-problem-delays-spacex-flight-to-replace-nasa-s-stuck-astronauts-8009048-html/8009493.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/https-www-voanews-com-a-launch-pad-problem-delays-spacex-flight-to-replace-nasa-s-stuck-astronauts-8009048-html/8009493.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 18:18:13 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5ee089cb-5149-4b45-0757-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኩዌት ከአደገኛ ዕጽ ጋራ በተያያዘ የታሰሩ የቀድሞ ሠራዊት አባላት ጨምሮ አሜሪካዊ እስረኞችን ለቃለች</title>
            <description>ኩዌት ከአደገኛ ዕፅ ጋራ በተያያዘ ክስ ተመስርቶባቸው ለዓመታት በእስር ላይ የነበሩ የቀድሞ ሠራዊት አባላትና እና የወታደራዊ ተቋራጭ ሠራተኞችን ጨምሮ አሜሪካውያን እስረኞችን ለቃለች።
የአሜሪካ መንግሥት በውጭ ሀገር የታሰሩ አሜሪካውያንን አስለቅቆ ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ ባደረገው ጥረት የተፈቱት እስረኞች ወደ ኒውዮርክ ተወስደዋል፡፡
እስረኞቹ የተለቀቁት በቅርቡ ዋናው የትረምፕ አስተዳደር የታጋቾች ጉዳይ መጓዛቸውን ተከትሎ መኾኑም ተመልክቷል፡፡
በአሜሪካዊያን ታጋቾች እና እስረኞች ጉዳይ የሚሰሩት አማካሪው ጆናታን ፍራንክ እስር ላይ ከነበሩ ስድስት እስረኞች ጋራ በመኾን ለኩዌት መንግሥት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን “ደንበኞቼና ቤተሰቦቻቸው የኩዌት መንግሥት ላሳየው ሰብአዊነት ምስጋናቸውን ያቀርባሉ”ሲሉም በመግለጫቸው ተናግረዋል፡፡ ደንበኞቻቸው ጥፋት የሌለባቸው ንጹሐን መኾናቸውንም...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/kuwait-frees-a-group-of-jailed-americans-including-contractors-held-on-drug-charges/8009398.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/kuwait-frees-a-group-of-jailed-americans-including-contractors-held-on-drug-charges/8009398.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 17:03:57 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/2b3bac0b-d475-42e6-0758-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቀረጡ ጉዳይ በዩናይትድ ስቴትስ ኢኮኖሚ ላይ ያስከተለው አለመረጋጋት</title>
            <description>የቀረጡ ጉዳይ ከዋጋ ንረት ስጋት ጋራ ተዳምሮ በፈጠረው አለመረጋጋት የተነሳ ሰኞ እና ማክሰኞ የዩናይትድ ስቴትስ የአክሲዮን ገበያ አሽቆልቁሏል፡፡
በአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ እና በሕዝብ ብዛት ትልቋ የካናዳ ጠቅላይ ግዛት ኦንታሪዮ ጠቅላይ ሚንስትር ደግ ፎርድ መካከል የሁለቱን ሀገሮች የንግድ ውዝግብ በሚመለከት የተደረገውን ልውውጥ ጠቅሳ የቪኦኤ የኋይት ሐውስ ዘጋቢ ካሮላይን ፕሬሱቲ የላከችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
የቪኦኤ ዋትስአፕ ቻናል ይከተሉ 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8009199.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8009199.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 13:56:26 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0c7bb9ac-79cd-4505-0e03-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በግሪንላንድ ምርጫ ያሸነፈው ፓርቲ የትረምፕን ዕቅድ ተቃወመ</title>
            <description>በግሪንላንድ በተካሄደው የምክር ቤት ምርጫ፣ ሀገሪቱ በሂደት ከዴንማርክ ነጻ እንድትወጣ የሚደግፈው ዴሞክራቲት ፓርቲ ያልተጠበቀ ድል ተቀዳጅቷል፡፡
የትላንት ማክሰኞው ምርጫ የተካሄደው፣ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ደሴቲቱን ለመጠቅለል ያላቸውን እቅድ ይፋ ባደረጉበት ድባብ ውስጥ ነው፡፡
ዲሞክራቲት ፓርቲ “የግዛቲቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወስኑት የግሪላንድ ነዋሪዎች ናቸው” በማለት የትረምፕን ንግግር ሲቃወም ቆይቷል፡፡
“የምርጫው ውጤት ግሪንላንድ አትሸጥም የሚለውን ግልፅ መልዕክት ለትረምፕ ማስተላለፍ አለበት” ሲሉ የፓርቲው መሪ ጄንስ ፍሪደሪክ ኒልሰን ለስካይ ኒውስ ተናግረዋል።
&quot;እኛ አሜሪካዊ መሆን አንፈልግም። ፣ ዴኒሽ መኾንም አንፈልግም። የምንፈልገው ግሪንላንድነታችንን  ነው። ወደፊትም  ነፃነታችንን እንፈልጋለን። የራሳችንን ሀገር እርሳቸው በሚሰጡት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8008519.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8008519.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 22:30:23 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/8231741b-316a-4e22-0b45-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአርጀንቲናው ጎርፍ የሞቱት ሰዎች 16 ሲደርስ ሁለት ሕጻናት የደረሱበት ጠፍቷል</title>
            <description>ባሂያ ብላንካ በምትባለው የአርጀንቲና የወደብ ከተማ በደረሰው የጎርፍ መጥለቅለቅ የሞቱት ሰዎች ቁጥር አሻቅቦ 16 መድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።
ጥልቅ ውሃ ዋናተኞች ጎርፉ የወሰዳቸውን ሁለት ሕጻናት ፍለጋ ላይ ተሰማርተዋል፡፡
ከቦይኖ ሳይረስ ክፍለ ግዛት በስተደቡብ የምትገኘው ከተማ ከሀገሪቱ ትላልቅ ወደቦች አንዱ የሚገኝባት ስትኾን በዓመት የሚጥለው መጠን ያለው ዝናብ ዓርብ ዕለት በጥቂት ሰዓት ውስጥ ወርዶባታል። መንገዶች እንዲሁም በርካታ መንደሮች በአንድ ጊዜ በጎርፍ ተጥለቅልቀዋል፡፡
በጎርፉ 400 ሚሊዮን ዶላር ግምት ያለው መሠረተ ልማት እንደወደመ የከተማዋ ከንቲባ ፌዴሬኮ ሱስቤልየስ ተናግረዋል። 16 ሰዎች መሞታቸው እንደተረጋገጠ የገለጹት ከንቲባው ቁጥሩ ይጨምራል የሚል ስጋት መኖሩንም አክለዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአንድ ዓመት እና የአምስት ዓመት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/argentina-flooding-death-toll-rises-to-16-two-girls-missing/8008222.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/argentina-flooding-death-toll-rises-to-16-two-girls-missing/8008222.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 19:54:58 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/440bbb0b-7eb5-413e-948b-399676398dfd_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የፓኪስታን ጦር ወደ 200 የሚጠጉ የባቡር ተሳፋሪዎችን ሕይወት አተረፈ</title>
            <description>ፓክሲታን ውስጥ ዛሬ ረቡዕ በታገተው ጃፈር ፈጣን ባቡር ላይ በተካሄደ ወታደራዊ ዘመቻ የሠራዊቱ አባላት 190 ተሳፋሪዎችን ሲታደጉ 30 አሸባሪዎችን መግደላቸው ተገለጸ።
ርምጃው የተወሰደው ደቡባዊ የባሎቺስታን ግዛት ውስጥ ትላንት በተካሄደበት ጥቃት ለ24 ሰዓታት ዋሻ ውስጥ እንዲያድር የተገደደውን ባቡርና ተሳፋሪዎችን ለማስለቀቅ በተደረገ ጥረት ነው፡፡
ወደ 450 የሚጠጉ ሰዎችን አሳፍሮ ከኩዌታ ወደ ፔሻዋር በመጓዝ ላይ የነበረው ባቡር የቦምብ እና የተኩስ ጥቃት የደረሰበት ትላንት ማክሰኞ መኾኑን ተነግሯል፡፡
ጥቃቱንም ተከትሎ ባቡሩ በሲቢ አቅራቢያ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ ከ24 ሰዓታት በላይ ታግቶ እንዲቆይ መደረጉ ተገልጿል።
ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደው የባሎክ ነፃ አውጪ ጦር (BLA) 200 ታጋቾችን በተለይም የደኅንነት እና የስለላ አባላትን መያዙን ገልጾ፣ የፖለቲካ እስረኞች...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/pakistan---train-attack/8008084.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/pakistan---train-attack/8008084.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 17:44:14 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a1642250-3b39-4fc6-8f72-00ccca9eebe4_cx0_cy3_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዩክሬን ሩሲያ አስቸኳይ የ30-ቀናት ተኩስ አቁም ተከትሎ የቡድን 7 ሀገራት ይወያያሉ</title>
            <description>በኢንዱስትሪ የበለጸጉ የቡድን 7 ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ የሦስት ዓመቱን የሩሲያ ወረራ እየመከተች ላለችው ዩክሬን የሚሰጡትን ድጋፍ ጨምሮ፣ በተለያዩ ጉዳዮች ለበርካታ ቀናት ለመምከር፣ በኩቤክ ካናዳ ይሰበሰባሉ፡፡  
ውይይቱ ዩክሬን እና አሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በሳዑዲ አረቢያ ጂዳ ከተገናኙ በኋላ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬን የምታደርገውን የመረጃ ልውውጥ እና የፀጥታ ድጋፍ እንድምትቀጥል ያሳለፈችውን ውሳኔ ተከትሎ ነው።
ዩክሬን ከሩሲያ ጋራ በሚደረገው ጦርነት “የ30 ቀን አስቸኳይ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም” የሚለውን የአሜሪካ ሐሳብ ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን ትላንት ማክሰኞ አስታውቃለች።
የጀርመኑ መሪ ቻንስለር ኦላፍ ሾልዝ ትላንት ረቡዕ ኤክስ በተሰኘ ገጻቸው እንደተናገሩት “ለዩክሬን ፍትሃዊ ሰላም ወሳኝ እና ትክክለኛ ርምጃ ነው” በማለት የ30 ቀን የተኩስ አቁም...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ubio-ukraine-g7/8008072.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ubio-ukraine-g7/8008072.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 17:36:17 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/c395cd8a-ce8a-4186-9789-c2a0489e14ad_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሩሲያ ሚሳይል ጥቃት በኦዴሣ አራት ሰዎች መግደሉን የዩክሬን ባለሥልጣናት አስታወቁ</title>
            <description>የዩክሬን ባለሥልጣናት በደቡባዊ ዩክሬን የወደብ ከተማ ኦዴሣ፣ ሌሊቱን በደረሰ የሩሲያ ሚሳይል ጥቃት፣ አራት ሶሪያውያን ሲገደሉ፣ በርካቶች ቆስለዋል ሲሉ፣ ዛሬ ረቡዕ አስታወቁ፡፡
የመልሶ ግንባታ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ኦሌክሲ ኩሌባ በቴሌግራም ማኅበራዊ መድረክ ላይ እንደተናገሩት፣ ሚሳይሉ ወደ አልጄሪያ የሚላክ ስንዴ በመጫን ላይ በነበረች የጭነት መርከብ ላይ ጉዳት አድርሷል።
ሩሲያ የዓለምን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ላይ የተሰማሩ ወደቦችን ጨምሮ የዩክሬን መሠረተ ልማቶችን እያጠቃች መኾኑ ተመልክቷል።
ሌላ የሚሳይል ጥቃት በዲኒፕሮፔትሮቭስክ ክልል ውስጥ በምትገኘው የፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ የትውልድ ከተማ ክሪቪ ሪህ ላይ ጉዳት አድርሷል፡፡ በዚህ ጥቃት ቢያንስ አንድ ሰው ሲሞት ዘጠኝ ሰዎች ቆስለዋል ሲሉ የክልሉ ገዥ ተናግረዋል።
አገረ ገዥው ሰርሂ ሊሳክ ክልሉ ከሩሲያ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/russia-ukraine-fighting/8007992.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/russia-ukraine-fighting/8007992.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 16:33:06 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/773824e6-60de-4dff-3282-08dd5c897904_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የእስራኤል ወግ አጥባቂዎች  ፍልስጤማውያንን ከጋዛ የሚያስወጣ &quot;የፍልሰት ባለሥልጣን&quot; ለማቋቋም አቅደዋል</title>
            <description>የእስራኤል  አክራሪ ወግ አጥባቂዎች  ከ2.3 ሚሊዮኑ ፍልስጤማውያን ብዙዎቹ ጋዛን  ለቀው እንዲወጡ የሚያደርገውን የፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕን እቅድ በደስታ ተቀብለዋል። “ስደትን ማበረታታት ዓለም አቀፍ ሕግን አይጥስም” ይላሉ። ፍልስጤማውያን ግን እቅዱን ውድቅ አድርገውታል።
የእስራኤሉ የገንዘብ ሚኒስትር ቤዛሌል ስሞትሪች ፍልስጤማውያን ጋዛን ለቀው እንዲወጡ ለማበረታታት በመከላከያ ሚኒስቴር ውስጥ &quot;የፍልሰት ባለሥልጣን&quot; እያቋቋሙ መኾኑን ተናግረዋል።
ቤዛሌል ስሞትሪች፣ የእስራኤል የገንዘብ ሚኒስትር “ስደትን ለማበረታታት የምናወጣው እያንዳንዱ ብር፣ ደጋግመን በመታገል ከምንከፍለው  ዋጋ ያነሰ ነው። በጀቱ ለዚህ እቅድ እንቅፋት አይሆንም፣ ይህ ሌላ እቅድ ብቻ አይደለም። በመካከለኛው ምስራቅ እና በእስራኤል ታሪካዊ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል አቅም ነው&quot; ብለዋል።
የኬኔሴት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8007406.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8007406.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 02:39:55 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/56e06c2a-a6ab-4d6f-0caa-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ውጥረቱ እያየለ በመጣባት ሰርቢያ ተቃዋሚዎች ወደ ዋናው የሰርቢያ ቴሌቭዥን ጣቢያ የሚወስደውን መንገድ ዘግተው ዋሉ</title>
            <description>በመቶዎች የተቆጠሩ ተማሪዎች ውጥረቱ እያየለ በመጣባት የባልካን ሀገር፣ ለፊታችን ቅዳሜና እሑድ ከታቀደው ግዙፍ ሰልፍ ቀናት አስቀድመው ቤልግሬድ የመንግሥቱን የሰርቢያ ቴሌቪዥን ጣቢያ ህንጻ ዘግተው ውለዋል። ለሳምንቱ መጨረሻ የተጠራው ግዙፍ ሰልፍ ለወራት የቀጠለው የጸረ መንግሥት ተቃውሞ መዳረሻ ተደርጎ ታይቷል።
ማዕከላዊ ቤልግሬድ የሚገኘውን የቴሌቭዥን ሕንጻ ትላንት ማምሻው ላይ የዘጉት ተማሪዎች፣ ዛሬ ማክሰኞም ብዙ መቶዎች ኾነው ተሰባስበው የመንገድ መዝጋቱ ጥረት ለተጨማሪ 22 ሰዓታት እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። በሁለተኛዋ የሃገሪቱ ትልቅ ከተማ ኖቪ ሳድ’ም ተመሳሳይ ተቃውሞ  ተደራጅቷል።
በኖቪ ሳድ የባቡር ጣቢያ የኮንክሪት ጣሪያ ተደርምሶ የ15 ሰዎች ህይወት ካጠፋ በኋላ፣ በየዕለቱ የሚካሄዱትን ሰልፎች የሚያደራጁት በተለያዩ የሰርቢያ ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ ተማሪዎች ናቸው።...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/protesters-block-main-state-serbian-tv-building-as-tensions-soar-ahead-of-a-planned-large-rally-belgrade-serbia-/8007238.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/protesters-block-main-state-serbian-tv-building-as-tensions-soar-ahead-of-a-planned-large-rally-belgrade-serbia-/8007238.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 23:10:45 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/1653dfed-e154-4489-04f8-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዛሬው የግሪንላንድ ምርጫ ነጻ አገር የመሆን ምኞቶች የሚፈተሹበት ነው ተባለ</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በማዕድን የበለጸገችውን ደሴት ለመቆጣጠር ፍላጎት እንዳላቸው ያንጸባረቁበት ውጥን ዓለም አቀፍ ትኩረት በሳበበት በዚህ ወቅት ፤ የግሪንላንድ ነዋሪዎች ዛሬ ማክሰኞ  ምርጫ እያካሄዱ ነው። 
ትረምፕ  ሥልጣን እንደተረከቡ ነበር ‘ለዩናይትድ ስቴትስ የደህንነት ጥቅም አስፈላጊ ናት’ ሲሉ ከፊል ራስ ገዟን የዴንማርክ ግዛት የዩናይትድ ስቴትስ አካል ለማድረግ ያላቸውን ፍላጎት ይፋ ያደረጉት።
57, 000 ሕዝብ ብቻ ያላት ደሴቲቱ ግዛት የከበባት በረዶ አለት መቅለጥ የተፈጥሮ ሃብቷን ይበልጥ ተደራሽ እያደረገ በመጣበት እና አዳዲስ የመርከቦች መመላለሻ መንገዶች እየተከፈቱ ባለበት፤ የአርክቲክ ውቅያኖስን እና አካባቢውን በበላይነት ለመቆጣጠር የተያዘው እሽቅድምድም ሆናለች። ሩስያ እና ቻይናም በአካባቢው  ወታደራዊ እንቅስቃሴያቸውን አጠናክረው...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8007019.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8007019.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 20:45:35 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/70bfa989-42d8-4bd9-a8ee-41006978a74e_cx0_cy7_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዩክሬይን በዩናይትድ ስቴትስ ለተወጠነው የሰላም ንግግር ዕቅድ ልታቀርብ ነው</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ እና የዩክሬን ባለሥልጣናት ዛሬ ማክሰኞ ሳዑዲ አረቢያ ላይ በኪየቭ እና ሞስኮ መካከል የከፊል ተኩስ የማቆም ስምነት የታለመ እቅዳቸውን እንዲያቀርቡ የሚጠበቅበት ንግግር ጀምረዋል።  
የዩክሬን እቅድ የረጅም ርቀት የሚሳዬል ጥቃቶችን ማቆም እና ጥቁር ባህርን የሚሸፍን የሰላም ስምምነት ያካትታል። 
የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ በዛሬው ንግግር አልተሳተፉም። በምትካቸው የፕሬዝደንታዊው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አንድሬ የርማክ፣ የዩክሬኑ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንድሪ ሲቢሃ፣ የመከላከያ ሚንስትሩ ረስተም ኡሜሮቭ እና ወታደራዊ አዛዡ ፓቭሎ ፓሊሳ ተወክለዋል።  
የርማክ ከስብሰባው አስቀድሞ ለጋዜጠኞች በሰጡት አስተያየት “ሰላምን እንዲመጣ ዩክሬን ሁሉንም ነገር ለማድረግ ዝግጁ ነች&quot; ብለዋል።.
ሀገራቸው የደኅንነት ዋስትና እንዲሰጣት ትሻ እንደሆን የተጠየቁት...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/rubio-ukraine/8006758.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/rubio-ukraine/8006758.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 18:40:25 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/d78f7d16-5b43-44a4-0b3f-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በጀርመን አየር ማረፊያዎች የተካሄደው የአንድ ቀን የሥራ ማቆም አድማ በረራዎችን አስተጓጎለ </title>
            <description>የፍራንክፈርት እና የሙኒኩን ጨምሮ በ13 የጀርመን አውሮፕላን ጣቢያዎች እና ሌሎች የሀገሪቱ ዋና መዳረሻዎች፤ ሠራተኞች በዛሬው ዕለት ያደረጉት የአንድ ቀን የሥራ ማቆም አድማ ቀደም ሲል ጊዜ ተይዞላቸው የነበሩ አብዛኛዎቹ በረራዎች እንዲሰረዙ ምክኒያት ሆኗል።


ትላንት እሑድ እኩለ ለሊት ላይ የጀመረው እና ለ24 ሰዓታት እንዲቀጥል የታቀደው የሥራ ማቆም አድማ፤ በአውሮፕላን ጣቢያዎቹ የሚያገለግሉ ከአየር ማረፊያ ጋራ የተዛመዱ የምድር አገልግሎቶች ሥራ የሚሠሩ እና የደኅንነት ሠራተኞችን ያካተተ ነው።


በፍራንክፈርት አውሮፕላን ጣቢያ ለዕለቱ ታቅደው ከነበሩት ቁጥራቸው 1 ሺሕ 54 ከሚደርሱት በረራዎች 1 ሽሕ 116ቱ መሰረዛቸውን የጀርመን ዜና አገልግሎት የሀገሪቱን የአየር ትራፊክ አስተዳደር ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።


ከበርሊን አውሮፕላን ጣቢያ የሚነሱ እና የሚመለሱ መደበኛ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/one-day-strike-at-13-german-airports-including-the-main-hubs-brings-most-flights-to-a-halt/8005589.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/one-day-strike-at-13-german-airports-including-the-main-hubs-brings-most-flights-to-a-halt/8005589.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 21:06:45 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/81e30477-6c01-4d9b-300a-08dd5c897904_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አባ ፍራንሲስ የቫቲካንን የጾም ጉባኤ በርቀት እየተከታተሉ ነው</title>
            <description>የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት አባ ፍራንሲስ በፋሲካ ጾም ወቅት የሚደረገውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ጉባኤ ሮም ከሚገኘው ሆስፒታል በርቀት በመከታተል ላይ መኾናቸው ታውቋል።


ከገጠማቸው የሳምባ ምች በማገገም ላይ ያሉት አባ ፍራንሲስ ከሆስፒታል አልጋቸው ላይ ሆነው ጉባኤውን በቪዲዮ በመከታተል ላይ ሲኾኑ፣ የጉባኤው ተሳታፊዎች ግን እርሳቸውን ማየትም ሆነ መስማት  እንደማይችሉ የአሶስዬትድ ፕረስ ዘገባ አመልክቷል።


የአንድ ሳምንቱ ጉባኤ፣ እስከ ፋሲካ የሚቆየው የቤተ ክርስቲያኗ ዐብይ ጾም በሚጀምርበት ወቅት በየዓመቱ የሚካሄድ ሲሆን፣ አባ ፍራንሲስም በርቀት ከሌሎቹ የቤተክርስቲያኗ ጳጳሳት ጋራ በጉባኤው እንደሚሳተፉ ቫቲካን አስታውቃለች፡፡


ለ12 ዓመታት ሊቃነ ጳጳስነት የቆዩት አባ ፍራንሲስ በሕመም መያዛቸው ቀጣዩ የጵጵስና ዘመናቸው ምን ሊሆን...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8005521.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8005521.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 20:45:12 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5b3060ae-b036-4ea7-0a17-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሰሜን ባህር ላይ ሁለት መርከቦች ተጋጩ</title>
            <description>አንድ ነዳጅ አመላላሽና አንድ የሸቀጥ አመላላሽ መርከብ በሰሜን ባህር ላይ ተጋጭተው 32 ሰዎች መጎዳታቸውንና ወደ ባህር ዳርቻ እንዲወጡ መደረጉን አንድ የእንግሊዝ ወደብ ኅላፊ አስታውቀዋል።


የተጎጂዎቹ ሁኔታን ወዲያውኑ ማወቅ እንዳልተቻለ ያመለከተው የአሶስየትድ ፕረስ ዘገባ፣ የእንግሊዝ የባህር ድንበር ኅይሎች አንድ አውሮፕላንን ጨምሮ በርካታ ነፍስ አድን ጀልባዎችንና አንድ ሄሊኮፕተር ማሰማራታቸውን አስታውቋል።


ከተጋጩት መርከቦች አንደኛው የአሜሪካንን ባንዲራ የሚያውለበልብ ሲኾን ሌላኛው ደግሞ የፖርቹጋልን ባንዲራ የሚያውለበልብ መሆኑም ታውቋል። የአሜሪካኑን ባንዲራ የሚያውለበልበውና ኬሚካልና ነዳጅ የሚያመላለሰው መርከብ ከግሪክ የተነሳ ሲሆን፣ የፖርቹጋልን ባንዲራ የሚያብለበልበው መርከብ ደግሞ ከስኮትላንድ ተነስቶ ወደ ኔዘርላንድ በማቅናት ላይ ነበር ተብሏል።


ግጭቱ...</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/port-chief-says-32-casualties-brought-ashore-after-ships-collide-and-catch-fire-in-north-sea-/8005440.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/port-chief-says-32-casualties-brought-ashore-after-ships-collide-and-catch-fire-in-north-sea-/8005440.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 19:38:41 +0300</pubDate>
            <category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0AF8478F-7B44-40BA-8802-5E7F9059AAEB_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        </channel></rss>