በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የፈረንሣይ አየር መንገድ አውሮፕላን ተጠርጣሪ ቦምብ በመገኘቱ ሞምባሳ ኬንያ አረፈ

የፈረንሣይ አየር መንገድ አውሮፕላን፥ በሌሊት በረራ ወቅት በውስጡ ተጠርጣሪ ቦምብ በመገኘቱ፥ ሞምባሳ ኬንያ ላይ ሲደርስ መንገደኞቹ በሙሉ ወደሌላ አውሮፕላን እንዲዛወሩ ተደርገ።

459 መንገደኞችን አሳፍሮ ከሞሪሽየስ ወደ ፓሪስ ያመራ የነበረው የፈረንሣይ አየር መንገድ አውሮፕላን፥ በሌሊት በረራ ወቅት በውስጡ ተጠርጣሪ ቦምብ በመገኘቱ፥ ሞምባሳ ኬንያ ላይ ሲደርስ መንገደኞቹ በሙሉ ወደሌላ አውሮፕላን እንዲዛወሩ ተደርጎ ጉዟቸውን ቀጥለዋል። ሆኖም የሞምባሳ ፖሊስ አንዳንድ በበረራ ቁጥር 463 ቦይንግ 777 የፈረንሣይ አውሮፕላን ላይ የነበሩ መንገደኞችንና ያውሮፕላኑን ሠራተኞች እያነጋገረ መሆኑ ታውቋል።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG