<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com</link>
        <description>የአሜሪካ ድምፅ  (ቪኦኤ) ከአርባ በላይ በሆኑ ቋንቋዎች ከዩናይትድ ስቴትስ ለመላው ዓለም የሚሠራጭ ዓለምአቀፍ ብዝኃ ሚድያ የሥርጭት አገልግሎት ነው</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2020 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Tue, 29 Dec 2020 22:54:27 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/ayto_qeqii_o" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>የኅዳሴ ጉዳይ ዓለምአቀፍ ውሎ</title>
            <description>የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ጉዳይ ትናንት ከሰዓት በኋላ ተነጋግሯል።


ለስብሰባው ጠለቅ ያለ ማብራሪያ የሰጡት የመንግሥታቱ ድርጅት የፖለቲካና የሰላም ግንባታ ጉዳዮች ረዳት ዋና ፀሐፊ ሮዝሜሪ ዲካርሎ የኅዳሴ ግድብ ሥራ ከተጀመረ አንስቶ ያለውን ታሪክና ኢትዮጵያ፣ ግብፅና ሱዳን እንዲሁም መሪዎቻቸው የተጓዙባቸውን መንገዶች ጠቋቁመዋል።


ሰሞኑንም የአፍሪካ ኅብረት የወቅቱ ሊቀመንበር በሆኑት የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፖሳ ሰብሳቢነት በተጠራ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ፣ የግብፅ ፕሬዚዳንት አብደልፋታህ ኤል ሲሲና የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱላ ሃምዶክ በተገኙበት ስብሰባ ላይ መሪዎቹ ቀሪ ጉዳዮቻቸውን ለመፍታት በአፍሪካ ኅብረት ወደሚመራ ሂደት ለመግባት መስማማታቸውን ረዳይ ዋና ፀሐፊዋ ዲካርሎ ለፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ አሳውቀዋል።


በሦስቱ ሃገሮች መካከል በሚካሄዱት ድርድሮች የቀሩት በተፈጥሯቸው የቴክኒክና የሕግ ጉዳዮች መሆናቸውን ዲካርሎ ጠቁመው እነዚህም የሚደርሱበት ስምምነት አሳሪነት፣ የውዝግብ አፈታት ሥርዓትና በድርቅ ጊዜ የውኃ አያያዝን እንደሚያካትቱ ተናግረዋል።


ረዳት ዋና ፀሐፊዋ አክለውም ወገኖቹ ስምምነት ላይ ለመድረስ ቁርጠኛ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበው የአፍሪካ ኅብረት ሂደቱን እስከፍፃሜው ለመምራት እያደረገ ያለውን ጥረትም አድንቀዋል።


ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅም ለጋራ ተጠቃሚነት የሚያደርሳቸውን ጥረት ጠብቀውና አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ያላቸውን መተማመን አጉልተው ተናግረዋል።


ይህ በእንዲህ እንዳለ በታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ጉዳይ ሰሞኑን መግለጫ ያወጣው የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት የጥቁር እንደራሴዎች ጉባዔ በግድቡ አሞላልና በሌሎችም የቴክኒክ ጉዳዮች የተነሣው ውዝግብ በሰላምና በመግባባት እንዲፈታ ለማስቻል ማንኛውንም ድጋፍ እንደሚሰጥ አስታውቆ ጉዳዩን አህጉራዊው የአፍሪካ ኅብረት እንዲይዘው እንደሚያበረታታም ገልፆ ነበር።




 


በጉባዔው መግለጫ ላይ ከቪኦኤ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት ሊቀመንበሯ የካሊፎርኒያ እንደራሴ ኬረን ባስ የደብዳቤአቸው ዋና ሃሳብና የእርሳቸውም አመለካከት ሦስቱ ሃገሮች ለችግሮቻቸው መፍትኄውን እራሳቸው እንዲፈልጉ መሆኑን ተናግረዋል። ዩናይትድ ስቴትስ ከሦስቱም ሃገሮች ከእያንዳንዳቸው ጋር ያሏት ግንኙነቶች የተለያዩ በመሆናቸው በጉዳዩ ውስጥ መግባቷ አሳስቧቸው እንደነበርም ገልፀዋል።


በሌላ በኩል ደግሞ በዳያስፖራ ያሉ አሥራ አምስት የኢትዮጵያዊያን ሲቪክ ማኅበራት በታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ጉዳይ ሰሞኑን መግለጫ አውጥተዋል።


የኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያ ባለሙያዎች፣ ምሁራንና የመብቶች ተሟጋቾች በዚሁ መግለጫቸው ለኢትዮጵያ መንግሥት ጥረቶች ያላቸውን ድጋፍና አድናቆት ከመግለፅም አልፈው ሌሎችም ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያ ማንኛቸውንም ልዩነቶቻቸውን አስወግደው ከመንግሥቱ ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አሰምተዋል። ለዓለምአቀፉ ማኅበረሰብም ባለስድስት ነጥብ ጥያቄ አቅርበዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ። 






 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/gerd-unsc-mass-minga-6-30-2020/5484248.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/gerd-unsc-mass-minga-6-30-2020/5484248.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 01 Jul 2020 04:14:30 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>ታላቁ የኅዳሴ ግድብ Great Reninssance</category><author> voadigital@voanews.com (ሰሎሞን አባተ, ሳሌም ሰለሞን)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/gerd-unsc-mass-minga-6-30-2020/5484248.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5DE18DA0-1ED8-4B34-9FCB-7AA979C1872A_cx0_cy2_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የአፍሪካ ጦሮችና ኮቪድ-19</title>
            <description>አንዳንድ የአፍሪካ ሃገሮች የኮሮናቫይረስን መተላለፍና መስፋፋት ለመቆጣጠር በሚል ያወጧቸውን ገደቦችና ድንጋጌዎች ለማስፈፀም ወታደሮቻቸውን ማሰማራታቸው በብዙዎች ዘንድ ሥጋትን አሳድሯል።


ሥጋቱ በተለይ ግጭቶች በተለመዱባቸው አካባቢዎች ይበልጥ ማየሉ እየተነገረ ነው። 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/covid-unhcr-4-30-2020/5399897.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/covid-unhcr-4-30-2020/5399897.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 01 May 2020 01:25:32 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ሳሌም ሰለሞን, ሰሎሞን አባተ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/covid-unhcr-4-30-2020/5399897.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/5bd79ea4-675a-4b38-b2b9-e11fab8d5c58_tv_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>