በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኦሮሚያ ዛሬ ግድያና የተቃውሞ ሰልፍ ማስተናገዷን ነዋሪዎችና የክልል ባለሥልጣናት ተናገሩ


ነቀምት ከተማ የተካሄደ ሰልፍ
ነቀምት ከተማ የተካሄደ ሰልፍ

በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በሐዊ ጉዲና ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች ውስጥ የሶማሌ ክልል የታጠቁ ኃይሎች ገብተው ከ80 በላይ የአርሶ አደር ቤቶች ማቃጠላቸውንና እስካሁን ቦታውን ተቆጣጥረው መያዛቸውን የዞኑ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ ተናገሩ። በሌላ በኩል ጋዱሎ በተባለ ቀበሌ ላይ በዚህ የተበሳጩ የሟች ቤተሰቦች የኢትዮጵያ ሶማሌዎችን ማጥቃታቸውን መረጃ እንደደረሳቸው ተናግረዋል።

ኦሮሚያ ዛሬ ግድያና የተቃውሞ ሰልፍ ማስተናገዷን ነዋሪዎችና የክልል ባለሥልጣናት ተናገሩ
please wait

No media source currently available

0:00 0:13:00 0:00

እስካሁን ሁለት ሰው ሞቶ ሁለት ሰው መቁሰሉን ተናገረው የመብራትና የኢንተርኔት አገልግሎት በመቋረጡ መረጃ ለማግኘት ተቸግረናል ብለዋል። በሁኔታዎች ግራ ተጋብተናል ያሉት የዞኑ ኃላፊ በዚህ ሳምንት ብቻ ከዚህ አደጋ ውጪ በዞኑ ስድስት ሰው ተገሎ አምስት ቆስሏል ብለዋል።

የሶማሌ ክልልን ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ስልካቸው ባለመነሳቱና ተነስቶም በመዘጋቱ ማካተት አልተቻለንም። በሌላ በኩል በምዕራብ ወለጋና በምስራቅ ወለጋ የሚገኙ ነዋሪዎች “ግድያ ይቁም መከላከያ ከሕዝብ ቆን ይቁም” የሚል መልዕክት ያዘለ ሰላማዊ ሰልፍ መደረጉን ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናገርዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG