<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com</link>
        <description>የአሜሪካ ድምፅ  (ቪኦኤ) ከአርባ በላይ በሆኑ ቋንቋዎች ከዩናይትድ ስቴትስ ለመላው ዓለም የሚሠራጭ ዓለምአቀፍ ብዝኃ ሚድያ የሥርጭት አገልግሎት ነው</description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2020 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Tue, 29 Dec 2020 01:38:35 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/a$piy_et-iyy" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>&quot;የኦነግ ሸኔን ታጣቂዎች ትደግፋላችሁ&quot; በሚል የታሰሩ ፍ/ቤት አልቀረቡም</title>
            <description>“የኦነግ ሸኔን ታጣቂዎች ትደግፋላችሁ” በሚል በቤኒሻንጉል ጉምዝ መተከል ዞን ውስጥ የተያዙ ሰዎች ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ከሦስት እስከ ስድስት ወራት መታሰራቸውን ቤተሰቦቻቸው ገልፀዋል።


ግለሰቦቹ በቡለንና ድባጤ ወረዳዎች ፖሊስ ጣቢያዎች እንዲሁም ግልገል በለስ ማረሚያ ቤት የሚገኙ ሲሆን ከመተከል ዞን አለመረጋጋት ጋር ተያይዞ በቁጥጥር ሥር ያሉት 1 ሺህ 137 ሰዎች መሆናቸውን የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ምክትል ኮሚሽነር ኮማንደር ምሥጋናው ኢንጂፈታ ለቪኦኤ ገልፀዋል።


659 ሰዎች ጉዳያቸው ውሳኔ ሳይሰጠው በግልገል በለስ ማረሚያ ቤት ለወራት ተይዘው እንደሚገኙና ይሄም የሆነው በዞኑ ውስጥ በሚታየው ያለመረጋጋት ሳቢያ ፖሊስ ማስረጃ አጠናቅሮ ለፍርድ ቤት ማቅረብ ባለመቻሉ መሆኑን ኮማንደር ምሥጋናው ተናግረዋል።


በመተከል ዞን የተለያዩ ወረዳዎችም 478 ሰዎች ፖሊስ ጣቢያዎች ውስጥ ታስረው እንደሚገኙና በመተከል ዞን የቀጠለው አለመረጋጋት የህግ ሂደቱን ለመቀጠል አዳጋች ሊያደርገው እንደሚችልም ምክትል ኮሚሽነሩ አመልክተዋል።


ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/benishangul-detainees-12-28-2020/5716296.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/benishangul-detainees-12-28-2020/5716296.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 28 Dec 2020 23:30:36 +0300</pubDate>
            <category>ኢትዮጵያ</category><category>ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/benishangul-detainees-12-28-2020/5716296.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0398C7EB-BC8F-4CA2-84DA-22CBD6319DA9_cx0_cy4_cw0_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እጃቸውን እንዲሰጠ የተጠየቁ ኃይሎች ጉዳይ</title>
            <description>የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሃሰን ክልሉ ውስጥ ያሉ ታጣቂዎች መሣሪያ እንዲፈቱ ያሳሰቡበት ቀነ ገደብ ቢጠናቀቅም እጅ የሰጠ የለም ሲሉ የክልሉ ኮሙኒኬሽንስ ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ኃላፊ አሳውቀዋል።


የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ መለሰ በየነ አሁንም በሩ ክፍት ስለሆነ ማንኛውም ታጥቆ የሚንቀሳቀስ ኃይል ለመንግሥት እጅ ሊሰጥ ይችላል ብለዋል።


በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 23 ታጣቂዎች ዛሬ በመተከል ዳንጉር ወረዳ ተደምስሰዋል ሲሉ ኃላፊው ገልፀዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/benshangul-gumz-ultimatum-deadline-12-8-2020/5691853.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/benshangul-gumz-ultimatum-deadline-12-8-2020/5691853.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 08 Dec 2020 21:18:03 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/benshangul-gumz-ultimatum-deadline-12-8-2020/5691853.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9102800F-528F-49FF-A491-136947325CB0_cx0_cy11_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ከቄለም ወለጋ አንፊሎ ወረዳ ሙጊ ከተማ የተፈናቀሉ ሥጋታቸውን ገለፁ</title>
            <description>ከቄለም ወለጋ አንፊሎ ወረዳ በፀጥታ ስጋት ምክንያት ወደ ጋምቤላ መሸሻቸውን አንዳንድ ግለሰቦች ገለፁ።
ከተፈናቀሉት መካከል የሸሸነው ታጥቀው ከሚንቀሳቀሱ የኦነግ ሸኔ አባላት ጥቃት ለማምለጥ ነው ብለዋል።</description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2020/12/04/fa9a5721-46ca-45a2-941b-c18c2096d0a7_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/displaced-fear-of-attack-12-4-2020/5687842.html</guid>            
            <pubDate>Sat, 05 Dec 2020 00:36:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>አጭር ድምጽ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9617342C-991C-4CB8-ADF0-0255A9D4FD3A_cx0_cy32_cw100_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ውስጥ እጃቸውን እንዲሰጠ የተጠየቁ ሃይሎች</title>
            <description>የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሃሰን በመተከል ዞን የሚንቀሳቀሱ የህወሓት ጥፋት አስፈጻሚ ርዝራዦች እጃቸውን እንዲሰጡ ጥሪ ማቅረባቸውን ተከትሎ እስከ አሁን እጅ የሰጠ እንደሌለ የክልሉ ኮሙኒኬሽንስ ጉዳዮች ፅህፈት ቤት አሳወቀ።</description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2020/12/02/144497c5-9109-47ff-91cd-f91cfbbe58a5_48k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/benishangul--rebeles-12-2-2020/5684987.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 03 Dec 2020 00:42:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>አጭር ድምጽ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9102800F-528F-49FF-A491-136947325CB0_cx0_cy9_cw100_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ውስጥ እጃቸውን እንዲሰጠ የተጠየቁ ሃይሎች</title>
            <description>የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሃሰን በመተከል ዞን የሚንቀሳቀሱ የህወሓት ጥፋት አስፈጻሚ ርዝራዦች እጃቸውን እንዲሰጡ ጥሪ ማቅረባቸውን ተከትሎ እስከ አሁን እጅ የሰጠ እንደሌለ የክልሉ ኮሙኒኬሽንስ ጉዳዮች ፅህፈት ቤት አሳወቀ።


የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ መለሰ በየነ እጅ ለመስጠት የተሰጠው ጊዜ አንድ ሳምንት በመሆኑ አሁንም በተቀሩት ቀናት እነዚህ የጥፋት ሃይሎች እጃቸውን በሰላማዊ መንገድ ይስጡ ሲሉም አሳስበዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/benihsangul-rebeles-ultimatum-12-2-2020/5684988.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/benihsangul-rebeles-ultimatum-12-2-2020/5684988.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 03 Dec 2020 00:40:46 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/benihsangul-rebeles-ultimatum-12-2-2020/5684988.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9102800F-528F-49FF-A491-136947325CB0_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሆሮ ቡሉቅ ወረዳ እና በሰሜን ሸዋ ደራ ወረዳ ሰዎች መገደላቸው ተገለፀ</title>
            <description>በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሆሮ ቡሉቅ ወረዳ የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች የኦሮሞ ነፃነት ሸማቂዎችን ከመደገፍ ጋር በተያያዘ ሁለት ወጣቶችንና አንድ መምህር ገደሉ ሲሉ ከቤተሰብ መካከል የቅርብ ዘመድ ነኝ ያሉ ግለሰብ ገለፁ።


የወረዳው ፀጥታና አስተዳደር ፅህፈት ቤት ኃላፊ ግለሰቦቹ ስለመገደላቸው ለፅህፈት ቤታቸው ያሳወቀ ባለመኖሩ ምንም አይነት ምርመራ አለመደረጉን አስታውቋል።


በተመሳሳይ ሁኔታ በሰሜን ሸዋ ደራ ወረዳም አንድ ግለሰብ በፀጥታ ሀይሎች ከተያዘ በኋላ ተገድሎ መገኘቱን አንድ የዐይን እማኝ ገልጿል።


የደራ ወረዳ ፀጥታና አስተዳደር ፅህፈት ቤት ኃላፊ ይህ ተገደለ የተባለው ግለስብ በወረዳችንም አልታሰረም፤ በወረዳችን የተገደለ ሰውም የለም ብለዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/oromia-killing-11-25-2020/5676125.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/oromia-killing-11-25-2020/5676125.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 25 Nov 2020 19:09:04 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/oromia-killing-11-25-2020/5676125.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/BEE55E25-DFE8-40BD-98DE-179B7EA83857_cx0_cy20_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የባለሞያዎች አስተያየት በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ስለሚስተዋሉ ግጭቶች</title>
            <description>በቤንሻንጉል ክልል መተከል ዞን ውስጥ ለሚስተዋሉ ሰብዓዊ ቀውሶች መነሻ የክልሉ ህገመንግሥት ለሌሎች ነዋሪዎች የባለቤትነት መብት መንፈጉ መሆኑን የፖለቲካ ሳይንስ መምህሩ ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው ተሰማ ገለፁ።


የህግ ባለሞያው አቶ ተመስገን ገመቹ ደግሞ የቤንሻንጉል ጉሙዝ በተለይ የጉሙዝ ብሄር ተወላጆች


“መሬታችንን እንቀማ ይሆን?” የሚል ስጋት ወደ ግጭት ሊያስገባቸው ይችላል ይላሉ።


ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው &quot;የህወሓት ጣልቃ ገብነት በመተከል ችግር ውስጥ ድርሻ አለው ሲሉ አቶ ተመስገን ደግሞ &quot;ችግራቸውን ወደ ውጭ አካል ከመጠቆም የክልሉ አመራሮች ራሳቸውን ማየት አለባቸው&quot; ብለዋል።


&quot;ዜጎች ላይ የሚደርሰው ግድያ እንዲቆምና መተከልን ለማረጋጋት ፖለቲካዊ መፍትሄ ያስፈልጋል&quot; ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል ምሁራኑ።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/benishangul-attack-causes-11-18-2020/5667712.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/benishangul-attack-causes-11-18-2020/5667712.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 18 Nov 2020 21:58:37 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/benishangul-attack-causes-11-18-2020/5667712.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/BEE55E25-DFE8-40BD-98DE-179B7EA83857_cx0_cy20_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፀጥታ ሁኔታ</title>
            <description>በቤኒሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን ድባጢ ወረዳ፣ ትናንት የታጠቁ ሃይሎች ንፁሃን ዜጎችን መግደላቸውን የክልሉ መንግሥት አስታወቀ።


የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽንስ ጉዳዮች ሃላፊ አቶ መለሰ በየነ &quot;ንፁሃን ዜጎች ላይ ዘግናኝ ጥቃት ተፈፅሟል። ጥቃት ፈፃሚዎቹ ከህወሓት የጥፋት ተልእኮ የተሰጣቸው ናቸው&quot; ብለዋል።


ሃላፊው ጥቃቱን የፈፀሙት የቤኒሻንጉል ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ አባላት ናቸው ቢሉም ከድርጅቱ ለማረጋገጥ አልተቻለም።


የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፀጥታና ደኅንነትን ለማጠናከር ፈጣንና የተቀናጀ እርምጃ አስፈላጊ ነው ሲል መግለጫ አውጥቷል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/gunmen-civilian-attack-11-16-2020/5664557.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/gunmen-civilian-attack-11-16-2020/5664557.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 16 Nov 2020 19:42:41 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/gunmen-civilian-attack-11-16-2020/5664557.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9102800F-528F-49FF-A491-136947325CB0_cx0_cy12_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>Benishangul-Gumuz, Ethiopia</title>
            <description></description>
            <link>https://av.voanews.com/clips/VAM/2020/11/15/f99bdb1b-bb8e-4223-943c-c86852bc01bb_32k.mp3</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/benishangul-gumz-killings-11-15-20/5663609.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 16 Nov 2020 00:07:00 +0300</pubDate>
            <category>ፖለቲካ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/FB5EB418-98F0-40D9-899D-4E1BE617FDAC_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በቤንሻንጉል መተከል ዞን ድባጤ ወረዳ ታጣቂዎች  ሰላማዊ ሰዎች መግደላቸው ተገለጸ</title>
            <description>በቤንሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን ድባጤ ወረዳ ታጣቂዎች ትናንት ሰላማዊ ሰዎች መግደላቸውን የክልሉ መንግሥት አስታወቀ።


ግድያውን የፈጸሙት ከህወሃት “የጥፋት ተልዕኮ የተሰጣቸው” ያሏቸው የቤንሻንጉል ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ አባላት እንደሆኑ የክልሉ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽንስ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ መለሰ በየነ ተናግረዋል። ከንቅናቄው የተሰማ ጥቃቱን የሚያረጋግጥም ይሁን የሚያስተባብል መግለጫ እስካሁን ለማግኘት አልተቻለም።


የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮምሽን በበኩሉ ባወጣው መግለጫ “በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ጸጥታ እና ደህንነትን ለማጠናከር ፈጣን እና የተቀናጀ ርምጃ አስፈላጊ ነው” ሲል አሳስቧል።






 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/ethioipia-benishangul-killing/5663586.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/ethioipia-benishangul-killing/5663586.html</guid>            
            <pubDate>Sun, 15 Nov 2020 23:15:11 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/ethioipia-benishangul-killing/5663586.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0398C7EB-BC8F-4CA2-84DA-22CBD6319DA9_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ጅማ ውስጥ ግለሰቦች በህገወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን ከንቲባው አስታወቁ</title>
            <description>በጅማ ከተማ የህወሓትን ተልዕኮ ለማስፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 26 ግለሰቦች ታሰሩ ሲሉ የከተማው ከንቲባ አስታወቁ።


ከንቲባው አቶ ትጃኒ ናስር ለእኩይ ተግባር የሚጠቀሙት የጦር መሳሪያዎችና ከ700 ሺ ብር በላይ የሚመነዘር የውጭ ሃገር ገንዘብም ተይዟል ብለዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 


 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/jimma-arrest-11-11-2020/5656733.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/jimma-arrest-11-11-2020/5656733.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 11 Nov 2020 18:23:40 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/jimma-arrest-11-11-2020/5656733.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9617342C-991C-4CB8-ADF0-0255A9D4FD3A_cx0_cy38_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በምዕራብ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች የስልክ እና የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡ ተገለፀ</title>
            <description>በምዕራብ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች አንዳንድ ከተሞችና ወረዳዎች ውስጥ የስልክና ኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡን ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት እንደተቸገሩ የተናገሩ ግለሰቦች ገለፁ።


የኦሮምያ ኮሙኒኬሽንስ ቢሮ ሃላፊ አቶ ጌታቸው ባልቻ በተጠቀሱ ስፍራዎች አገልግሎቱ ስለመቋረጡ መረጃ እንደሌላቸው አስታውቀዋል።


መንግሥት &quot;በቦታው የሚንቀሳቀሱ አጥፊ ሃይሎች ላይ እርምጃ እየወሰደ ነው። አካባቢውን ሰላም ለማድረግ እርምጃው ይቀጥላል&quot; ብለዋል አቶ ጌታቸው።


በዚህ ዙሪያ ከኢትዮ-ቴሌኮም የሥራ ሃላፊዎች መረጃ ለማግኘት አልተቻለም።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/west-wollega-blackout-11-10-2020/5655599.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/west-wollega-blackout-11-10-2020/5655599.html</guid>            
            <pubDate>Tue, 10 Nov 2020 22:03:45 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/west-wollega-blackout-11-10-2020/5655599.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9617342C-991C-4CB8-ADF0-0255A9D4FD3A_cx0_cy38_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በቤንሻንጉል እና ጋምቤላ ክልል “ህገወጥ ተግባር ሊፈፅሙ ነበር” የተባሉ ግለሰቦች ተያዙ </title>
            <description>በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል &quot;መንግሥት የለም በማለት ህገወጥ ተግባርን ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 37 ግለሰቦችን ይዣለሁ&quot; ሲል የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።


&quot;ሠላሳ የሚሆኑ የህወሓት አባላትና ባለሃብቶች ሲሆኑ ሰባቱ ደግሞ የኦነግ ሸኔ አባላት ናቸው&quot; ብሏል የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር አብዱላዚዝ መሃመድ።


በተመሳሳይ ሁኔታ በጋምቤላ ክልልም ብሄር ብሄረሰቦችን ለማጋጨት አሲረው ሲንቀሳቀሱ ነበር በሚል የተጠረጠሩ የህወሃትና የኦነግ ሸኔ የጥፋት ኃይሎች ናቸው ያላቸው 19 ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታውቋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/arrest-in-benishangul-and-gambella-11-5-2020/5649393.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/arrest-in-benishangul-and-gambella-11-5-2020/5649393.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 05 Nov 2020 18:50:55 +0300</pubDate>
            <category>ኢትዮጵያ</category><category>ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/arrest-in-benishangul-and-gambella-11-5-2020/5649393.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/08D7B813-6E2B-40B9-AB2F-0F70F0BCF6D7_cx0_cy10_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በምዕራብ ወለጋ በንፁሃን ዜጎች ላይ የተፈፀመው ግድያ </title>
            <description>በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ውስጥ &quot;የኦሮሞ ነፃነት ሸማቂዎች ወይም ኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በፈፀሙት ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት ቁጥራቸው በወል ያልታወቀ ንፁሃን ዜጎች መገደላቸውን ከጥቃቱ ያመለጡ የአይን እማኞች ተናግረዋል።


ማንነትን መሰረት ባደረገው ጥቃት ማዘናቸውን የገለፁት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መንግሥት ሁሉንም ዓይነት አማራጮች ተጠቅሞ የችግሩን ይነቅለዋል ብለዋል።


የኢትዮጵያ ጠላቶች ወይ እኛ እንገዛለን ወይ ሀገር አትኖርም ብለው ተነስተዋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለዋል።


የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ በወጡት መግለጫ በኦነግ ሸኔ እና በወያኔ የጥፋትና የሽብር ሴራ ኢትዮጵያ አትፈረስም” ብለዋል።


በጥቃቱ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ግን በመንግሥት በወጡ መግለጫዎች አልተጠቀሰም።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/gulesso-attack-11-2-2020/5645324.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/gulesso-attack-11-2-2020/5645324.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 02 Nov 2020 21:43:49 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/gulesso-attack-11-2-2020/5645324.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/88B76004-B253-4D58-A394-4404FB3CA31A_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በመተከል ኦነግ ሸኔን በመርዳት ተጠርጥረው የታሰሩ እንዳሉ ተነገረ</title>
            <description>ከኦሮሞ ነፃነት ሸማቂዎች ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የተጠረጠሩ የቤተሰብ አባሎቻቸው ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ለወራትና ለሳምንታት መታሰራቸውን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የሚገኙ አንዳንድ ነዋሪዎች ተናግረዋል።


የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኮሙዩኒኬሽንስ ኃላፊ አቶ መለሰ በየነ በበኩላቸው በአንዳንድ ወረዳዎች መንግሥት ኦነግ ሸኔ ብሎ የሚጠራቸው ታጣቂዎች እንቅስቃሴ መኖሩን ገልፀው ታሰሩ ስለተባሉ ሰዎች ግን መረጃ እንደሌላቸው አመልክተዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/olf-10-23-2020/5633317.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/olf-10-23-2020/5633317.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 23 Oct 2020 21:36:08 +0300</pubDate>
            <category>ኢትዮጵያ</category><category>ዜና</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/olf-10-23-2020/5633317.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/FCB2F48A-0EC9-4232-A222-56AB2205F5B0_cx0_cy12_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ነቀምቴ ከተማ ውስጥ ሁለት ሰዎች ተገደሉ</title>
            <description>በነቀምቴ ከተማ ሁለት የመንግሥት ፀጥታ አስከባሪዎች ባልታወቁ ታጣቂዎች መገደላቸውን የከተማው ኮሙዩኒኬሽንስ ፅህፈት ቤት አስታወቀ።


አንድ የኦሮምያ ልዩ ኃይል አባልና አንድ የኦሮምያ ፖሊስ አባል ናቸው በሥራ ላይ እንዳሉ መገደላቸው የተገለፀው።


የከተማው አስተዳደርና ፅህፈት ቤት እንዳለው ጥቃት በተፈፀመበት ሥፍራ የነበረ ሌላ አንድ ግለሰብም ቆስሏል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/nekemte-killing-10-19-2020/5627354.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/nekemte-killing-10-19-2020/5627354.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 19 Oct 2020 21:06:17 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/nekemte-killing-10-19-2020/5627354.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9617342C-991C-4CB8-ADF0-0255A9D4FD3A_cx0_cy36_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፀጥታ ጉዳይ</title>
            <description>መተከል ዞን በማዘዣ ትዛዝ ሥር እንዲተዳደር ተወሰነ። በመተከል ዞን የደረሱ ጥቃቶችን አስመልክቶ ከአማራና ቤንሻንጉል ክልሎች መሪዎች ጋር መወያየታቸውን ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታውቀዋል።


በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመተከል ዞን ውስጥ አልፎ አልፎ ከሚከሰቱ ችግርች በስተቀር አንፃራዊ መረጋጋት መስፈኑን ደግሞ የክልሉ ኮሙኒኬሽንስ ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።


የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ መለሰ በየነ፤ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮነን በተገኙበት ውይይት ከተካሄደ በኋላ ዞኑ በማዘዣ ማዕከል ትዕዛዝ ሥር እንዲተዳደር ተወስኗል ብለዋል።


ማኅበረሰቡ አብሮነቱን አጠናክሮ የሚመጣበትን ማናቸውንም ጥቃት መመከት የሚያስችል ሥራ መሰራት እንዳለበት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰናል ሲሉም ተናግረዋል። በዞኑ ሰባት ወረዳዎች ስልጠና የወሰዱ ነባርና አዳዲስ ሚሊሻዎችም ከፀጥታ አካላት ጎን ሆነው ሰላም ለማስፈን ይሠራሉ ብለዋል ኃላፊው።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/benshangul-gumz-conflict-10-16-2020/5624487.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/benshangul-gumz-conflict-10-16-2020/5624487.html</guid>            
            <pubDate>Fri, 16 Oct 2020 21:22:58 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/benshangul-gumz-conflict-10-16-2020/5624487.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/0398C7EB-BC8F-4CA2-84DA-22CBD6319DA9_cx0_cy3_cw0_w800_h450.png" length="0" type="image/png"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኦሮምያ ክልል የታሰሩ ግለሰቦች ቤተሰቦች አቤቱታ</title>
            <description>በምዕራብ ኦሮምያ አንዳንድ ከተሞችና ወረዳዎች ግለሰቦች ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ለወራት መታሰራቸውን ቤተሰቦቻቸው አንዳንዶቹ ለቪኦኤ ገለፁ።


እስራት ከተፈፀመባቸው ስፍራዎች መካከል የምዕራብ ወለጋ ሰዮ ኖሌ ወረዳ አስተዳደርና ፀጥታ ፅህፈት ቤት በወረዳቸው ወንጀል ፈፅመው እንጂ ሸማቂዎችን ትደግፋላችሁ ተብለው የታሰሩ እንደሌሉ አስታውቆ፣ ፖሊስ ወንጀላቸውን እያጣራ ነው ብለዋል።


ከተለያዩ ከተሞች ለሚነሱት የእስራት ቅሬታዎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት ሥራ ኃላፊዎች ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።


ከዚህ በፊት የፀጥታና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ፍርድ ቤቶች ዝግ ስለሆኑ በምዕራብ ኦሮምያ የታሰሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት አለመቅረባቸውንና ምርመራው ጊዜ ወሳጅ መሆኑንም ጭምር ገልፀው ነበር። የኢትዮዽያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ቅሬታው እንዳልቀረበለት ገልጿል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/detention-due-process-10-15-2020/5622979.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/detention-due-process-10-15-2020/5622979.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 15 Oct 2020 21:19:20 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/detention-due-process-10-15-2020/5622979.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9617342C-991C-4CB8-ADF0-0255A9D4FD3A_cx0_cy39_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ሦስት ዩኒቨርስቲዎች ለ2013 የትምህር ዘመን ዝግጁ መሆናቸውን ጠቆሙ</title>
            <description>የአምቦ፣ ወለጋና ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲዎች በ2013 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ለማስተማር ዝግጅት አድርገናል ብለዋል።


የዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዚዳንቶች ዩኒቨርሲቲዎቻቸው የኮቪድ-19 ወረርሽኝን አስቀድሞ እየተከላከሉና የተማሪዎችን ደኅንነት እያስጠበቁ ትምህርት ለመስጠት የሚያስችል ቁመና ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።


ባለፈው ዓመት በኮቪድ-19 ምክንያት ትምህርታቸውን አጠናቀው ያልተመረቁ ተማሪዎችን ተቀብሎ አስተምሮ በሁለት ወራት ውስጥ ለማስመረቅም የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ውሳኔ እየጠበቁ መሆናቸውን ገልፀዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/western-oromia-universities-10-14-2020/5621763.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/western-oromia-universities-10-14-2020/5621763.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 15 Oct 2020 02:16:36 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/western-oromia-universities-10-14-2020/5621763.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9617342C-991C-4CB8-ADF0-0255A9D4FD3A_cx0_cy36_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>ቤኒሻንጉል ጉምዝ ውስጥ 14 ሰው በታጣቂዎች ተገደለ</title>
            <description>በቤኒሻንጉል ጉምዝ መተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ ውስጥ “የሚንቀሳቀሱ ሽፍቶች ጉዞ ላይ የነበሩ አሥራ አራት ሰዎችን ገድለዋል” ሲል የክልሉ ፀጥታና ሰላም ግንባታ ቢሮ አስታውቋል።


ከሟቾቹ አንዱ ቻይናዊ መሆኑም ታውቋል።


በ14 የታጠቁ ሽፍቶች ላይ እርምጃ መወሰዱንና ሁለቱ በመንግሥት ፀጥታ አስከባሪዎች መያዛቸውን የቢሮው ኃላፊ አቶ ጋሹ ዱጋስ ገልፀዋል።


ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።






 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/benshangul-attack-10-8-2020/5613995.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/benshangul-attack-10-8-2020/5613995.html</guid>            
            <pubDate>Thu, 08 Oct 2020 20:46:18 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>ኢትዮጵያ</category><author> voadigital@voanews.com (ናኮር መልካ)</author><comments>https://amharic.voanews.com/a/benshangul-attack-10-8-2020/5613995.html#comments</comments><enclosure url="https://gdb.voanews.com/9102800F-528F-49FF-A491-136947325CB0_cx0_cy11_cw0_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>