በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አሜሪካ ለአፍሪካ 33 ቢሊዮን ዶላር አሰባሰበች


please wait

No media source currently available

0:00 0:11:11 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

እኛ ከአፍሪካ የተፈጥሮና የከርሰ-ምድር ሃብቷን ብቻ ፈልገን ሳይሆን በቅድሚያ የምናየውና የምንተማመንበትም የሰው ሃብቷ ነው ሲሉ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በአፍሪካ ላይ ያላቸውን የወደፊት ተስፋና እምቅ አቅም አድንቀው ተናግረዋል፡፡

የእርሣቸው መንግሥት ፍላጎት በአፍሪካና በአሜሪካ መካከል ያለው2ን ሥራና መተጋገዝ አሁን ባለው ሁኔታ እንዲቀጥል ማድረግ ሳይሆን ከፍ ወዳለ ደረጃ እንዲሸጋገር መሥራት ነው ብለዋል፡፡

በመላ አፍሪካ ለሚንቀሣቀሱ የግልና የመንግሥት አጋርነት ሥራዎችን ለማገዝ የተገኘው ገንዘብ ዋሺንግተን ዲሲ ላይ እየተካሄደ ላለው የአሜሪካ-አፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ ትናንት እርሣቸው ንግግር ያደርጉ እስከነበረበት ጊዜ 33 ቢሊየን ዶላር መድረሱን አስታውቀዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG