በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የፍልሰተኞች የክረምቱ መከራ በጣልያን

ወደ ኢጣልያ የሚገቡ ስደተኞችና ፍልሰተኞች ቁጥር እየቀነሰ የመጣ ይምሰል እንጂ ከፈረንሣይ ጋር በምትዋሰነው ውቢቱ ቬንቲሚግሊያ ከተማ ያለው ሁኔታ ግን የሚያሳየው እንደዚያ ዓይነቱን እውነት አይደለም።

ብዙዎቹ ፍልሰተኞች ወደ ፈረንሣይ ለማቋረጥ እየሞከሩና እየጠበቁ ባሉበት በዚህ ጊዜ የአውሮፓው የክረምት ወራት ብርድ እጅግ እየበረታ ሲሆን አንዳንዶቹ በዚያ ጥረታቸው ውስጥ ሕይወታቸውን ከፍለዋል።
የተሻለ ሕይወትን ፍለጋ ነው ፍልሰተኞቹን ገፍቶ አሁን ያሉበት ሁኔታ ላይ ያደረሣቸው። ከዚህ በኋላም ቢሆን ሕይወታቸውን ሊጠይቅ ለሚችል ጉዞ ወደ ፈረንሣይ ከመቀጠላቸው በፊት የተወሰነ ጊዜ ቬንቲሚግሊያ ላይ እያሳለፉ ናቸው።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG