<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>ዓለምአቀፍ - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/3737</link>
        <description>International news, features</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>ዓለምአቀፍ - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/3737</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Sat, 25 Apr 2026 04:24:37 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zii$qejg$i" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>ሚሳይል መስሪያ ግብአት በመጫን የተጠረጠረችው ሁለተኛ የኢራን መርከብ ከቻይና ተነሳች</title>
            <description>ከቻይና የሚሳይል ነዳጅ መስሪያ ቁልፍ ግብአቶችን ጭናለች ተብላ በምዕራባዊያን የዜና ዘገባዎች  የተጠረጠረችው ሁለተኛዋ የኢራን  መርከብ ወደ ኢራን እያመራች መሆኑን የቪኦኤ ልዩ የትንታኔ ዘገባ አመልክቷል፡፡
የመርከብ እንቅስቃሴ ክትትል ድረ-ገጾች እንደሚያሳዩት የኢራን ባንዲራ የሚያውለበልበው ጃይራን የተባለው የጭነት መርከብ፣ ከቻይና ይነሳል ተብሎ ከተጠበቀበት ጊዜ ከአንድ ወር በኋላ ዘግይቶ ባለፈው ሰኞ መነሳቱ ተጠቅሷል፡፡
በጥር እና በየካቲት  ዘ ፋይናንሺያል ታይምስ፣ ዘ ዎል ስትሪት ጆርናል እና ሲ ኤን ኤን ባቀረቧቸው ዘገባዎች፣ ቴህራን  በሚሳይል ነዳጅ ውስጥ ጥቅም ላይ የሚውለውን 1,000 ሜትሪክ ቶን ኬሚካል (ሶዲየም ፐርክሎሬት) ለመጫን ከምትጠቀምባቸው ሁለት መርከቦች መካከል ጃይራን አንዱ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡
ሦስቱ የዜና ማሰራጫዎች ስማቸው ያልተጠቀሱ የምዕራባውያን የስለላ ምንጮችን ጠቅሰው እንደተናገሩት የተጠቀሱት ኬሚካሎች ለኢራን 260 መካከለኛ ርቀት ሚሳይሎችን ማምረት ያስችላሉ፡፡
በዘገባዎቹ ጎልቦን በሚል ስያሜ የተጠቀሰው ሌላኛው የኢራን የጭነት መርከብ፣ እ ኤ አ የካቲት 13  ከምሥራቃዊ ቻይና ብሩክ አባስ ወደተባለው የኢራን ወደብ ያደረገውን የ19 ቀናት ጉዞ አጠናቋል፡፡
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጃይራን ከቻይና መነሳት አስመልክቶ ከቪኦኤ ለቀረበለት ጥያቄ ምንም አስተያየት አልሰጠም፡፡ በኒውዮርክ የሚገኘው የኢራን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሚሽንም ባለፈው ማክሰኞ በኢሜል ለተላከከለት ተመሳሳይ የቪኦኤ ጥያቄ ምላሽ አልሰጠም።
ባለፈው ወር የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለቪኦኤ እንደተናገረው፣ ኢራን ኬሚካሎቹን ለማስመጣት፣ ጎልቦን እና ጃይራን የተባሉ መርከቦችን እንደምትጠቀም በፋይናንሺያል ታይምስ እና ዎል ስትሪት ጆርናል ከወጡ ዘገባዎች ተመልክቷል፡፡
ቃል አቀባዩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በደህንነት መረጃ ጉዳዮች ላይ ምንም ዐይነት አስተያየት ባይሰጥም &quot;ለኢራን ሚሳይል ወይም ሌሎች የጦር መሳሪያ ፕሮግራሞች ሊጠቅሙ የሚችሉ እቃዎች፣ መሣሪያዎች እና ቴክኖሎጂዎች መስፋፋትን መከላከል ላይ ማትኮሩን እና ኢራንን በማዕቀብ ተጠያቂ ማድረጉን ቀጥሏል&quot; ብለዋል ።
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ ማኦ ኒንግ፣ እ ኤ አ ጥር 23 በዜና ማሰራጫዎቹ ስለቀረቡት ዘገባዎች በሰጡት ምላሽ ፣ ቻይና፣ በራሷ የኤክስፖርት ቁጥጥር እና፣ በዓለም አቀፍ ግዴታዎች እንደምትገዛ ጠቅሰው፣  እንደ ህገ ወጥ የተናጠል ማዕቀቦች የምትቆጥራቸውን የሌሎችን ሀገሮች ተጽዕኖ እንደማትቀበል ተናግረዋል፡፡  
ባለፈው ወር የቻይና መንግሥት የመገናኛ ብዙሃን ስለ ጃይራን ጉዞ ምንም ተናግረው አያውቁም፡፡ በቻይና ማህበራዊ ሚዲያ መድረኮችም ስለ ኢራን መርከብ የተደረገ ውይይት እንዳልነበረ የቪኦኤ የማንዳሪን ቋንቋ አገልግሎት ዘገባ አመልክቷል፡፡
መሠረቱን ኒው ዮርክ ያደረገ ፣ የፖለቲካዊ ስጋቶች ጉዳይ አማካሪ ተቋም፣ ዩሬዥያ ቡድን ከፍተኛ የኢራን ተንታኝ የሆኑት፣ ግሪጎሪ ብሩው፣ &quot;ኢራን፣ ጃይራንን ከመላኳ በፊት፣ ጎልቦን የተባለው ሌላኛው መርከብ ጉዞውን ክልከላ ሳይገጥመው ለማጠናቀቅ ይችል እንደሆነ ለመፈተሽ ፈልጋ ሊሆን ይችላል&quot; ብለዋል ።
ብሩው አያይዘውም &quot;በአሜሪካ ማዕቀብ ሥር ከሆነው የኢራን ሚሳይል ኢንዱስትሪ ጋር የተያያዙ በጣም ሚስጥራዊነት ያላቸው ቁሶችን የያዙ መርከቦች የመያዝ አደጋ ተጋርጦባቸዋል፣ ኢራናውያንም ይህን አውቀውታል&quot; ብለዋል ።
በጂም ሪሽ እና በፒት ሪኬትስ የሚመሩ ስምንት ሪፐብሊካን ሴነተሮች፣ እ ኤ አ የካቲት 4 ቀን ስለ ኢራን-ቻይና የኬሚካል ትብብር ደባ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ደብዳቤ ልከዋል፡፡
 የዜና ማሰራጫዎቹ ዘገባዎች ትክክለኛ ከሆኑ ከአሜሪካ ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር “አሁን ጉዞ ላይ የሚገኘውን ጭነት ጣልቃ ገብተው እንዲያስቆሙ” አሳስበዋል ።
በቅርቡ ጎልቦን ከቻይና ወደ ኢራን ባደረገው ጉዞ መንገድ ላይ መያዙን የሚያሳይ ምንም ምልክት አልታየም።
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ስለ ደብዳቤው ከቪኦኤ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፡- “ከምክር ቤት ጋር በሚደረጉ መልእክቶች ላይ አስተያየት አንሰጥም” ብለዋል። 
የሪኬትስ ቢሮም ሩቢዮ ከሴነተሮቹ ለተላከላቸው ደብዳቤ ምላሽ ሰጥተው እንደሆነ ከቪኦኤ ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ አልሰጠም።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/iran-china-missile-scheme-/8010868.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/iran-china-missile-scheme-/8010868.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 19:50:09 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/73570913-c12b-459d-b0a3-828c76588f8a_cx0_cy18_cw0_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አይኤምኤፍ እና ኢትዮጵያ በዋጋ ግሽበት ትንበያ ተለያዩ</title>
            <description>. ትንበያዎቹ &quot;የተለያዩ ብቻ ሳይኾኑ ከእውነታውም የራቁ ናቸው&quot; - ባለሞያ
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ)፣ በቅርቡ ስለ ኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ያወጣው ትንበያ፣ እ.ኤ.አ በ2025፣ 25 ከመቶ መድረሱን ይገልጻል፡፡ የዋጋ ንረቱ አኹን ካለበት ሁለት አኀዝ ወደ ነጠላ አኀዝ ለመውረድ እስከ 2028 ሊቆይ እንደሚችልም አይኤምኤፍ ተንብይዋል፡፡
በአንጻሩ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የዋጋ ግሽበቱ እየወረደ መምጣቱንና አኹን ከ15 እስከ 16 በመቶ ዝቅ ማለቱን ይናገራል፡፡
በለንደን የሚገኙት የፋይናንስ እና የምጣኔ ሀብት ባለሞያ ዶር. አብዱልመናን መሐመድ ሃምዛ ግን፣ የአይኤምኤፍም ኾነ የኢትዮጵያ መንግሥት ቁጥሮች፣ &quot;የተለያዩ ብቻ ሳይኾኑ ከእውነታው የራቁ ናቸው፤&quot; ይላሉ፡፡
ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ አጭር ቆይታ ያደረጉት ዶር. አቡዱልመናን፣ በአይኤምኤፍ እና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል ያለውን የትንበያ ልዩነት አብራርተዋል፡፡ ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይይ ይከታተሉ።
   የቪኦኤ ዋትስአፕ ቻናል ይከተሉ
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/imf-ethiopia-s-inflation/8010710.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/imf-ethiopia-s-inflation/8010710.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 14 Mar 2025 18:06:32 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ደረጀ ደስታ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5ca8d0af-a26a-49ff-0900-08dd5c8b1668_cx0_cy12_cw0_w800_h450.jpeg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሩሲያ የተቆጣጠረቻቸውን የዩክሬን ግዛቶች እንደያዘች መቀጠል ትሻለች</title>
            <description>ሩሲያ በዩክሬን የምታካሒደውን ጦርነት ለማስቆም፣ አሜሪካ የምታደርገው ጥረት በክሬምሊን ላይ ጫናን ፈጥሯል። ይኹንና ሞስኮ አሁንም በቀጠለችው ጥቃት ተጨማሪ የዩክሬን ስፍራዎችን ተቆጣጥራለች፡፡
በሩሲያ የሚገኙ አንዳንድ ባለሥልጣናት ደግሞ፣ በድርድሩ ሩሲያ ምንም ነገር አሳልፋ መስጠትን እንደማትሻ በመናገር ላይ ናቸው።
የቪኦኤው ጄፍ ከስተር የላከውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/russia-ukraine-concessions/8009965.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/russia-ukraine-concessions/8009965.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 23:21:08 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/fce71d0f-fae4-482a-0ed0-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኤኮዋስ የፀረ-ሽብር ጦሩ በተጠንቀቅ እንዲቆም አደረገ</title>
            <description>የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ &quot;ኤኮዋስ&quot; የቀጠናው የጦር ኃይል በተጠንቀቅ እንዲጠባበቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል። የጸጥታ ተንታኞች ርምጃውን ያደነቁ ቢሆንም፣ የተቋሙ ሦስት አባል ሀገራት በቅርቡ መውጣታቸው ውጤታማነቱን አጠራጣሪ እንደሚያደርገው ተገልጿል።
የናይጄሪያ መከላከያ ሚኒስትር ሞሃመድ ባዳሩ አቡባካር የኤኮዋስ የጦር ኃይል በተጠንቀቅ ላይ እንደሚሆን ያስታወቁት፣ ትላንት ማክሰኞ በተካሄደው የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት ጥምረት የሆነው ኤኮዋስ 43ኛ መደበኛ የፀጥታ ስብሰባ ወቅት ነው።
5 ሺሕ ወታደሮች እንደሚኖሩት የሚጠበቀው የጦር ኃይል፣ በቀጠናው የሚካሄዱትን ሽብርተኝነት እና ድንበር ዘለል ወንጀሎች ለመከላከል የሚደረግ ቀጠናዊ የፀጥታ እንቅስቃሴ አካል ነው።
አቡበከር በንግግራቸው &quot;ይህ  ኃይል በተጠንቀቅ እንዲቆም ሆኖ ሥራ መጀመሩ፣ የሽብርተኝነትን መስፋፋት ለመጋፈጥ እና የዜጎቻችንን ደኅንነት ለማረጋገጥ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት ያሳያል&quot; ብለዋል።
በተጨማሪ የኤኮዋስ የፀጥታ ኃላፊዎች በጊኒ ባህረ ሰላጤ የባህር ላይ ደኅንነት እና የሰላም ድጋፍ ለማድረግ በሚቻልበት መንገድ ላይም ተወያይተዋል።
የምዕራብ አፍሪካው ተቋም አካል የነበሩት ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር ከኤኮዋስ ተገንጥለው  &quot;የሳህል አገሮች ጥምረት&quot; የተባለ ኮንፌዴሬሽን አቋቁመዋል። ወታደራዊ አመራር ያላቸው ሦስቱም ሀገራት፣ ኤኮዋስን &quot; የአባል ሀገራቱን ጥቅም ከማስጠበቅ ይልቅ የውጭ ሀገራት ጥቅም ማስፈፀሚያ ሆኗል&quot; ሲሉ ይከሳሉ። 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ecowas-regional-bloc-activates-counterterror-force/8009724.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ecowas-regional-bloc-activates-counterterror-force/8009724.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 20:42:16 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9a78e2c0-aa66-46a3-95bd-53dfc7c9bc06_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ትረምፕ ከአውሮፓ በሚገቡ የአልኮል መጠጦች ላይ ከበድ ያለ ታሪፍ እንደሚጥሉ አስታወቁ</title>
            <description>የአውሮፓ ኅብረት ከአሜሪካ በሚገባው ዊስኪ ላይ የ50 በመቶ ታሪፍ መጣሉን ተከትሎ፣ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ከአውሮፓ በሚገባው የወይን ጠጅ፣ ሻምፓኝና ሌሎች የአልኮል መጠጦች ላይ የ200 በመቶ ታሪፍ እንደሚጭኑ አስጠንቅቀዋል።
የ27 ሃገራት ስብስብ የሆነውን የአውሮፓ ኅብረት &quot;በዓለም የከፋው ታክስና ታሪፍ ጣይ&quot; ሲሉ የገለጹት ትረምፕ፣ &quot;እ.አ.አ በ1993 ሲመሠረት ዓላማው &quot;ከአሜሪካ የኢኮኖሚ ጥቅም ለማግኘት ነው&quot; ብለዋል። 
ባለፈው አንድ ወር ከአሜሪካ ከፍተኛ የንግድ ሸሪኮች፣ ማለትም ከሜክሲኮ፣ ካናዳ፣ ቻይናና የአውሮፓ ኅብረት ጋራ የታሪፍ ውዝገብ ውስጥ የገቡት ትረምፕ፣ ታሪፉን መጣሉ አስፈላጊ የሆነው ሃገራቱ ወደ አሜሪካ የሚገባውን አደገኛ  ዕጽ እና መድሃኒት እንዲያስቆሙና እንዲሁም የሸቀጥ አምራቾች በውጪ ያላቸውን ፋብሪካ ዘግተው ወደ አሜሪካ እንዲመጡ ለማስገደድ መሆኑን ይገልጻሉ።
ትረምፕ ትላንት ረቡዕ የአውሮፓ ኅብረትን ጨምሮ ብረታብረት ወደ አሜሪካ በሚልኩ 35 ሃገራት ላይ የ25 በመቶ ታሪፍ ጥለዋል። አውርፓውያኑ በአጸፋው ከአሜሪካ በሚላከው የ28 ቢሊዮን ዶላር ሸቀጥ ላይ ታሪፍ ጥለዋል። ካናዳ በበኩሏ 20.7 ቢሊዮን ዶላር በሚጠጋ የአሜሪካ ሸቀጥ ላይ ታሪፍ ጥላለች፡፡
አውሮፓውያኑ የሚጥሉት ታሪፍ ያተኮረው እንደ ትረምፕ ባሉ ሪፐብሊካኖች ቁጥጥር ሥር ካሉ ግዛቶች በሚላኩ ሸቀጦች ላይ ነው። ከካንሳስ እና ኔብራስካ በሚላከው ሥጋና ዶሮ፣ ከአላባማ እና ጆርጂያ በሚላከው የእንጨት ውጤት፣ እንዲሁም ከኬንተኪ እና ቴነሲ በሚላከው የአልኮል መጠጥ ላይ ነው። በብረት እና አሉምነም ላይ አንዱ በሌላው ላይ በሚጥለው ታሪፍና ውዝግብ መሃል የአልኮል አምራቾችም ሰለባ ሆነዋል።
የአውሮፓ ኅብረት ለአሜሪካ ዊስኪ ትልቁ ገበያዋ ሲሆን፣ ከዚህ በፊት የነበረው ታሪፍ መነሳቱን ተከትሎ ባለፉት ሦስት ዓመታት ወደ አውሮፓ የሚላከው የአሜሪካ ዊስኪ በ60 በመቶ ጨምሮ ነበር። 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/trump-tariffs/8009704.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/trump-tariffs/8009704.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 20:34:24 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a1531c9d-c3db-422b-0e43-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከታቀደው በላይ የቆዩትን ጠፈርተኞች ለመተካት ሊላክ የነበረው የስፔስ ኤክስ ተልእኮ ዘገየ</title>
            <description>ጠፈር ላይ ከጊዜያቸው በላይ የቆዩ የ ዩናይትድ ስቴትስ የኤሮኖቲክስ እና ጠፈር ምርምር (ናሳ) ጠፈር ተመራማሪዎችን ለመተካት ወደ  ሊላክ የነበረው የስፔስ ኤክስ መንኮራኩር የሮኬት ማስወንጨፊያ እክል ስለገጠመው ወደ ጠፈር ጣቢያው የሚያደርገው በረራ ዘግይቷል፡፡
ቡች ዊልሞር እና ሱኒ ዊሊያምስ የተባሉት ጠፈርተኞች ከዘጠኝ  ወራት  ቆይታ በኋላ ወደ ምድር ከመመለሳቸው በፊት እነሱን የሚተካ የጠፈርተኞች ቡድን ከዓለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ መድረስ ይኖርበታል፡፡
ይሁን እንጂ ከኬኔዲ የጠፈር ማእከል ሊወነጨፍ ተዘጋጅቶ የነበረውን ፋልከን ሮኬት እክል ገጥሞታል፡፡
አሶስየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ሮኬቶቹን ደግፈው ከያዙት መሳሪያዎች መካከል አንዱን የሚቆጣጠረው የማስወንጨፊያ ክፍል (የማስነሻ ፓድ)  ችግር የገጠመው መኾኑን መሀንዲሶች በመናገራቸው ስፔስ ኤክስ (SpaceX) ተልዕኮውን እንዲያዘገይ ተደርጓል፡፡
ችግሩ የታወቀው ሮኬቱ ከመወንጨፉ ከአራት ሰዐታት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ሲሆን ተልእኮ ሙሉ ለሙሉ እንዲሰረዝ የተደረገው ከመወንጨፊያ አንድ ሰዓት ያነሰ ጊዜ ሲቀረው መሆኑ ተመልክቷል፡፡
ስፔስ ኤክስ ተልእኮው እንደገና የሚጀመርበትን ቀን መቸ እንደሚኾን ባይረጋገጥም ቀጣዩ ሙከራ ኅሙስ ምሽት ሊደረግ እንደሚችል ተገልጿል ((ኤፒ)፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/https-www-voanews-com-a-launch-pad-problem-delays-spacex-flight-to-replace-nasa-s-stuck-astronauts-8009048-html/8009493.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/https-www-voanews-com-a-launch-pad-problem-delays-spacex-flight-to-replace-nasa-s-stuck-astronauts-8009048-html/8009493.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 18:18:13 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5ee089cb-5149-4b45-0757-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኩዌት ከአደገኛ ዕጽ ጋራ በተያያዘ የታሰሩ የቀድሞ ሠራዊት አባላት ጨምሮ አሜሪካዊ እስረኞችን ለቃለች</title>
            <description>ኩዌት ከአደገኛ ዕፅ ጋራ በተያያዘ ክስ ተመስርቶባቸው ለዓመታት በእስር ላይ የነበሩ የቀድሞ ሠራዊት አባላትና እና የወታደራዊ ተቋራጭ ሠራተኞችን ጨምሮ አሜሪካውያን እስረኞችን ለቃለች።
የአሜሪካ መንግሥት በውጭ ሀገር የታሰሩ አሜሪካውያንን አስለቅቆ ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ ባደረገው ጥረት የተፈቱት እስረኞች ወደ ኒውዮርክ ተወስደዋል፡፡
እስረኞቹ የተለቀቁት በቅርቡ ዋናው የትረምፕ አስተዳደር የታጋቾች ጉዳይ መጓዛቸውን ተከትሎ መኾኑም ተመልክቷል፡፡
በአሜሪካዊያን ታጋቾች እና እስረኞች ጉዳይ የሚሰሩት አማካሪው ጆናታን ፍራንክ እስር ላይ ከነበሩ ስድስት እስረኞች ጋራ በመኾን ለኩዌት መንግሥት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን “ደንበኞቼና ቤተሰቦቻቸው የኩዌት መንግሥት ላሳየው ሰብአዊነት ምስጋናቸውን ያቀርባሉ”ሲሉም በመግለጫቸው ተናግረዋል፡፡ ደንበኞቻቸው ጥፋት የሌለባቸው ንጹሐን መኾናቸውንም ፍራንክ አያይዘው ገልጸዋል።
ምንም እንኳን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስለ ሁኔታው ምንም ዐይነት አስተያየት ባይሰጥም፣ ከኩዌት እስር ቤት ተጨማሪ አሜሪካውያን እስረኞች ይፈታሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በነዳጅ የበለጸገችው እና በመካከለኛው ምስራቅ የአሜሪካ ቁልፍ አጋር የሆነችው ኩዌት፣ ጉልህ የሆነ የአሜሪካ ጦር ኅይል የሠፈረባት እና ብዙ የአሜሪካ ሥራ ተቋራጮች የሚገኙባት ሀገር ናት፡፡
ኩዌት በርካቶችን ለእስር የዳረጋቸውን ጠንካራ የአደገኛ እፅ ሕግጋትን የምታስፈጽም ሲሆን እስረኞች ላይ የተለያዩ የሰብአዊ አያያዝ በደሎች እንደሚፈጸሙ ቤተሰቦች ይናገራሉ፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኩዌት የአደገኛ እፅ ሕጎች፣ የሞት ቅጣትን ጨምሮ ረጅም እስራት እና ከባድ ቅጣት እንደሚያስከትሉ ያስጠነቅቃል፡፡
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ወደ ሥልጣን ከተመለሱ በኋላ አስተዳደራቸው ከሩሲያዊው ማርክ ፎጌል እና ከቤላሩስ የመጣውን ሌላ አሜሪካዊ ዜጋን ጨምሮ በእስር ላይ የሚገኙ በርካታ አሜሪካውያን እንዲፈቱ አድርጓል።


   የቪኦኤ ዋትስአፕ ቻናል ይከተሉ
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/kuwait-frees-a-group-of-jailed-americans-including-contractors-held-on-drug-charges/8009398.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/kuwait-frees-a-group-of-jailed-americans-including-contractors-held-on-drug-charges/8009398.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 17:03:57 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/2b3bac0b-d475-42e6-0758-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቀረጡ ጉዳይ በዩናይትድ ስቴትስ ኢኮኖሚ ላይ ያስከተለው አለመረጋጋት</title>
            <description>የቀረጡ ጉዳይ ከዋጋ ንረት ስጋት ጋራ ተዳምሮ በፈጠረው አለመረጋጋት የተነሳ ሰኞ እና ማክሰኞ የዩናይትድ ስቴትስ የአክሲዮን ገበያ አሽቆልቁሏል፡፡
በአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ እና በሕዝብ ብዛት ትልቋ የካናዳ ጠቅላይ ግዛት ኦንታሪዮ ጠቅላይ ሚንስትር ደግ ፎርድ መካከል የሁለቱን ሀገሮች የንግድ ውዝግብ በሚመለከት የተደረገውን ልውውጥ ጠቅሳ የቪኦኤ የኋይት ሐውስ ዘጋቢ ካሮላይን ፕሬሱቲ የላከችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
የቪኦኤ ዋትስአፕ ቻናል ይከተሉ 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8009199.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8009199.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 13 Mar 2025 13:56:26 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0c7bb9ac-79cd-4505-0e03-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በግሪንላንድ ምርጫ ያሸነፈው ፓርቲ የትረምፕን ዕቅድ ተቃወመ</title>
            <description>በግሪንላንድ በተካሄደው የምክር ቤት ምርጫ፣ ሀገሪቱ በሂደት ከዴንማርክ ነጻ እንድትወጣ የሚደግፈው ዴሞክራቲት ፓርቲ ያልተጠበቀ ድል ተቀዳጅቷል፡፡
የትላንት ማክሰኞው ምርጫ የተካሄደው፣ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ደሴቲቱን ለመጠቅለል ያላቸውን እቅድ ይፋ ባደረጉበት ድባብ ውስጥ ነው፡፡
ዲሞክራቲት ፓርቲ “የግዛቲቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወስኑት የግሪላንድ ነዋሪዎች ናቸው” በማለት የትረምፕን ንግግር ሲቃወም ቆይቷል፡፡
“የምርጫው ውጤት ግሪንላንድ አትሸጥም የሚለውን ግልፅ መልዕክት ለትረምፕ ማስተላለፍ አለበት” ሲሉ የፓርቲው መሪ ጄንስ ፍሪደሪክ ኒልሰን ለስካይ ኒውስ ተናግረዋል።
&quot;እኛ አሜሪካዊ መሆን አንፈልግም። ፣ ዴኒሽ መኾንም አንፈልግም። የምንፈልገው ግሪንላንድነታችንን  ነው። ወደፊትም  ነፃነታችንን እንፈልጋለን። የራሳችንን ሀገር እርሳቸው በሚሰጡት ተስፋ ሳይሆን በራሳችን መገንባት እንፈልጋለን&quot; ብለዋል።
ግሪንላንድ ሞባይል ሞባይል ስልክ  እና የታዳሽ ኅይል ቴክኖሎጂን ጨምሮ   ለመሥራት  አስፈላጊ ግብዓት የኾኑ  ውድ የምድር ማዕድናት ክምችት የያዘች ናት፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ አየር ኃይል የጦር ሰፈር የሚገኝባት  ስትኾን ለሰሜን አትላንቲክ የአየር እና የባህል መስመሮች ቁልፍ የስትራቴጂ ስፍራ ናት፡፡
ትረምፕ ግሪንላንድን የመቆጣጠር ፍላጎታቸውን በግልጽ ተናግረዋል፡፡ ባለፈው ሳምንት ለዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤቶች የጋራ ጉባኤ ባሰሙት ንግግር  &quot;ዩናይትድ ስቴትስ “በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ታገኛዋለች&quot; ሲሉ ሐሳባቸውን ገልጸዋል።
56 ሺሕ የሕዝብ ብዛት ያላት ግሪንላንድ ከ300 ዓመታት በፊት የዴንማርክ ቅኝ ግዛት የነበረች ሲኾን  አሁንም የውጭ እና የመከላከያ ፖሊሲዋን የምትቆጣጠረው ዴንማርክ ነች፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8008519.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8008519.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 22:30:23 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/8231741b-316a-4e22-0b45-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በአርጀንቲናው ጎርፍ የሞቱት ሰዎች 16 ሲደርስ ሁለት ሕጻናት የደረሱበት ጠፍቷል</title>
            <description>ባሂያ ብላንካ በምትባለው የአርጀንቲና የወደብ ከተማ በደረሰው የጎርፍ መጥለቅለቅ የሞቱት ሰዎች ቁጥር አሻቅቦ 16 መድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።
ጥልቅ ውሃ ዋናተኞች ጎርፉ የወሰዳቸውን ሁለት ሕጻናት ፍለጋ ላይ ተሰማርተዋል፡፡
ከቦይኖ ሳይረስ ክፍለ ግዛት በስተደቡብ የምትገኘው ከተማ ከሀገሪቱ ትላልቅ ወደቦች አንዱ የሚገኝባት ስትኾን በዓመት የሚጥለው መጠን ያለው ዝናብ ዓርብ ዕለት በጥቂት ሰዓት ውስጥ ወርዶባታል። መንገዶች እንዲሁም በርካታ መንደሮች በአንድ ጊዜ በጎርፍ ተጥለቅልቀዋል፡፡
በጎርፉ 400 ሚሊዮን ዶላር ግምት ያለው መሠረተ ልማት እንደወደመ የከተማዋ ከንቲባ ፌዴሬኮ ሱስቤልየስ ተናግረዋል። 16 ሰዎች መሞታቸው እንደተረጋገጠ የገለጹት ከንቲባው ቁጥሩ ይጨምራል የሚል ስጋት መኖሩንም አክለዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአንድ ዓመት እና የአምስት ዓመት ህጻናት የሆኑ እህትማማቾች በጎርፉ መወሰዳቸው መላ ሐገሪቱን አሳዝኗል፡፡ ሁለቱ ልጆች ከእናታቸው ጋር &quot;ቫን&quot; መኪና ጣሪያ ላይ ወጥተው እንደነበረ እና ጎርፉ ደርሶ ይዟቸው እንደሄደ የከተማዋ ባለሥልጣናት ተናግረዋል፡፡ ዋናተኞች አሁንም በአንድ ሜትር ከፍታ አካባቢውን ባጥለቀለው ውሃ ውስጥ ፍለጋ ቀጥለዋል፡፡
የአርጀንቲና መንግሥት በጎርፉ ለተጎዱት አካባቢዎች አስቸኳይ ጥገና ሥራ የሚውል 9 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር መመደቡ ተገልጿል፡፡
ባሂያ ብላንካ ከተማ ከአሁን ቀደምም ከአየር ንብረት ጋር ተያያዥ አደጋ ያጋጠማት ሲሆን እ አ አ በ2023 የጣለው ኃይለኛ ዝናብ 13 ሰዎች ሲገድል መጠነ ሰፊ የመሠረተ ልማት አውታሮች አውድሟል፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/argentina-flooding-death-toll-rises-to-16-two-girls-missing/8008222.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/argentina-flooding-death-toll-rises-to-16-two-girls-missing/8008222.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 19:54:58 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤኤፍፒ AFP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/440bbb0b-7eb5-413e-948b-399676398dfd_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የፓኪስታን ጦር ወደ 200 የሚጠጉ የባቡር ተሳፋሪዎችን ሕይወት አተረፈ</title>
            <description>ፓክሲታን ውስጥ ዛሬ ረቡዕ በታገተው ጃፈር ፈጣን ባቡር ላይ በተካሄደ ወታደራዊ ዘመቻ የሠራዊቱ አባላት 190 ተሳፋሪዎችን ሲታደጉ 30 አሸባሪዎችን መግደላቸው ተገለጸ።
ርምጃው የተወሰደው ደቡባዊ የባሎቺስታን ግዛት ውስጥ ትላንት በተካሄደበት ጥቃት ለ24 ሰዓታት ዋሻ ውስጥ እንዲያድር የተገደደውን ባቡርና ተሳፋሪዎችን ለማስለቀቅ በተደረገ ጥረት ነው፡፡
ወደ 450 የሚጠጉ ሰዎችን አሳፍሮ ከኩዌታ ወደ ፔሻዋር በመጓዝ ላይ የነበረው ባቡር የቦምብ እና የተኩስ ጥቃት የደረሰበት ትላንት ማክሰኞ መኾኑን ተነግሯል፡፡
ጥቃቱንም ተከትሎ ባቡሩ በሲቢ አቅራቢያ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ ከ24 ሰዓታት በላይ ታግቶ እንዲቆይ መደረጉ ተገልጿል።
ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደው የባሎክ ነፃ አውጪ ጦር (BLA) 200 ታጋቾችን በተለይም የደኅንነት እና የስለላ አባላትን መያዙን ገልጾ፣ የፖለቲካ እስረኞች በ48 ሰዓት ውስጥ እንዲፈቱ ጠይቋል።
በጥቃቱ የተጎዱ በትንሹ 37 ሰዎች ህክምና እየተደረገላቸው ሲኾን ቆስሎ የነበረው የባቡሩ ሹፌር ሕይወቱ ማለፉ ተመልክቷል።
ባለሥልጣናት የአደጋ ጊዜ ቡድኖችን፣ የነፍስ አድን ባቡርን እና አምቡላንሶችን ወደ ቦታው ልከዋል፣ ነገር ግን አካባቢው ተራራማ በመሆኑ የስልክ መስመሮች ችግር ተደራሽነቱን ከባድ አድርጎታል።
የባሎክ ነፃ አውጪ ጦር በፓኪስታን ጥቃቱን አጠናክሮ በመቀጠሉ “ከሽብርተኝነት ጋራ በተያያዘ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ካለፈው ዓመት በ45 ከመቶ ከፍ ብሏል” ሲል ዓለም አቀፍ የሽብርተኝነት ጠቋሚ ድርጅት አመልክቷል።
ባሎክ ባሎቺስታን ውስጥ የተሰማሩ የፓኪስታን ባለ ሀብቶች እና የቻይና ኢንቨስትመንቶች የአካባቢውን ሕዝብ ይጎዳሉ በሚል ይቃወማል፡፡
ባሎክ በፓኪስታንና በዩናይትድ ስቴትስ በጸረ ሽብርተኝነት የተፈረጀ ድርጅት ነው፡፡
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/pakistan---train-attack/8008084.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/pakistan---train-attack/8008084.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 17:44:14 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/a1642250-3b39-4fc6-8f72-00ccca9eebe4_cx0_cy3_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዩክሬን ሩሲያ አስቸኳይ የ30-ቀናት ተኩስ አቁም ተከትሎ የቡድን 7 ሀገራት ይወያያሉ</title>
            <description>በኢንዱስትሪ የበለጸጉ የቡድን 7 ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ የሦስት ዓመቱን የሩሲያ ወረራ እየመከተች ላለችው ዩክሬን የሚሰጡትን ድጋፍ ጨምሮ፣ በተለያዩ ጉዳዮች ለበርካታ ቀናት ለመምከር፣ በኩቤክ ካናዳ ይሰበሰባሉ፡፡  
