አዲስ አበባ —
የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ባለፈው ጥር የደረሱበትን የተኩስ አቁም ስምምነት መፈራረማቸው በኢጋድ በተነገረ በማግሥቱ ተቃዋሚዎቹ አልፈረምንም ሲሉ አስተባብለዋል።
የተቃዋሚዎቹ ዋነኛ ተደራዳሪ ለቪኦኤ ሲናገሩ “ስምምነቱን ፈረሙ” ተብሎ በኢጋድ የተሠራጨው መረጃ ሃሰት ነው ብለዋል።
የደቡብ ሱዳን መንግሥት ዋነኛ ተደራዳሪ ግን “ተቃዋሚዎቹ ስምምነቱን የፈረሙት በዓለም ፊት ነው” ብለዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