<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com</link>
        <description>የአሜሪካ ድምፅ  (ቪኦኤ) ከአርባ በላይ በሆኑ ቋንቋዎች ከዩናይትድ ስቴትስ ለመላው ዓለም የሚሠራጭ ዓለምአቀፍ ብዝኃ ሚድያ የሥርጭት አገልግሎት ነው</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2020 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Tue, 29 Dec 2020 01:39:56 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/arupmteuimmr" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>&quot;ህወሓት በማያንሰራራበት ሁኔታ ተንኮታኩቷል&quot; - ጀነራል ብርሃኑ ጁሉ</title>
            <description>ህወሓት በማያንሰራራበት ሁኔታ ተንኮታኩቷል ሲሉ የኢትዮጵያ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀነራል ብርሃኑ ጁላ ተናግረዋል።


ጀነራሉ ይሄንን የተናገሩት በትግራይ ክልል የተካሄደው ጦርነት አሁንም እንዳልቆመ የሚገልፁ አንዳንድ አስተያየቶችን ባጣጣሉበት ምላሽ ነው።


በሌላም በኩል ንፁሃን ዜጎች የሚገደሉበት የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፀጥታ ችግር ህወሓት ቀርጿቸው ከነበሩ ፕሮጀክቶች አንዱ ነው ሲሉ ኤታማዦር ሹሙ ጠቁመዋል።


በአካባቢው ያለውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት ሁለገብ ስራ እየተሰራ መሆኑንም ለአሜሪካ ድምፅ አብራርተዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/army-chief-metekel-12-28-2020/5715979.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/army-chief-metekel-12-28-2020/5715979.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 28 Dec 2020 18:55:20 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/army-chief-metekel-12-28-2020/5715979.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/920ACB0C-6A03-477D-9AA2-A7C6A963F208_cx0_cy6_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሁለት የደርግ ባለሥልጣናት ከ30 ዓመታት በኋላ ነፃ ወጡ</title>
            <description>በእነ ኮሎኔል መንግሥቱ ሃይለማርያም መዝገብ የተፈረደባቸው ሁለት ከፍተኛ የደርግ ባለሥልጣናት በአመክሮ እንዲለቀቁ የተወሰነው የሃገሪቱን ሕጎችና በዳኛች የተሰጠውን ትርጓሜ መሠረት በማድረግ መሆኑን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋ።


የውሳኔው መነሻ ደግሞ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው ከነበረው ከነዚሁ ባለሥልጣናት የቀረበው አቤቱታ መሆኑን የፌደራል ምክትል ዐቃቤ ሕግ ፈቃዱ ፀጋ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።


በተመሳሳይ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ ኮሎኔል መንግሥቱ ሃይለማሪያም ግን እስካሁን ያቀረቡት አቤቱታ እንደሌለ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ጠቁመዋል።


በአመክሮ እንዲለቀቁ የተወሰነላቸው የቀድሞ የደርግ ባለሥልጣናት ለ30 ዓመታት በአዲስ አበባው የጣሊያን ኤምባሲ የቆዩት ሻለቃ ብርሃኑ ባይህ እና ሻለቃ አዲስ ተድላ ናቸው።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/dergue-officials-12-25-2020/5713671.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/dergue-officials-12-25-2020/5713671.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 25 Dec 2020 23:44:20 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/dergue-officials-12-25-2020/5713671.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/445FC485-C3FF-44A2-9BD3-5F43A5AF6591_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>&quot;የኢትዮጵያ መንግሥት ትግራይ ክልል ውስጥ ያካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ ህጋዊ ነው” - ሙሳ ፋኪ ማሃማት</title>
            <description>የኢትዮጵያ መንግሥት ትግራይ ክልል ውስጥ ያካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ “ህጋዊ ነው” ሲሉየአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ተናግረዋል።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/igad-summit-/5708100.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/igad-summit-/5708100.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 22 Dec 2020 01:41:50 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/igad-summit-/5708100.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/CBB70026-13D9-49FE-B21F-CD23A0AF1851_cx0_cy11_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኢትዮጵያ እና በሱዳን የፀጥታ ሃይሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት</title>
            <description>ማክሰኛ ዕለት በኢትዮጵያ እና በሱዳን የፀጥታ ሃይሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት በሁለቱ አገራትከፍተኛ ባለስልጣናት ውይይት እንደሚደረግበት ተገልጿል::</description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2020/12/18/cea866f6-6d51-4304-b6ce-80cd9f3ff6ee_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5704651.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 18 Dec 2020 16:29:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>አጭር ድምጽ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/795F5151-7B87-4D67-9F5F-0B127E87B7E0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኢትዮጵያ እና በሱዳን የፀጥታ ሃይሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት</title>
            <description>ማክሰኛ ዕለት በኢትዮጵያ እና በሱዳን የፀጥታ ሃይሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት በሁለቱ አገራትከፍተኛ ባለስልጣናት ውይይት እንደሚደረግበት ተገልጿል::</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5704654.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5704654.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 18 Dec 2020 16:09:54 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5704654.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/795F5151-7B87-4D67-9F5F-0B127E87B7E0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያ መንግሥት የሰብዓዊ ድጋፍ ወደ ትግራይ እየላከ ነው</title>
            <description>የምግብ አቅርቦትና መድኃኒት የጫኑ በርካታ ተሽከርካሪዎች መቀሌ አዲግራት እና ሽሬ መግባታቸውን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል።


በተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች እየተካሄደ ያለ ውጊያ ለሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት እንቅፋት ሆኗል በሚል የሚሰጡ አስተያየቶችንም ሐሰት በማለት አጣጥሏል።


በሽሽት ላይ ከሚገኙ የሚሊሻ አባላት ጋር አልፎ አልፎ የሚደረግ የተኩስ ልውውጥና ወንጀለኞችን ለመያዝ የሚደረግ ጥረት እንደ ውጊያ አይቆጠርም ነው ይላል መግለጫው።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-assistant-for-tigray-12-11-2020/5696347.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-assistant-for-tigray-12-11-2020/5696347.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 11 Dec 2020 23:53:11 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-assistant-for-tigray-12-11-2020/5696347.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/291BA2B3-4666-4011-9CE5-27E0002C757C_cx0_cy22_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የሰብአዊ ድጋፍ ወደ ትግራይ ክልል መላኩን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ</title>
            <description>ለ250 ሺህ ዜጎች የሚሆን ሰብአዊ ድጋፍ ወደ ትግራይ ክልል መላኩን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል።


ሰብአዊ ድጋፉን የሚያስተባብሩ ቡድኖች መሰማራታቸውንም አመልክቷል። የሰብአዊ ድጋፍ እንቅስቃሴው የሚመራው በኢትዮጵያ መንግሥት መሆኑን የገለፁት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ፍሰት ቃል አቀባይ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የተባበሩት መንግሥታትም ሆነ ሌሎች የሰብአዊ ድጋፍ ተቋማት የመንግሥትን መመሪያዎች እና የአገሪቱን ሕግ አክብረው እንዲሳተፉ አሳስበዋል።


ትግራይ ውስጥ ወደሚገኘው ሽመልባ የስደተኞች መጠለያ እያተጓዙ እንደነበር የገለጹ የተባበሩት መንግሥታት ሠራተኞች ተኩስ ያጋጠማቸውም ሁለት ኬላዎችን ከጣሱ በኋላ ሦስተኛውንም ሊጥሱ ሲሉ መሆኑን አምባሳደር ሬድዋን ተናግረዋል።


በፖሊስ ቁጥጥር ሥር በሚገኙት የህወሃት ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የቀድሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም እንደዚሁም በቀድሞው የትግራይ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አምባሳደር አዲስ አለም ባሌማ ላይ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑንም ቃል አቀባዩ አመልክተዋል::


“በሽሽት ላይ ካሉት የህወሓት መሪዎች አብዛኛዎቹም በጥቂት ቀናት ወይም ሳምንታት ውስጥ ተይዘው ለፍርድ ይቀርባሉ” ብለዋል አምባሳደር ሬድዋን።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/spokes-person-for-the-state-of-emergency-fact-sheet-in-ethiopia-press-conference-12-8-2020/5691681.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/spokes-person-for-the-state-of-emergency-fact-sheet-in-ethiopia-press-conference-12-8-2020/5691681.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 08 Dec 2020 19:03:15 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/spokes-person-for-the-state-of-emergency-fact-sheet-in-ethiopia-press-conference-12-8-2020/5691681.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/B43F9B44-1F1F-4AEC-A211-851F1F19A589_cx0_cy3_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የብልፅግና ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ</title>
            <description>ትግራይ ክልል ውስጥ ሲካሄድ የቆየው ወታደራዊ ውጊያ መጠናቀቁንና መቆሙን የገዥው ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ዋና ኃላፊ ገልፀዋል።


የፓርቲው የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የዋና ፅ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ብናልፍ አንዱአለም ዛሬ ከአሜሪካ ድምፅ ጋር በተለይ ባደረጉት ቃለ ምልልስ ወታደራዊ ዘመቻው ያበቃ ቢሆንም “በተወሰኑ ቀናት የሚጠናቀቅና በፖሊስ ኃይል እየተካሄደ ነው” ያሉት “ህግ የማስከበር ዘመቻ የሚጠናቀቀው ግን የህወሓት መሪዎች ለፍርድ ሲቀርቡ ነው” ብለዋል።


እስካሁን ‘ተሸንፈናል’ ያላለው ህወሓት ይልቁንም ‘ሥልታዊ ማፈግፈግ’ ማድረጉን እየገለፀ የሚገኝ ሲሆን አቶ ብናልፍ ግን እንደዚህ ዓይነት አስተያየቶችንና የተራዘመ የሽምቅ ውጊያ ሊኖር ይችላል የሚሉ ግምቶችን አጣጥለዋል።


ህወሓት በሽብርተኝነት እንዲፈረጅ እየቀረቡ ያሉ ጥሪዎች መኖራቸውን የጠቀሱት የፅ/ቤቱ ኃላፊ ገዥው የብልፅግና ፓርቲ ገና ቁርጥ ያለ ውሳኔ ላይ አለመድረሱንም አመልክተዋል።


በሌላም በኩል ወደ 30 ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ በምዕራብ ትግራይ ሲነሳ የቆየው የማንነትና የአስተዳደር ወሰን ጥያቄ አግባብነት ባለው መንገድ እንዲመለስ የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መወሰኑንም ኃላፊው አስታውቀዋል።


የፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ኅዳር 25 እና 26 ለሁለት ቀናት ያካሄደውን ስብሰባ ትናንት አጠናቅቋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/prosperity-party-12-7-2020/5690531.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/prosperity-party-12-7-2020/5690531.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 07 Dec 2020 22:28:28 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/prosperity-party-12-7-2020/5690531.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/CA53A7CB-A676-4EC9-A14E-B647B4A5E9F0_cx0_cy3_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ኢትዮ-ቴሌኮም በትግራይ አንዳንድ አካባቢዎች አገልግሎት ጀመረ</title>
            <description>በትግራይ ክልል የተወሰኑ አካባቢዎች የቴሌኮም አገልግሎት እንደገና መጀመሩን ኢትዮ-ቴሌኮም አስታውቋል።


ያጋጠሙ ጉዳቶችን በመጠገን እና መልሶ በማቋቋም እንዲሁም አማራጭ የሃይል አቅርቦቶችን በመጠቀም ላይ መሆናቸውን የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ለአሜሪካ ድምፅ አብራርተዋል።


አገልግሎቱ በዳንሻ፣ በተርካን፣ በሁመራ፣ በሽራሮ፣ በማይፀብሪ እና በማይካድራ በከፊል በአላማጣ ደግሞ ሙሉ በሙሉ መጀመሩንም ጠቁመዋል።


የመቀሌው የቴሌኮም መሰረተ ልማት መጎዳት አለመጎዳቱን የሚያጠና ቡድን መላኩን እና እስከ ነገ ድረስ ውጤቱ እንደሚታወቅም ተናግረዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/tigray-communication-12-2-2020/5684705.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/tigray-communication-12-2-2020/5684705.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 02 Dec 2020 21:18:25 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/tigray-communication-12-2-2020/5684705.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/D1062FA9-501A-4F25-A2A7-5B7A8774630F_cx7_cy68_cw83_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ቆይታ ከኢትዮጵያ አየር ኃይል አዛዥ ጋር</title>
            <description>ህወሓት ትናንት ሌሊት ወደ ባህርዳር የተኮሳቸው ሮኬቶች ምንም ዓይነት ጉዳት አለማድረሳቸውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሜጄር ጄነራል ይልማ መርዳሳ አስታወቁ። ሮኬቶቹ ከየት እንደተተኮሱ እናውቃለን ያሉት ዋና አዛዡ ያረፉትም በገበሬ ማሳ ላይ ነው ሲሉ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።


እንደ ሜጄር ጀነራሉ ገለፃ በህወሓት እጅ የነበሩ ሮኬቶች አየር ኃይሉ ከዚህ ቀደም ባካሄዳቸው ድብደባዎች ወድመዋል። ህወሓት አሁን የተኮሳቸውም በኮንትሮባንድ እና በተለያየ መንገድ ያስገባቸው እና በየጉድጓዱ የደበቃቸው ናቸው ብለዋል።


የኢትዮጵያ አየር ኃይል እየወሰዳቸው ባሉ እርምጃዎች ሲቪሎች ተጎድተው እንደማያውቁ የገለፁት ዋና አዛዡ ህወሓት በዚህ ረገድ የሰነዘራቸውን ውንጀላዎችም አጣጥለዋል።




 


በሌላም በኩል ወደ ባህርዳር የተተኮሱት ሮኬቶች ጉዳት አለማድረሳቸውን እና ያረፉትም ማሳ ላይ መሆኑን የዓይን እማኞችም ለአሜሪካ ድምፅ አረጋግጠዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/Ethiopia-conflict-11-20-2020/5670728.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/Ethiopia-conflict-11-20-2020/5670728.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 20 Nov 2020 23:19:08 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው, አስቴር ምስጋናው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/Ethiopia-conflict-11-20-2020/5670728.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/3040177D-E87D-4BEC-B046-35720F85EE12_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የኢትዮጵያ መንግሥት በህወሓትና በዶ/ር ቴድሮስ ጉዳይ </title>
            <description>ህወሓት አንደገና የሚዋቀረው የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር አካል መሆን እንደማይፈቀድለት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገልጸዋል።


በአሁኑ የትግራይ አስተዳዳርር ውስጥ ያሉት አብዛኞቹ በህገ ወጥ ምርጫ የተመረጡ ናቸው ብለዋል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ዶ/ር ሙሉ ነጋ።


በተያያዘ ዜና ለህወሓት ድጋፍ እያሰባሰቡና በጫና ወደ ድርድር እንዲገባ እየሰሩነው ባላቸው የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድኃኖም ላይ ስለሚወስደው አቋም ገና ግልፅ ውሳኔ ላይ አለመድረሱን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል።


ሆኖም መንግሥት የቴድሮስን እንቅስቃሴዎች ያውቃል ብለዋል የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ የመረጃ ፍሰት ቃል አቀባይ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-conflict-11-19-2020/5669228.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-conflict-11-19-2020/5669228.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 19 Nov 2020 22:48:52 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-conflict-11-19-2020/5669228.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/3E4D17A5-8198-41DD-894C-A16D5E2AEE2A_cx0_cy12_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የትግራይ ክልል አስተዳደር እንደገና ይዋቀራል</title>
            <description>የመጀመሪያው ኃላፊነት የክልሉን አስተዳደር መልሶ ማዋቀር ነው ሲሉ በትግራይ የተቋቋመው ጊዚያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተናግረዋል።


በፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ የተቋቋመው የጊዚያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሙሉ ነጋ ለአሜሪካ ድምፅ እንደገለፁት የክልሉ ምክር ቤትና ካቢኔ እንደገና ይዋቀራሉ።


መንግሥት እያካሄደ ካለው ዘመቻ በኋላ ክልሉ የሚመራበት ቻርተር መዘጋጀቱንም አብራርተዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/the-chief-executive-of-tigray-interim-administration-dr-mulu-nega-with-voa-11-18-2020/5667375.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/the-chief-executive-of-tigray-interim-administration-dr-mulu-nega-with-voa-11-18-2020/5667375.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 18 Nov 2020 18:12:39 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/the-chief-executive-of-tigray-interim-administration-dr-mulu-nega-with-voa-11-18-2020/5667375.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/E8028A3A-8CFD-40CF-8D83-3345CE777E8C_cx0_cy5_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የአምነስቲ ሪፖርት በማይካድራ ጭፍጨፋ</title>
            <description>ማይካድራ ውስጥ በመቶዎች ሲቪሎች ላይ ጭፍጨፋ ለመካሄዱ ማስረጃ  እንዳለው አምነስቲ አስታወቀ።ድርጊቱ በትግራይ የፀጥታ ኃይሎች ስለመፈፀሙ መረጃዎች ያመለክታሉ ሲል ያነጋገራቸውን እማኞች ቃል ጠቅሶ በሪፖርቱ ላይ አስፍሯል።የትግራይ ክልል  በትግራይ ሕዝብ ላይ የተጀመረው ከባድ የዘር ማጥፋት ወረራን ለመቀጠል ሆን ተብሎ የተሰራጨ የሐሰት ዜና ነው ብሎታል። በአካባቢው የነበረ የህወሃት ልዩ ሃይልና ሚሊሻ የፈጸመው ጅምላ ጭፍጨፋ ነው ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል:</description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2020/11/13/18f887f7-4cce-412c-9b9b-cf78a36be940_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5659906.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 13 Nov 2020 21:51:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>ሳምንታዊ  ዝግጅቶች</category><category>ፖለቲካ</category><author> voadigital@voanews.com (ጽዮን ግርማ, እስክንድር ፍሬው, ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9ad8e988-6e5b-40bc-ada7-78894db0b3f9_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የአምነስቲ ሪፖርት በማይካድራ ጭፍጨፋ</title>
            <description>ማይካድራ ውስጥ በመቶዎች ሲቪሎች ላይ ጭፍጨፋ ለመካሄዱ ማስረጃ  እንዳለው አምነስቲ አስታወቀ።ድርጊቱ በትግራይ የፀጥታ ኃይሎች ስለመፈፀሙ መረጃዎች ያመለክታሉ ሲል ያነጋገራቸውን እማኞች ቃል ጠቅሶ በሪፖርቱ ላይ አስፍሯል።የትግራይ ክልል  በትግራይ ሕዝብ ላይ የተጀመረው ከባድ የዘር ማጥፋት ወረራን ለመቀጠል ሆን ተብሎ የተሰራጨ የሐሰት ዜና ነው ብሎታል። በአካባቢው የነበረ የህወሃት ልዩ ሃይልና ሚሊሻ የፈጸመው ጅምላ ጭፍጨፋ ነው ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል:</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/5659913.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/5659913.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 13 Nov 2020 21:39:28 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><category>የዕለቱ አብይ ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ጽዮን ግርማ, እስክንድር ፍሬው, ሙሉጌታ አጽብሃ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/5659913.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9ad8e988-6e5b-40bc-ada7-78894db0b3f9_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>&quot;ወታደራዊ እርምጃው ሦስት ግቦችን አሳክቶ ይጠናቀቃል&quot; - ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ</title>
            <description>በትግራይ ክልል የተጀመረው ሕግ የማስከበር እርምጃ ባቀድነው መሠረት እየሄደ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታውቀዋል።


ህገወጡን ቡድን ትጥቅ ማስፈታት በክልሉ ህጋዊ አስተዳደር መመለስና በሽሽት ላይ ያሉ ተጠርጣሪ ወንጀለኞችን ለፍርድ ማቅረብ ደግሞ የወታደራዊ የእርምጃው ዓላማዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህወሓት በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት መፈፀሙን ያስታወቁት ልክ የዛሬ ሳምንት ነበር። ወደ ስፍራው ተጉዘው የመጡት ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ ህወሓት በሰሜን ዕዝ ላይ የፈፀመው ጥቃት ታሪክ ይቅር የማይለው ነው ብለዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/Ethiopia-conflict-11-10-2020/5655729.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/Ethiopia-conflict-11-10-2020/5655729.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 10 Nov 2020 23:41:03 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/Ethiopia-conflict-11-10-2020/5655729.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/B423288D-EBC9-44F7-A09B-63C119EE19BF_cx0_cy7_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>&quot;የሰሜኑ እርምጃ የሚጠናቀቀው ወንጀለኞች ለፍርድ ሲቀርቡ ነው&quot;- ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ</title>
            <description>በህወሓት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ወንጀለኞችን ለፍርድ በማቅረብ በቅርቡ ይጠናቀቃል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ።


&quot;ኢትዮጵያ ሁኔታው እንደሚያሳስባቸው የገለፁ ወዳጆቿን ታመስግናለች&quot; ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ግን የአንዲት ሉዓላዊት ሃገር የውስጥ ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰዋል።


በሌላም በኩል “የኢትዮጵያ አየር ሃይል የጦር ጄት መትተን ጥለናል” በሚል በህወሓት የተሰጠውን መረጃ የመከላከያ ሚኒስቴር አጣጥሏል።


የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር ኢንዶክትሪኔሽን ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል መሀመድ ተሠማ ለአሜሪካ ድምፅ ሲናገሩ መረጃው ሕዝብን ማደናገሪያ ነው በማለት ነው ያስረዱት።


“የተመታ ጄትም የለም። ጄቶቻችን በሥራ ላይ ናቸው” ብለዋል ጄነራሉ።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-military-attack-11-9-2020/5654044.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-military-attack-11-9-2020/5654044.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 09 Nov 2020 21:18:37 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-military-attack-11-9-2020/5654044.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/1E167B31-6563-45ED-A0C9-4E0745EA4B94_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>&quot;በህወሓት ላይ የተወሰደው የመጀመሪያ ዙር እርምጃ በስኬት ተጠናቋል&quot; - ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ</title>
            <description>በህወሓት ላይ የተወሰደው የመጀመሪያ ዙር እርምጃ በስኬት ተጠናቋል ሲሉ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ። ተጨማሪ ጥቃት መሰንዘር ወደማይችልበት ደረጃ አድርሰነዋል፣ የማድረግ አቅሙንም አዳክመናል ነው ብለዋል ጠ/ሚኒስትሩ።


ዘመቻውም የህወሓት ቡድን ሙሉ በሙሉ ለህግ እስከሚቀርብ ድረስ እንደሚቀጥል ነው ማምሻውን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ባደረጉት ንግግር ያመለከቱት።


ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀድም ሲል ባሰፈሩት ፅሁፍ የመከላከያ ሠራዊት እየወሰደ ያለው እርምጃ ግልፅ ውስን እና ሊደረስባቸው የሚችል አላማዎች ያሉት ነው ብለዋል።


ኩሩ ኢትዮጵያዊ የሆነው የትግራይ ሕዝብና ሌሎችም ከህግ ተጠያቂነት ባመለጡ ወንጀለኞች እገታ ሥር ሊቆዩ አይችሉም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ ለወንጀለኞች ቦታ የላትም ሲሉም አክለዋል::


ትናንት በትግራይ ቴሌቪዥን የቀረቡት የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካዔል ደግሞ የተቃጣብንን ጦርነት በድል እንወጣለን ነበር ያሉት።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/Ethiopia-military-update-11-6-2020/5650974.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/Ethiopia-military-update-11-6-2020/5650974.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 06 Nov 2020 20:39:48 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/Ethiopia-military-update-11-6-2020/5650974.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/EE62FF5F-598B-416B-9543-987268185104_cx0_cy2_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በጦርነቱ ንጹሃን ዜጎች እንዳይጎዱ ጥንቃቄ እንደሚደረግ ተገለፀ</title>
            <description>ህወሓት በትግራይ ክልል በሚገኙ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ካምፖች ላይ ጥቃት እንደፈፀመ የሚገልፁ ሪፖርቶች በእጅጉ እንዳሳሰቧቸው የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፔዎ ገለጹ።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/tigray-situation-reaction-11-5-2020/5649575.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/tigray-situation-reaction-11-5-2020/5649575.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 05 Nov 2020 21:17:56 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/tigray-situation-reaction-11-5-2020/5649575.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0CB48274-9486-4EE4-9A92-56BB25A9196C_cx0_cy3_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጥያቄዎችን ይፈታል የተባለ ጥናት እየተካሄደ ነው</title>
            <description>ካለፈው ሰኔ ጀምሮ ሲያካሂድ የቆየውን የዳሰሳ ጥናት የፊታችን ግንቦት እንደሚያጠናቅቅና ምክረ ሐሳብም እንደሚያቀርብ የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን አስታወቀ።


ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚቀርበውም አንተም ተው፣ አንችም ተይ ዓይነት መፍትሔ ሳይሆን በጥናት ላይ የተመሰረተ ምክረ ሐሳብ ነው ብለዋል የኮሚሽኑ ፅ/ቤት ዳይሬክተር አወል ሁሴን።


ከአስተዳደር ወሰን እና ከማንነት ጋር በተያያዘ ለሚፈጠሩ ግጭቶች የመጨረሻ እልባት ለመስጠት እንዲያስችል ነው ኮሚሽኑ በየካቲት 2011 በአዋጅ የተቋቋመው።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/border-commission-interview-10-29-2020/5640736.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/border-commission-interview-10-29-2020/5640736.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 29 Oct 2020 23:14:52 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/border-commission-interview-10-29-2020/5640736.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/44FAE358-A530-4A0A-8A5E-B0B84183F54E_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>“ኢትዮጵያ ከፖለቲካ ለውጡ ወዲህ” - አዲስ መጽሃፍ</title>
            <description>ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ መዋቅራዊ ኃይሎች ሃገሪቱ ለያዘችው የለውጥ ሂደት ፈተና መሆናቸውን ምሁራንና የፖለቲካ ተንታኞ ተናግረዋል። ሃገሪቱ የለውጥ ጉዞ ብትጀምርም መታለፍ ያለባቸውን መሰረታዊ እንቅፋቶች እንዳሉ ጠቁመዋል።


“ኢትዮጵያ ከፖለቲካ ለውጡ ወዲህ” በሚል ርዕስ ለታተመውና ዛሬ ይፋ ለተደረገው መጽሃፍ፣ ፅሁፎች ያበረከቱ ምሁራን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በተካሄደ ሥነ ስርዓት ላይ ሐሳባቸውን አካፍለዋል።


በመጽሃፉ ውስጥ የተካተቱ ምክረ አዘል ሐሳቦችም ለፖሊሲ ግብዓት እንደሚጠቀምባቸው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት ገልጿል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/Ethiopia-in-the-wake-of-political-reforms-10-22-2020/5632036.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/Ethiopia-in-the-wake-of-political-reforms-10-22-2020/5632036.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 23 Oct 2020 00:28:04 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (እስክንድር ፍሬው)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/Ethiopia-in-the-wake-of-political-reforms-10-22-2020/5632036.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/4915C7A3-F921-446A-8A28-3B0F0D66299D_cx0_cy11_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>