ውይይቱ ዩክሬን እና አሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በሳዑዲ አረቢያ ጂዳ ከተገናኙ በኋላ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬን የምታደርገውን የመረጃ ልውውጥ እና የፀጥታ ድጋፍ እንድምትቀጥል ያሳለፈችውን ውሳኔ ተከትሎ ነው።
ዩክሬን ከሩሲያ ጋራ በሚደረገው ጦርነት “የ30 ቀን አስቸኳይ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም” የሚለውን የአሜሪካ ሐሳብ ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን ትላንት ማክሰኞ አስታውቃለች።
የጀርመኑ መሪ ቻንስለር ኦላፍ ሾልዝ ትላንት ረቡዕ ኤክስ በተሰኘ ገጻቸው እንደተናገሩት “ለዩክሬን ፍትሃዊ ሰላም ወሳኝ እና ትክክለኛ ርምጃ ነው” በማለት የ30 ቀን የተኩስ አቁም ሐሳብን ተቀብለዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ዩክሬን ሐሳቡን መቀበሏ ሩሲያ እንድትስማማ ጫና ይፈጥራል ብለዋል።
ሩቢዮ አያይዘውም &quot;አሁን ይህን ጥያቄ ከተስፋ ጋራ ወደ ሩሲያውያን እንወስዳለን፣ እሺ እንደሚሉም ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ለሰላም እሺ ይላሉ፡፡ ኳሱ አሁን በእነሱ ሜዳ ውስጥ ነው&quot; ብለዋል፡፡
በጂዳ ከሩቢዮ ጋራ የነበሩት የአሜሪካ ብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ ማይክ ዎልትስ፣ በተኩስ አቁም ስምምነቱ ላይ ለመወያየት፣ በቅርቡ ከሩሲያ አቻቸው ጋራ ለመነጋገር አቅደዋል፡፡
ነገ ሐሙስ የኔቶ ዋና ጸሃፊ ማርክ ሩት፣ ዋይት ሐውስን ይጎበኛሉ።
እነዚህ ሁሉ ውይይቶች የሰላሙን ሂደት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚደረገው ጥረት አካል መሆናቸው ተገልጿል።
የዩክሬን ፕሬዝደንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ በአሜሪካ እና ዩክሬን ድርድር ላይ አልተሳተፉም፡፡ ይሁን እንጂ ትላንት ማክሰኞ ምሽት ባደረጉት ንግግር የተኩስ አቁም እቅዱ “አዎንታዊ ጥያቄ” ነው ብለዋል።
ዜለነስኪ አክለውም &quot;አሁን ሩሲያ ተመሳሳይ ነገር እንድታደርግ ማሳመን የዩናይትድ ስቴትስ ጉዳይ ነው&quot; ብለዋል።
ሩሲያ ከተስማማች የተኩስ አቁም ስምምነቱ ወዲያውኑ ተግባራዊ ይሆናል።
ትረምፕ ለቀጣይ ወታደራዊ ርዳታ የዩክሬንን ጥሬ ዕቃ ማግኘትን እንደ ቅድመ ሁኔታ በማስቀመጥ ፍላጎት አሳይተዋል።
የማክሰኞውን ድርድር ተከትሎ ሁለቱም ወገኖች “የዩክሬንን ኢኮኖሚ ለማስፋፋት እና የዩክሬንን የረዥም ጊዜ ብልጽግና እና ደኅንነትን ለማረጋገጥ፣ እንዲሁም የዩክሬንን ወሳኝ የማዕድን ሀብት ለማልማት በተቻለ ፍጥነት ሁሉን አቀፍ ስምምነት ለማድረግ መስማማታቸውን ያወጡት የጋራ መግለጫ ያስረዳል፡፡
 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ubio-ukraine-g7/8008072.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ubio-ukraine-g7/8008072.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 17:36:17 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/c395cd8a-ce8a-4186-9789-c2a0489e14ad_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሩሲያ ሚሳይል ጥቃት በኦዴሣ አራት ሰዎች መግደሉን የዩክሬን ባለሥልጣናት አስታወቁ</title>
            <description>የዩክሬን ባለሥልጣናት በደቡባዊ ዩክሬን የወደብ ከተማ ኦዴሣ፣ ሌሊቱን በደረሰ የሩሲያ ሚሳይል ጥቃት፣ አራት ሶሪያውያን ሲገደሉ፣ በርካቶች ቆስለዋል ሲሉ፣ ዛሬ ረቡዕ አስታወቁ፡፡
የመልሶ ግንባታ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ኦሌክሲ ኩሌባ በቴሌግራም ማኅበራዊ መድረክ ላይ እንደተናገሩት፣ ሚሳይሉ ወደ አልጄሪያ የሚላክ ስንዴ በመጫን ላይ በነበረች የጭነት መርከብ ላይ ጉዳት አድርሷል።
ሩሲያ የዓለምን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ላይ የተሰማሩ ወደቦችን ጨምሮ የዩክሬን መሠረተ ልማቶችን እያጠቃች መኾኑ ተመልክቷል።
ሌላ የሚሳይል ጥቃት በዲኒፕሮፔትሮቭስክ ክልል ውስጥ በምትገኘው የፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ የትውልድ ከተማ ክሪቪ ሪህ ላይ ጉዳት አድርሷል፡፡ በዚህ ጥቃት ቢያንስ አንድ ሰው ሲሞት ዘጠኝ ሰዎች ቆስለዋል ሲሉ የክልሉ ገዥ ተናግረዋል።
አገረ ገዥው ሰርሂ ሊሳክ ክልሉ ከሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥቃት እንደደረሰበት እና በጥቃቱም ከፍተኛ ፎቆች፣ አስተዳደራዊ ሕንፃዎች እና ትምህርት ቤት ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።
የዛፖሪዥያ ክልል ባለሥልጣናት የሩስያ ሰው አልባ አውሮፕላን ሕክምና ተሽከርካሪ ላይ ጉዳት ማድረሱንም ገልጸዋል፡፡
የዩክሬን ጦር ዛሬ ረቡዕ እንዳስታወቀው የሩሲያ ጦር በአንድ ሌሊት ካስወነጨፋቸው 133 ሰው አልባ አውሮፕላኖች ውስጥ 98ቱን መትቶ ማውረዱን አስታውቋል።
ድሮኖቹ የተመቱት “በቼርካሲ፣ ቼርኒሂቭ፣ ዲኒፕሮፔትሮቭስክ፣ ካርኪቭ፣ ክኸርሰን፣ ክምለኒትስኪ፣ ኪይቭ፣ ኦዴሳ፣ ፖልታቫ፣ ሪቪኔ፣ ሱሚ፣ ቴርኖፒል፣ ቪኒትሲያ፣ ዛፖሪዥያ እና ዚሂቶሚር ክልሎች ላይ ነው” ሲል ጦር ሠራዊቱ ይፋ አድርጓል።
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ዛሬ ረቡዕ ፣ 21 የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) አውድሟል፡፡ የአየር መከላከያው ድሮኖቹ የተመቱት በብሪያንስክ፣ ኩርስክ እና ካልጋ ክልሎች እንዲሁም በጥቁር ባህር እና በሩሲያ በተያዘው ክራይሚያ ውስጥ መኾኑን ገልጿል።
የአካባቢዎቹ ባለሥልጣናት በዩክሬን ጥቃት ስለደረሰው ጉዳት እና ውድመት አልገለጹም። 
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/russia-ukraine-fighting/8007992.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/russia-ukraine-fighting/8007992.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 16:33:06 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/773824e6-60de-4dff-3282-08dd5c897904_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የእስራኤል ወግ አጥባቂዎች  ፍልስጤማውያንን ከጋዛ የሚያስወጣ &quot;የፍልሰት ባለሥልጣን&quot; ለማቋቋም አቅደዋል</title>
            <description>የእስራኤል  አክራሪ ወግ አጥባቂዎች  ከ2.3 ሚሊዮኑ ፍልስጤማውያን ብዙዎቹ ጋዛን  ለቀው እንዲወጡ የሚያደርገውን የፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕን እቅድ በደስታ ተቀብለዋል። “ስደትን ማበረታታት ዓለም አቀፍ ሕግን አይጥስም” ይላሉ። ፍልስጤማውያን ግን እቅዱን ውድቅ አድርገውታል።
የእስራኤሉ የገንዘብ ሚኒስትር ቤዛሌል ስሞትሪች ፍልስጤማውያን ጋዛን ለቀው እንዲወጡ ለማበረታታት በመከላከያ ሚኒስቴር ውስጥ &quot;የፍልሰት ባለሥልጣን&quot; እያቋቋሙ መኾኑን ተናግረዋል።
ቤዛሌል ስሞትሪች፣ የእስራኤል የገንዘብ ሚኒስትር “ስደትን ለማበረታታት የምናወጣው እያንዳንዱ ብር፣ ደጋግመን በመታገል ከምንከፍለው  ዋጋ ያነሰ ነው። በጀቱ ለዚህ እቅድ እንቅፋት አይሆንም፣ ይህ ሌላ እቅድ ብቻ አይደለም። በመካከለኛው ምስራቅ እና በእስራኤል ታሪካዊ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል አቅም ነው&quot; ብለዋል።
የኬኔሴት አባል የሆኑት ሲምቻ ሮትማን ይህ &quot;ወደሌላ ቦታ የማዛወር&quot; እቅድ በቅርቡ በግብጽ እና በአረብ ሊግ ከቀረበው እቅድ የበለጠ ተጨባጭ ነው፣ የእነሱ እቅድ ዩናይትድ ስቴትስ፣ በአሸባሪነት የፈረጀችው ሐማስ ትጥቅ ሳይፈታ የፍልስጤም አስተዳደር፣ ጋዛን  እንዲመራ ያስችለዋል።” ይላሉ።
&quot;ሰዎች ሐማስን መልሰን እናቋቁም ፣ ሐማስ ኃይሉን መልሶ እንዲገነባ ሁሉንም ዕድል እንስጥ ይላሉ።” ያሉት ሮትማን “ይህ እንዴት ተጨባጭ መፍትሔ ሊሆን ይችላል? አይደለም ፤ አደገኛ ነው። ለጋዛ አደገኛ ነው። ለጋዛ ሕዝብ አደገኛ ነው፤ እንዲሁም ለአካባቢው ሰላም አደገኛ ነው።” ሲሉ ሀሳቡን አጣጥለውታል።
ቀኝ አክራሪዎቹ የህግ ምሁራን፣ የእስራኤልን የታሪክ እና የግዛት ሉአላዊነት ለማስከበር በሚሟገተው ቡድን ስብሰባ ላይ ሲናገሩ “ስደተኞችን ከጦርነት ቀጠና እንዲወጡ ማበረታት የዓለም አቀፍ ህግን መጣስ አይደለም” ብለዋል ።
የከኮሄሌት ፖሊሲ መድረክ የህግ ምሁር  የሆኑት ዩጂን ኮንቶሮቪች “በጦርነት ጊዜ ስደተኞች እንደሚኖሩ እናውቃለን። ከአፍጋኒስታን፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ስደተኞች። ከሶሪያ ጦርነት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ስደተኞች፣ ከዩክሬን ጦርነት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ስደተኞች። ከእነዚህ ውስጥ አንዳቸውም የዘር ማፅዳት አልተባሉም። አሁን እንደዚህ ዓይነት ስደተኞችን  ሆን ብሎ መፍጠር አይቻልም። በተለይ ጦርነትን ተከትሎ የመጣ በመሆኑ ምክንያት ግን ሊከለከል አይገባም።” ሲሉ ስደተኞችን አስመልክቶ የሚነሳውን የተቃውሞ ሀሳብን ተከላክለዋል።
የእስራኤል ግራ ዘመም (ሊበራል) ድርጅቶች ተወካዮች ግን በዚህ አይስማሙም። በእስራኤል “ሰላም አሁን” ለተሰኘው እንቅስቃሴ የሰፈራ ፕሮጀክት ላይ የሚሰሩ ሃጊት ኦፍራን &quot;ይህ ሰዎችን በፈቃደኝነት ማስወገድ አይደለም። ይህ ማፈናቀል ወይም ማስተላለፍ ነው። የጦር ወንጀል ነው። ሥነ ምግባር የጎደለው ነው። የሰዎችን ህይወት ስቃይ የበዛበት ካደረጋችሁ፣ ሰዎች ከዚያ ቦታ ለቀው መውጣት ይፈልጋሉ፣ በፈቃዳቸው መውጣታቸው ነው ማለት ግን አይደለም።” ይላሉ።
ብዙዎቹ የካንሴት ቡድን አባላት ፣ እ.ኤ.አ. በ2005 እስራኤል ሙሉ ለሙሉ ግዛቱን ለቃ በወጣችበት ወቅት ከጋዛ ሰርጥ የለቀቁት 21 የአይሁድ ሰፈሮች፣  መልሰው እንዲመሰረቱ ጠይቀዋል።
የረዥም ጊዜ የአይሁድ የሰፈራ ንቅናቄ መሪ ዳንዬላ ዌይስ ፣ ወደ ጋዛ ለመሄድ ዝግጁ መሆናቸውን  ሲገልጹ&quot;የእስራኤል ሰዎች ለመታገል ዝግጁ ናቸው፣ ጋዛውያን ወደ ሌላ ቦታ ለቀው እንዲሄዱ ፕሬዚዳንት ትረምፕ ያቀረቡትን  ሀሳብ ለመፈጸም ዝግጁ ናቸው፣ በተመሳሳይ ጊዜ፣ የእስራኤል ሕዝብ የአይሁድ ሰፋሪዎችን በመላው ጋዛ ለማስፈር፣ የጽዮናዊነትን ግብ ለመፈጸም ዝግጁ እና ፈቃደኞች ናቸው።” ብለዋል።
በጋዛ የአይሁዶችን ሰፈራ መልሶ የመገንባት ተስፋ የማይመስል ቢመስልም፣ አብዛኞቹ እስራኤላውያን ሃማስ በወደፊቷ ጋዛ ምንም አይነት ሚና ሊኖረው እንደማይገባ ይስማማሉ፣  አንዳንዶች ይህን ለማረጋገጥ የተሻለው መንገድ አብዛኞቹ ፍልስጤማውያን ጋዛን ለቀው እንዲወጡ ማድረግ ነው ብለው ያምናሉ።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8007406.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8007406.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 12 Mar 2025 02:39:55 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/56e06c2a-a6ab-4d6f-0caa-08dd5c8d307c_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ውጥረቱ እያየለ በመጣባት ሰርቢያ ተቃዋሚዎች ወደ ዋናው የሰርቢያ ቴሌቭዥን ጣቢያ የሚወስደውን መንገድ ዘግተው ዋሉ</title>
            <description>በመቶዎች የተቆጠሩ ተማሪዎች ውጥረቱ እያየለ በመጣባት የባልካን ሀገር፣ ለፊታችን ቅዳሜና እሑድ ከታቀደው ግዙፍ ሰልፍ ቀናት አስቀድመው ቤልግሬድ የመንግሥቱን የሰርቢያ ቴሌቪዥን ጣቢያ ህንጻ ዘግተው ውለዋል። ለሳምንቱ መጨረሻ የተጠራው ግዙፍ ሰልፍ ለወራት የቀጠለው የጸረ መንግሥት ተቃውሞ መዳረሻ ተደርጎ ታይቷል።
ማዕከላዊ ቤልግሬድ የሚገኘውን የቴሌቭዥን ሕንጻ ትላንት ማምሻው ላይ የዘጉት ተማሪዎች፣ ዛሬ ማክሰኞም ብዙ መቶዎች ኾነው ተሰባስበው የመንገድ መዝጋቱ ጥረት ለተጨማሪ 22 ሰዓታት እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። በሁለተኛዋ የሃገሪቱ ትልቅ ከተማ ኖቪ ሳድ’ም ተመሳሳይ ተቃውሞ  ተደራጅቷል።
በኖቪ ሳድ የባቡር ጣቢያ የኮንክሪት ጣሪያ ተደርምሶ የ15 ሰዎች ህይወት ካጠፋ በኋላ፣ በየዕለቱ የሚካሄዱትን ሰልፎች የሚያደራጁት በተለያዩ የሰርቢያ ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ ተማሪዎች ናቸው። የተቃውሞ ሰልፎቹ የሕዝበኝነት  አቀንቃኙን የፕሬዝዳንት አሌክሳንዳር ቩቲች አገዛዝ እና ሥልጣን የሙጥኝ ብለው በመቀጠል የያዙትን አቋም አናውጠዋል።
ትላንት ሰኞ አመሻሹ ላይ በቴሌቪዥን ጣቢያው ዋና የዜና እወጃ ወቅት እንግዳ የነበሩት የሰርቢያው ፕሬዝደንት  በቃለ መጠይቁ ወቅት በተማሪዎች የሚመራውን የተቃውሞ ሰልፍ ሲዘልፉ ታይተዋል። &quot;የጸጥታ ኃይሎች በቅዳሜው ታላቅ ሰልፍ ላይ የኃይል ርምጃ ይወስዳሉ&quot; ሲልም አስጠንቅቀዋል። 
በመላ አገሪቱ የተካሄደውን መጠነ ሰፊ ሕዝባዊ አመጽ ተከትሎ ከሥልጣን አልወርድም ሲሉ የዛቱት ቩቲች &quot;ሃሳባችሁ እኔን መተካት ከሆነ የምትተኩኝ ገድላችሁኝ ነው&quot; ሲሉ ተደምጠዋል። ተማሪዎቹ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት ከቩቲች እና ከአስተዳደራቸው ጎን የቆመውን የመንግሥቱን ቴሌቭዥን ጣቢያ ፈጸመ ላሉት ድርጊት ተጠያቂ አድርገዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ቩቲች በዛሬው ዕለት ቤልግሬድ ከገቡት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ የበኩር ልጅ ዶናልድ ትረምፕ ጁኒየር ጋር ተገናኝተው ተነጋግረዋል። የጉብኝቱ ዓላማ ግን ለጊዜው አልታወቀም።ሩሲያው  ቩቲች  የፕሬዝደንት ትረምፕ ዋና ደጋፊ መሆናቸው ይታወቃል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/protesters-block-main-state-serbian-tv-building-as-tensions-soar-ahead-of-a-planned-large-rally-belgrade-serbia-/8007238.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/protesters-block-main-state-serbian-tv-building-as-tensions-soar-ahead-of-a-planned-large-rally-belgrade-serbia-/8007238.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 23:10:45 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/1653dfed-e154-4489-04f8-08dd5c8b1668_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የዛሬው የግሪንላንድ ምርጫ ነጻ አገር የመሆን ምኞቶች የሚፈተሹበት ነው ተባለ</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በማዕድን የበለጸገችውን ደሴት ለመቆጣጠር ፍላጎት እንዳላቸው ያንጸባረቁበት ውጥን ዓለም አቀፍ ትኩረት በሳበበት በዚህ ወቅት ፤ የግሪንላንድ ነዋሪዎች ዛሬ ማክሰኞ  ምርጫ እያካሄዱ ነው። 
ትረምፕ  ሥልጣን እንደተረከቡ ነበር ‘ለዩናይትድ ስቴትስ የደህንነት ጥቅም አስፈላጊ ናት’ ሲሉ ከፊል ራስ ገዟን የዴንማርክ ግዛት የዩናይትድ ስቴትስ አካል ለማድረግ ያላቸውን ፍላጎት ይፋ ያደረጉት።
57, 000 ሕዝብ ብቻ ያላት ደሴቲቱ ግዛት የከበባት በረዶ አለት መቅለጥ የተፈጥሮ ሃብቷን ይበልጥ ተደራሽ እያደረገ በመጣበት እና አዳዲስ የመርከቦች መመላለሻ መንገዶች እየተከፈቱ ባለበት፤ የአርክቲክ ውቅያኖስን እና አካባቢውን በበላይነት ለመቆጣጠር የተያዘው እሽቅድምድም ሆናለች። ሩስያ እና ቻይናም በአካባቢው  ወታደራዊ እንቅስቃሴያቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል።
ግሪንላንድ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ1979 የመጀመሪያው ፓርላማዋ ሲቋቋም የተወሰነ የራስ ገዝ አስተዳደር ስልጣን ተጎናጽፋለች። 
ይሁን እንጂ የውጭ ግንኙነቷን፣ እንዲሁም መከላከያ እና የገንዘብ ፖሊሲዋን የሚቆጣጠረው  የዴንማርክ መንግሥት ነው። ለኢኮኖሚዋ የሚመደበውም ወጭ በዓመት ከአንድ ቢሊዮን ዶላር ያነሰ ነው።
ከዴንማርክ ተገንጥላ ሙሉ ነፃ ሃገር ለመሆን በሕዝበ ውሳኔ የማወጅ መብት እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ2009 ብትጎናጸፍም፤ ያለ ዴንማርክ ኢኮኖሚያዊ ድጋፍ የዜጎቿ የኑሮ ደረጃ ሊወድቅ ይችላል በሚል ሥጋት ዕውን ሳታደርገው ቀርታለች። 
ይሁን እንጂ ትራምፕ ‘አሳካዋለሁ’ ሲሉ እያራመዱ ያሉት ፍላጎት፣  የአገሬው ተወላጆች ‘ኢኒዩት’ በተሰኘው ጥንታዊ ባህላቸው ያላቸው ኩራት እያደገ ከመምጣቱ ጋር ተዳምሮ፣ ነፃ አገር መሆን የሚለው ሃሳብ በዘንድሮው ምርጫ ልዩ ትኩረት አግኝቷል።
የምርጫ ጣቢያዎች ለ11 ሰዓታት ክፍት ሲሆኑ፤ ውጤቱም በነገው ዕለት ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል። ከወዲሁ የሚወጣ የምርጫ ውጤት ትንበያ አይኖርም።
ቀድሞ የዴንማርክ ቅኝ ግዛት እና እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር ከ1953 አንስቶ ደግሞ የግዛቷ አካል የሆነችው ግሪንላንድ፡ በቆዳ ስፋቷ ከዩናይትድ ስቴትሷ የቴክሳስ ክፍለ ግዛት በሦስት እጅ ትበልጣለች።
በጥር ወር የወጣ የሕዝብ አስተያየት ግምገማ እንደሚያሳየው  አብዛኛው የግሪንላንድ ሕዝብ ግዛቲቱ ነጻ ሀገር እንድትሆን የሚፈልግ ሲሆን ክፍፍል ያለው  &quot;መቼ  ይሁን እና የሕዝቡ የኑሮ ደረጃ እንዲያሽቆለቁል ካደረገስ?&quot; በሚሉት ጉዳዮች ነው።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8007019.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/greenland-election-tests-independence-ambitions-as-us-interest-looms/8007019.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 20:45:35 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>አሜሪካ</category><author> voadigital@voanews.com (ሮይተርስ Reuters)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/70bfa989-42d8-4bd9-a8ee-41006978a74e_cx0_cy7_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ዩክሬይን በዩናይትድ ስቴትስ ለተወጠነው የሰላም ንግግር ዕቅድ ልታቀርብ ነው</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ እና የዩክሬን ባለሥልጣናት ዛሬ ማክሰኞ ሳዑዲ አረቢያ ላይ በኪየቭ እና ሞስኮ መካከል የከፊል ተኩስ የማቆም ስምነት የታለመ እቅዳቸውን እንዲያቀርቡ የሚጠበቅበት ንግግር ጀምረዋል።  
የዩክሬን እቅድ የረጅም ርቀት የሚሳዬል ጥቃቶችን ማቆም እና ጥቁር ባህርን የሚሸፍን የሰላም ስምምነት ያካትታል። 
የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ በዛሬው ንግግር አልተሳተፉም። በምትካቸው የፕሬዝደንታዊው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አንድሬ የርማክ፣ የዩክሬኑ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንድሪ ሲቢሃ፣ የመከላከያ ሚንስትሩ ረስተም ኡሜሮቭ እና ወታደራዊ አዛዡ ፓቭሎ ፓሊሳ ተወክለዋል።  
የርማክ ከስብሰባው አስቀድሞ ለጋዜጠኞች በሰጡት አስተያየት “ሰላምን እንዲመጣ ዩክሬን ሁሉንም ነገር ለማድረግ ዝግጁ ነች&quot; ብለዋል።.
ሀገራቸው የደኅንነት ዋስትና እንዲሰጣት ትሻ እንደሆን የተጠየቁት የርማክ &quot;አዎን! ዩክሬን ሩስያ ይህን መሰል የኃይል ጥቃቷን ፈጽሞ እንደማትደግም ማረጋገጥ ትሻለች&quot; ብለዋል።
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ2022 መጀመሪያ ላይ ሩስያ በዩክሬን ላይ ለከፈተችው መጠነ ሰፊ ወረራ አፋጣኝ ማብቂያ ለማበጀት በያዙት ጥረት የዩናይትድ ስቴትስን ልዑካን ቡድን የመሩት የዩናይትድ ስቴትሱ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ እና የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪው ማይክ ዋልትዝ ናቸው።
ሩቢዮ ትላንት ሰኞ ሲናገሩ ዩናይትድ ስቴትስ ለጊዜው የተቋረጠው ለዩክሬን ይሰጥ የነበረው ርዳታ ጉዳይም እልባት ያገኛል የሚል ተስፋ እንዳላት አመልክተዋል። 
ሩቢዮ አክለውም ከዩክሬይን ጋራ በሚደረገው ንግግር ላበረከቱት አስተዋፆ ብሪታንያን እና ፈረንሳይን አወድሰዋል።
</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/rubio-ukraine/8006758.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/rubio-ukraine/8006758.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 11 Mar 2025 18:40:25 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><category>መካከለኛው ምሥራቅ</category><author> voadigital@voanews.com (ቪኦኤ ዜና)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/d78f7d16-5b43-44a4-0b3f-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በጀርመን አየር ማረፊያዎች የተካሄደው የአንድ ቀን የሥራ ማቆም አድማ በረራዎችን አስተጓጎለ </title>
            <description>የፍራንክፈርት እና የሙኒኩን ጨምሮ በ13 የጀርመን አውሮፕላን ጣቢያዎች እና ሌሎች የሀገሪቱ ዋና መዳረሻዎች፤ ሠራተኞች በዛሬው ዕለት ያደረጉት የአንድ ቀን የሥራ ማቆም አድማ ቀደም ሲል ጊዜ ተይዞላቸው የነበሩ አብዛኛዎቹ በረራዎች እንዲሰረዙ ምክኒያት ሆኗል።


ትላንት እሑድ እኩለ ለሊት ላይ የጀመረው እና ለ24 ሰዓታት እንዲቀጥል የታቀደው የሥራ ማቆም አድማ፤ በአውሮፕላን ጣቢያዎቹ የሚያገለግሉ ከአየር ማረፊያ ጋራ የተዛመዱ የምድር አገልግሎቶች ሥራ የሚሠሩ እና የደኅንነት ሠራተኞችን ያካተተ ነው።


በፍራንክፈርት አውሮፕላን ጣቢያ ለዕለቱ ታቅደው ከነበሩት ቁጥራቸው 1 ሺሕ 54 ከሚደርሱት በረራዎች 1 ሽሕ 116ቱ መሰረዛቸውን የጀርመን ዜና አገልግሎት የሀገሪቱን የአየር ትራፊክ አስተዳደር ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።


ከበርሊን አውሮፕላን ጣቢያ የሚነሱ እና የሚመለሱ መደበኛ በረራዎች በሙሉ የተሰረዙ ሲኾን፤ ከሃምቡርግ አውሮፕላን ጣቢያ የተነሳ ምንም ዓይነት በረራ እንዳነበርም ተዘግቧል። የኮሎኝ - ቦን አውሮፕላን ጣቢያም ምንም ዐይነት የመንገደኞች አገልግሎት ያለመኖሩን፤ የሙኒክ አውሮፕላን ጣቢያ በበኩሉ ‘እጅግ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው የበረራ መርሃ ግብሮች ብቻ ተፈጻሚ ይሆናሉ’ ሲል ለተጓዦች አስታውቆ ነበር።


በጀርመኑ የአውሮፕላን ጣቢያዎች ማኅበር ግምት መሰረት፤ በጠቅላላው ከ3ሺሕ 500 በላይ በረራዎች ሲሰረዙ፤ ቁጥራቸው 560 ሺሕ የሚጠጉ መንገደኞች የጉዞ መስተጓጎል ገጥሟቸዋል። በሌላ ተዛማች ዜና፡ ስለ ሰኞው የሥራ ማቆም አድማ ዕቅድ ባለፈው ዐርብ አስቀድሞ ያስታወቀው የሠራተኞች ማኅበር፣ ‘ርምጃው ውጤታማ እንዲሆን’ ሲል ትላንት እሐድ ሌላ አጭር ማሳሰቢያ ከሰጠ በኋላ፤ በሃምቡርግ አውሮፕላን ጣቢያ የሥራ ማቆም አድማ ማድረጉም ተመልክቷል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/one-day-strike-at-13-german-airports-including-the-main-hubs-brings-most-flights-to-a-halt/8005589.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/one-day-strike-at-13-german-airports-including-the-main-hubs-brings-most-flights-to-a-halt/8005589.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 21:06:45 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/81e30477-6c01-4d9b-300a-08dd5c897904_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>አባ ፍራንሲስ የቫቲካንን የጾም ጉባኤ በርቀት እየተከታተሉ ነው</title>
            <description>የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት አባ ፍራንሲስ በፋሲካ ጾም ወቅት የሚደረገውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ጉባኤ ሮም ከሚገኘው ሆስፒታል በርቀት በመከታተል ላይ መኾናቸው ታውቋል።


ከገጠማቸው የሳምባ ምች በማገገም ላይ ያሉት አባ ፍራንሲስ ከሆስፒታል አልጋቸው ላይ ሆነው ጉባኤውን በቪዲዮ በመከታተል ላይ ሲኾኑ፣ የጉባኤው ተሳታፊዎች ግን እርሳቸውን ማየትም ሆነ መስማት  እንደማይችሉ የአሶስዬትድ ፕረስ ዘገባ አመልክቷል።


የአንድ ሳምንቱ ጉባኤ፣ እስከ ፋሲካ የሚቆየው የቤተ ክርስቲያኗ ዐብይ ጾም በሚጀምርበት ወቅት በየዓመቱ የሚካሄድ ሲሆን፣ አባ ፍራንሲስም በርቀት ከሌሎቹ የቤተክርስቲያኗ ጳጳሳት ጋራ በጉባኤው እንደሚሳተፉ ቫቲካን አስታውቃለች፡፡


ለ12 ዓመታት ሊቃነ ጳጳስነት የቆዩት አባ ፍራንሲስ በሕመም መያዛቸው ቀጣዩ የጵጵስና ዘመናቸው ምን ሊሆን እንደሚችል ጥያቄ ጭሯል።


የሳምባ ምቹ ተባብሶ ሁለቱም ሳምባዎችና የመተንፈሻ ቧንቧቸውም ለመቆጣት እንደበቃ ታውቋል። ባለፈው አንድ ሳምንት ግን በተረጋጋ ሁኔታ እንደሚገኙ እንዲሁም ትኩሳትና የኦክሲጅን መጠን መወላወል እንዳልገጠማቸውም ታውቋል። እንዲህ ዐይነቱ መሻሻል ጳጳሱ የሚሰጣቸው ሕክምና እየሠራ ለመሆኑ አመልካች እንደሆነ ሐኪሞቻቸው አስታውቀዋል።


የአባ ፍራንሲስ ባእለ ሲመት ሐሙስ የሚከበር ሲሆን፣ ይህም ለመጀመሪያ ጊዜ የማይታደሙበት እንደሆነ ታውቋል።


በትላንትናው ዕለት እሑድ፣ አባ ፍራንሲስ ከከፍተኛ የቤተ ክርስቲያኒቱ ኅላፊዎችና ጳጳሳት ጋራ በሆስፒታል ሳሉ ለሦስተኛ ጊዜ እንደተገናኙ የአሶስዬትድ ፕረስ ዘገባ አመልክቷል።


አባ ፍራንሲስ ከእርሳቸው በፊት የነበሩት አባ ቤኔዲክት በፈቃዳቸው ቦታውን በመልቀቃቸው ቢያደንቁም፣ የሊቃነ ጳጳሳት ቦታው የሕይወት ዘመን መሆኑንና ለመልቀቅም ሐሳብ እደሌላቸው በቅርቡ አስታውቀዋል።

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/8005521.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/8005521.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 20:45:12 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5b3060ae-b036-4ea7-0a17-08dd5c8d307c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሰሜን ባህር ላይ ሁለት መርከቦች ተጋጩ</title>
            <description>አንድ ነዳጅ አመላላሽና አንድ የሸቀጥ አመላላሽ መርከብ በሰሜን ባህር ላይ ተጋጭተው 32 ሰዎች መጎዳታቸውንና ወደ ባህር ዳርቻ እንዲወጡ መደረጉን አንድ የእንግሊዝ ወደብ ኅላፊ አስታውቀዋል።


የተጎጂዎቹ ሁኔታን ወዲያውኑ ማወቅ እንዳልተቻለ ያመለከተው የአሶስየትድ ፕረስ ዘገባ፣ የእንግሊዝ የባህር ድንበር ኅይሎች አንድ አውሮፕላንን ጨምሮ በርካታ ነፍስ አድን ጀልባዎችንና አንድ ሄሊኮፕተር ማሰማራታቸውን አስታውቋል።


ከተጋጩት መርከቦች አንደኛው የአሜሪካንን ባንዲራ የሚያውለበልብ ሲኾን ሌላኛው ደግሞ የፖርቹጋልን ባንዲራ የሚያውለበልብ መሆኑም ታውቋል። የአሜሪካኑን ባንዲራ የሚያውለበልበውና ኬሚካልና ነዳጅ የሚያመላለሰው መርከብ ከግሪክ የተነሳ ሲሆን፣ የፖርቹጋልን ባንዲራ የሚያብለበልበው መርከብ ደግሞ ከስኮትላንድ ተነስቶ ወደ ኔዘርላንድ በማቅናት ላይ ነበር ተብሏል።


ግጭቱ እንደተከሰተ እሳት እንደተፈጠረና በርካታ ሰዎች መርከቦቹን ለቀው እንደወጡ ተመለክቷል።


በአቅራቢያው ከሚገኝ መርከብ የተቀረጸውና በቢቢሲ የተሰራጨው ቪዲዮ ከሁለቱም መርከቦች ጥቁር ጭስ ሲወጣ አሳይቷል።


የአደጋው ሥፍራ ከለንደን በስተ ሰሜን 250 ኪ.ሜ እንደሚርቅም ታውቋል

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/port-chief-says-32-casualties-brought-ashore-after-ships-collide-and-catch-fire-in-north-sea-/8005440.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/port-chief-says-32-casualties-brought-ashore-after-ships-collide-and-catch-fire-in-north-sea-/8005440.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 10 Mar 2025 19:38:41 +0300</pubDate>
            <category>ዓለምአቀፍ</category><author> voadigital@voanews.com (ኤፒ AP)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0AF8478F-7B44-40BA-8802-5E7F9059AAEB_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        </channel></rss>